ርእዮ ለይብኪ ዐይነ ልብ ዘቦ (ሰቈቃወ ድንግል)

አባ ጽጌ ድንግል ይህን ቃል የተናገረው የቅድስት ድንግል ማርያምን ስደቷን፣ በስደቷ ጊዜም የደረሰባትን መከራና ኃዘን አምልቶ በገለጸበትና አምላክን በኅቱም ድንግልና ፀንሳ በኅቱም ድንግልና የወለደች ድንግል ማርያምን ባመሰገነበት ክፍሉ ነው። ሙሉ ቃሉን እንደሚከተለው እንመልከተው።…

ምኞት

ሰው አንድን ነገር የራስ ለማድረግ በብርቱ ፍላጎት ወይንም ምኞት ይነሣሣል፤ በመልካም ምኞቱ የነፍስ ፍላጎትን ሲፈጽም የሥጋዊው ግን ወደ ጥፋት ይመራዋል፡፡ ሥጋዊ ምኞት በመጀመሪያ ጊዜያዊ ደስታን ቢሰጥም ፍጻሜው ግን መራራ ኅዘንን የሚያስከትል ነው፡፡ ጠቢቡ ሰሎሞንም ይህን በምሳሌው እንዲህ ሲል ገልጾታል፤ ‹‹የጻድቃን ምኞት መልካም ነው፤ የኃጥአን ተስፋ ግን መቅሠፍት ነው›› (ምሳሌ. ፲፩፥፳፫)

‹‹እመን እንጂ አትፍራ›› (ማር. ፭፥፴፮)

የደኅነታችን መሠረት እምነት በክርስቲያናዊ ሕይወታችን ውስጥ ችግርና መከራ በበዛብን ጊዜ ጸንተን እንድናለፍ ይረዳናል፡፡ የሰው ዘር በኃጢአቱ የተነሣ በምድር እንዲኖር ከተፈረደበት ጊዜ አንስቶ በተለያዩ ችግርና መከራ ተይዞ ሲሠቃይ ፈጣሪውን ያስባል፤ ይማጸናልም፡፡ አንዳንድ ጊዜ ፈውስን ሲያገኝ በሌላ ጊዜ ግን ወደማይመለስበት ዓለም በሞት ይለያል፤ ሆኖም ድኅነተ ሥጋንም ሆነ ድኅነተ ነፍስን ከአምላካችን እናገኝ ዘንድ እምነት ያስፈልጋል፡፡

‹‹የሞተ ሰውስ ዐረፈ፤ ነገር ግን መታሰቢያውን አድርግለት›› (ሲራክ ፴፰፥፳፫)

ሰዎች ሕያው ሆነን በፈጣሪ አምሳል እንደተፈጠርነው ሁሉ በኃጢአት ሳቢያ የተፈረደበትንን ሥጋዊ ሞት እንሞት ዘንድ አይቀሬ ነው፤ ‹‹አፈር ነህና ወደ አፈር ትመለሳለህና›› እንደተባለውም የሰው ዘር በሙሉ ወደ አፈርነት ይመለሳል፡፡ በሕፃንነትም ይሁን በጎልማሳነት እንዲሁም በእርጅና ሰዎች ይሞታሉ፡፡ በበሽታ፣ በአደጋ ወይንም በግድያ የሰዎች ሕይወት በየጊዜው ይቀጠፋል፡፡ በተለይም በዚህ ትውልድ ዓለማችን በየጊዜው በሺዎች የሚቆጠሩ ሰዎችን አያጣች ነው፡፡ በእርስ በርስ ግጭትና ጦርነት እንዲሁም የሰዎችን ሕይወት እንደ ቅጠል እያረገፈ ባለው ኮሮና በሽታ እጅግ ብዙ ሰዎች ሞተዋል፡፡ 

መክሊት

በምድራዊ ሕይወታችን ሰዎች የራሳችን መክሊት አለን፤ ይህም የእግዚአብሔር መልካም ስጦታ ነው፡፡ ስጦታዎች ሁሉ ከእግዚአብሔር ናቸውና ፈጣሪያችን ከጊዜ (ዕድሜያችን) ጋር ለእያንዳንዳችን ተሰጥኦ አድሎናል፡፡ ለአንዱ ጥበብ ለሌላው ዕውቀት ይሰጣል፤ አንዱን የዋህ ሌላውን ደግሞ ትሑት ያደርጋል፤ አስተዋይነትን ወይንም ብልሀትንም ያድላለል፤ እንዲሁም አንዱን ባለጠጋ ሲያደርገው ገንዘብ የሌለውን ደግሞ ባለሞያ ያደርገዋል፤ አንዱን የሥዕል ተሰጥኦ ሲያድለው ሌላውን ደግሞ ድምጸ መረዋ ያደርገዋል፤ የእግዚአብሔር ሥራ ድንቅ ነውና፡፡…

‹‹በቸልተኝነት እና በግዴለሽነት ፈጣሪን አትርሱ!›› ሊቀ ጉባኤ አባ አበራ በቀለ

ቸልተኝነትና ግዴለሽነት በዚህ ትውልድ ከመንጸባረቁም ባሻገር ሰዎች ፈጣሪን ረስተውና ሃይማታቸውን ትተው እንዲኖሩ አድርጓቸዋል፡፡ በተለያዩ አጋጣሚዎችም የእግዚአብሔርን ቃል ሲሰሙም ሆነ ምንባባትን ሲያነቡ በግዴለሽነትና ቸል ብሎ በማለፍ ሌሎች ነገሮች ላይ ትኩረት ይሰጣሉ፡፡ ምድራዊ ሕይወታቸው ላይ ብቻ በማተኮር ለጥቅም በመገዛትና ጊዜያዊ ደስታን ለማግኘት ሲሉም መንፈሳዊነትን ንቀው ዓለማዊ ሕይወት እየኖሩ ይገኛሉ፡፡

የኒቂያ ጉባኤ

በቢታንያ አውራጃ፤  ጥቁር ባሕር ወደብ አካባቢ የምትገኘው ኒቂያ በባሕርም ሆነ በየብስ ለሚጓዙ ሰዎች እጅግ ተስማሚ ከተማ እንደነበረች ቅዱሳት መጽሐፍት ይጠቅሳሉ፡፡ የእስክንድርያ ንጉሠ ነገሥታት መናገሻቸውን ወደ ቁስጥንኒያ እስከዛወሩበት ዘመነ መንግሥት ድረስ ከኒቂያ በ፴፪ …

መስቀል ብርሃን ለኵሉ ዓለም

ለ፭፼፭፻ ዘመናት የሰው ዘር በኃጢአት ሰንሰለት ታስሮና በጨለማ ተውጦ በነበረበት ዓመተ ፍዳ እግዚአብሔር ወልድ ለዓለም ድኅነት የተሰዋበት ግማደ መስቀሉን ‹‹መስቀል ብርሃን ለኵሉ ዓለም፤ መስቀል የዓለም ብርሃን ነው›› እያልን እንዘክረዋለን፡፡

‹‹ዘመኑን ዋጁት›› (ኤፌ. ፭፥፲፮)

ዕለታት በወራት ተተክተው፣ አዲስ ዓመት ዘመንን ወክሎ በጊዜ ዑደት ውስጥ ያልፋሉ፡፡  ሰማይና ምድር እያፈራረቁ ቀንና ሌሊትን፣ ፀሐይንና ዝናብን ይለግሳሉ፡፡ ክስተቶቹም አልፈው ዳግም እስኪመለሱ በሌሎች ይተካሉ፤ የእግዚአብሔር ስጦታ ‹‹ጊዜ›› እንደዚሁ እስከ ዓለም ፍጻሜ ይቀጥላል፡፡

ሊቀ ሐመር

በባሕሩ ማዕበል፣ በአውሎ ነፋሱ ውሽንፍር ጊዜ ጭምር ሕይወቱን ለተሳፋሪዎች ደኅንነት አሳልፎ ይሰጣል፤ ሊቀ ሐመር፡፡ ከመርከቡ ርቀው፣ ስፍራቸውንም ትተው ጠፍተውም እንዳይሰጥሙ ይከታተላቸዋል፡፡ እርሱ ጠባቂያቸው ነውና፡፡ ያለ ሥጋት ተጉዘው ወደ ባሕሩ ዳርቻ እንዲደርሱም በሰላም ይመራቸዋል፡፡