‹‹የሚራሩ ብፁዓን ናቸው›› (ማቴ.፭፥፯)

መራራት ማለት ምሕረት ማድረግ፣ ቸርነት፣ ለተጨነቀ ወይም ለተቸገረ ማዘንና ርዳታን መስጠት፣ ይቅር ማለት፣ ማዘን፣ ወዘተ ሲሆን ምሕረት ሥጋዊና ምሕረት መንፈሳዊ ተብሎ በሁለት ሊከፈል ይችላል።

‹‹አንተ ሰይጣን፤ ከአጠገቤ ሂድ!›› (ማቴ.፬፥፱)

መቈጣት ተገቢ የሚሆንበት ጊዜ አለ፤ ሊቃውንቱ እንዲህ ዓይነቱን ቊጣ ‹‹መዓት ዘበርትዕ›› ይሉታል፤ የሚገባ ቊጣ ማለታቸው ነው፡፡ ቊጣና ተግሣጽ ከሚያስፈልጋቸው ፍጥረታት አንዱ ሰይጣን ነው፡፡ ለስም አጠራሩ ክብር ይገባውና አምላካችን ኢየሱስ ክርስቶስ ተቈጥቶ የሚያውቀው በአይሁድና በአጋንንት ላይ ነው፡፡ ሰይጣንን ተቈጥቶ ካስወገደበት ቀን አንዱ ይህ ዛሬ የምናነሣው ነው፡፡ ሰይጣን አፍሮ ከኛ የሚርቅባት ቀን ምንኛ የተባረከች ቀን ናት? ጌታ ከተጠመቀ በኋላ ሳይውል ሳያድር ገዳመ ቆሮንቶስ ገባ፡፡ ካመኑ ከተጠመቁ በኋላ ወደ መንፈሳዊው ዓለም መጓዝ ይገባል ማለቱ ነው፡፡ ገዳም ገብቶ አርባ ቀንና አርባ መዓልት ጾመ ጸለየ፡፡ ሲጠመቅ በመጠመቁ ዋጋ የሚያገኝበት ሆኖ አይደለም፡፡ ውኆችን ለማክበር በጥምቀት ምእመናን እንዲወለዱ ጥምቀትን የጸጋ ምንጭ ሊያደርጋት ተጠምቋል እንዳልን በመጾሙና በመጸለዩም እንደ ኤልያስ ወደ ሰማይ ያረገ፣ እንደ ዳንኤል የአንበሳን አፍ የዘጋ፣ እንደ ሙሴም ሕግን የተቀበለበት አይደለም፡፡ ጾምና ጸሎት ዋጋ ማሰጠታቸውን አውቀው ከእሱ በኋላ የተነሡ ምእመናን እንዲይዙት ለማስተማር ነው፡፡ በዚያውም ላይ ጥንቱንም የጎዳን መብልና መጠጥ ነው፤ አሁንም ነፍሳችን የምትታደሰው በጾምና በጸሎት ስለሆነ ነው፡፡

‹‹የአባቴን ቤት የንግድ ቤት አታድርጉ›› (ዮሐ.፪፥፲፮

በኢየሩሳሌም፤ ምኵራብ ተብሎ በተሰየመው የዐቢይ ጾም ሦስተኛው ሳምንት ዕለተ እሑድ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ወደ ቤተ መቅደስ ሄደ፤ አይሁድ ንጉሥ ናቡከደነፆር ቤተ መቅደስን ካፈረሰባቸው በኋላ ሕገ ኦሪትን መማሪያ እና መጸለያ ስፍራ በማጣታቸው የሠሩት አዳራሽ ምኵራብ ነበርና፡፡ በዚያም ጌታችን በሬዎችንና በጎችን፥ ርግቦችንም የሚሸጡትን፥ ገንዘብ ለዋጮችንም ተቀምጠው ባገኘ ጊዜ ያየውን ባለመውደዱ የገመድ ጅራፍ ካዘጋጀ በኋላ በጎችንና በሮዎችን እንዲሁም ሁሉንም ከቤተ መቅደስ አስወጣቸው፤ የሻጮቹንም ገንዘብ በተነባቸው፤ ገበታዎቻቸውንም ገለበጠ፤ ርግብ ይሸጡ የነበሩትን ደግሞ፤ ‹‹ይህን ከዚህ አውጡ፤ የአባቴን ቤት የንግድ ቤት አታድርጉ አላቸው፡፡›› (ዮሐ.፪፥፲፬-፲፮)

ቅድስት

ቅድስት የሚለው ቃል ትርጉሙ ‹‹የተለየች፣ የተመረጠች፣ የከበረች›› ማለት ነው። ሥርወ ቃሉም ‹‹ተቀደሰ›› ሲሆን ፍቺው ደግም ‹‹ክቡር፣ ምስጉን፣ ምርጥ›› ማለት ነው፡፡ ሊቁ ቅዱስ ያሬድ ለዐቢይ ጾም ሁለተኛው እሑድ በአዘጋጀው ምስጋና አማካኝነት ዕለቱ ‹‹ቅድስት›› የሚል ስያሜ ተሰጥቶታል፡፡ (መጽሐፈ ሰዋስው ወግስ ወመዝገበ ቃላት ገጽ ፯፻፹፬)

‹‹ኢየሱስን በማመን የሚጸኑት ቅዱሳን ትዕግሥታቸው ይህ ነው›› (ራእ. ፲፬፥፲፪)

በዮሐንስ ራእይ ላይ ሐዋርያው ቅዱስ ዮሐንስ ‹‹ኢየሱስን በማመን የሚጸኑት ቅዱሳን ትዕግሥታቸው ይህ ነው›› በማለት የተናገረው ኃይለ ቃል የመጨረሻውን ዘመን አስጨናቂ እና ፈታኝ መሆን እንዲሁም ክርስቲያኖች ይህን ተረድተው በትዕግሥት መጽናት እንደሚገባቸው ለማስረዳት ነው፡፡ በዚሁ ምዕራፍ ቁጥር ፲፩ ላይ ለአውሬውና ለምስሉ የሚሰግዱ፣ የስሙንም ምልክት የሚጽፉ ሁሉ ቀንና ሌሊት ዕረፍት እንደሌላቸው፣ ሕዝብንና አሕዛብን ስለሚፈትነው፣ በመጨረሻ ዘመን ስለሚነሣው አውሬ እና በእርሱም ምክንያት ብዙዎች ወደ ዘለዓለማዊ እሳት እንደሚጣሉም ይገልጻል፡፡ (ራእ. ፲፬፥፲፪)

‹‹ወደ እኔ ተመለሱ፤ እኔም ወደ እናንተ እመለሳለሁ›› (ሚል ፫፥፯)

የሰው ልጆችን ጥፋት የማይወደው ፈጣሪያችን እግዚአብሔር በንስሓ እንድንመለስ ይሻል፤ ‹‹ወደ እኔ ተመለሱ፤ እኔም ወደ እናንተ እመለሳለሁ›› ብሎም ዘወትር ወደ እርሱ ይጠራናል፡፡ (ሚል ፫፥፯)

‹‹በወንድማማችነትም ፍቅርን ጨምሩ›› (፪ ጴጥ. ፩፥፯)

በክርስቲያናዊ ሕይወት ውስጥ ፍቅር ልባዊ መዋደድ ነው፤ ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ ስለ ፍቅር ሲገልጽ እንዲህ ብሏል፤ ‹‹ፍቅር ያስታግሣል፤ ፍቅር ያስተሳዝናል፤ ፍቅር አያቀናናም፤ ፍቅር አያስመካም፤ ፍቅር ልቡናን አያስታብይም፡፡ ብቻዬን ይድላኝ አያሰኝም፤ አያበሳጭም፤ ክፉ ነገርንም አያሳስብም፡፡ ጽድቅን በመሥራት ደስ ያሰኛል እንጂ፥ ግፍን በመሥራት ደስ አያሰኝም፡፡ በሁሉ ያቻችላል፤ በሁሉ ያስተማምናል፤ በሁሉም ተስፋ ያስደርጋል፥ በሁሉም ያስታግሣል፤ ፍቅር ለዘወትር አይጥልም፡፡›› (፩ ቆሮ. ፲፫፥፬-፰)

ስእለት

ስእለት ማለት ልመና፣  ምልጃ፣ ጸሎት፣ ጥየቃ እንደሆነ አለቃ ኪዳነ ወልድ ክፍሌ በመጽሐፈ መጽሐፈ ሰዋስው ወግስ ወመዝገብ ቃላት ሐዲስ ገልጸዋል፡፡ ሰዎች በተለያዩ ምክንያቶች ስእለት ይሳላሉ፡፡ ለምሳሌ ‹‹እግዚአብሔር የልቤን ጭንቀት ቢፈጽምልኝ እንዲህ አደርግለታለሁ፡፡ እመቤቴ ማርያም ስእለቴን ወይንም ልመናዬን ብትሰማኝ ለቤተ ክርስቲያን እንዲውል ጃን ጥላ አስገባለሁ››  ብለው ይሳለሉ፤ ወይንም አቅማቸው የፈቀደውን ነገር እንደሚሰጡ ቃል ይገባሉ፡፡ ስእለታቸውም ሲደርስ ‹‹እመቤታችን እንዲህ አድርጋልኛለች›› ብለው ለክብሯ መገለጫ ድባብ ወይንም የተሳሉትን ነገር ለቤተ ክርስቲያን ይሰጣሉ፡፡(ገጽ ፰፻፵፪)

‹‹አሁንስ ተስፋዬ ማነው? እግዚአብሔር አይደለምን?›› (መዝ.፴፰፥፯)

በእግዚአብሔር ተስፋ መኖር በእርሱ ላይ ሙሉ እምነት እንዲኖረን ያደርጋል፡፡ እግዚአብሔር ከጎናችን ሲሆንም እያንዳንዳችን ከምናስበው ዳርቻ መድረስ እንችላለን፡፡ ስለዚህ ተስፋችን የሚወሰነው በአምላካችን ላይ ባለን የእምነት ጥንካሬ ነው፡፡ ተስፋ በሕይወታችን ውስጥ ወደፊታችን የምንራመድበት መወጣጫ ድልድይ፣ የኑሮአችን መሠረት እንዲሁም የደስታችን መጀመሪያ ነው፤ በተስፋ ኖረን ወደ ዘለዓለማዊ ሕይወት እንሸጋገራለንና፡፡

‹‹ከአነጋገርህ የተነሣ ትጸድቃለህ፤ ከአነጋገርህ የተነሣ በቃልህ ይፈረድብሃልና›› (ማቴ. ፲፪፥፴፯)

በአንደበታችን የምንናገረው ነገር መልካም ሲሆን ጽድቅ ሆኖ እንደሚቆጠርልን ሁሉ መጥፎ ከሆነ ደግሞ ኃአጢት ይሆንና በእግዚአብሔር ፊት ተጠያቂ ያደርገናል፡፡ ኃጢአት በአብዛኛው ከንግግር የሚመነጭ ነው፡፡ በማቴዎስ ወንጌል እንደተጻፈው ‹‹ከአነጋገርህ የተነሣ ትጸድቃለህ፤ ከአነጋገረህ የተነሣ በቃልህ ይፈረድብሃልና።›› ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በተራራው ስብከት ውስጥ እንዲህ ሲል ተናግሯል፡፡ ‹‹በወንድሙ ላይ በከንቱ የሚቈጣ ሁሉ እርሱ ይፈረድበታል፤ ወንድሙንም ጨርቅ ለባሽ የሚለው በአደባባይ ይፈረድበታል፡፡›› (ማቴ. ፲፪፥፴፯፣፭፥፳፪)