‹‹ለጠቢብ ሰው ትምህርትን ስጠው፤ ጥበብንም ያበዛል›› (ምሳ. ፱፥፱)

ጥበብ ከእግዚአብሔር አምላክ የሚሰጥ፣ ከሁሉ የበለጠና የላቀ የዕውቀት ሥጦታ እንዲሁም ሰማያዊ ርስትን የሚያወርስ መንፈሳዊ ጸጋ ነው፡፡ በሰዎች አእምሮ ውስጥም ማስተዋልን ያጎናጽፋል፡፡ በዚህም ጸጋ የእውነት መንገድን ማወቅና ጽድቅን መሥራት ይቻላል፡፡ ጠቢቡ ሰሎሞን በምሳሌው እንደተናገረው ‹‹ለጠቢብ ሰው ትምህርትን ስጠው፤ ጥበብንም ያበዛል፤ ጽድቅንም አስተምረው ዕውቀትን ያበዛል፡፡›› (ምሳ. ፱፥፱)

በጎ ኅሊና

በዓለም የምናያቸው መልካምም ሆኑ ክፉ ነገሮች ሁሉ መነሻቸው ሐሳብ መሆኑን ስናስተውል ኅሊና ምን ያህል ታላቅ መሆኑን እንገነዘባለን፡፡ ኅሊና የሚለው ቃል ‹ሐሳብ፣ ምኞት፣ ከልብ የሚመነጭ ሐሳብ› ማለት ነውና፡፡ በሰው ልጆችም የአእምሮ ሥራ ሂደት ውስጥ ሐሳብ ሲደጋገም ወደ አመለካከት፣ ከሐሳብ የተነሣ አመለካከት ሲያድግም ክፉ ወይም በጎ ወደ ሆነ ማመን፣ አንድ ሰው ከሐሳቡ ወደ ማመኑ የደረሰበት መንገድም ማንነቱን እንደሚወስኑት ባለሙያዎች ያስተምሩናል፡፡ ከሐሳባችን ተነሥቶ ወደ ማንነታችን የደረሰ ነገርም ፍጻሜያችንን ይወስነዋል፡፡…

‹‹አንደበትህን ከክፉ ከልክል›› (መዝ.፴፫፥፲፫)

ሰዎች አንደበታችንን እግዚአብሔርን ለማመስገንና በጎ ነገርን ለመናገር ልንጠቀመው ይገባል። በእያንዳንዱ ንግግራችን የምናወጣቸው ቃላትም ሆነ የምንመሠርታቸው ዓረፍተ ነገሮች ከክፋት የጸዱ መሆን አለባቸው። ለዚህም ነው ቅዱስ ዳዊት በመዝሙሩ ‹‹አንደበትህን ከክፉ ከልክል፥ ከንፈሮችህም ሽንገላን እንዳይናገሩ›› በማለት የተናገረው። ሊቁ ቅዱስ ያሬድም በጾመ ድጓው ሲናገር ‹‹ይጹም ዐይን ይጹም ልሳን እዝንኒ ይጹም እምሰሚዐ ሕሡም፥ ዐይን ይጹም፣ አንደበትም ይጹም፣ ዦሮም ክፉን ከመስማት ይጹም›› ብሎ እንደተናገረ አንደበት በቃለ እግዚአብሔር እና በበጎ መንፈሳዊ ምግባራት ካልተገታችና ካልታረመች የሰውን ልጅ ወደ ጥልቅ የበደልና የጥፋት መንገድ ሊጥሉት ከሚችሉ ሕዋሳት አንዲቱ ናት። (መዝ.፴፫ (፴፬)፥፲፫)

‹‹ለነገ አትጨነቁ፤ ነገ ለራስዋ ታስባለችና›› (ማቴ.፮፥፴፬)

ጭንቀት እንደ የማኅበረሰቡ አኗኗርና የኑሮ ፍልስፍና የሚሰጠው ትርጉም ከቦታ ቦታና ከሰው ሰው ይለያያል። የሕዝቦቻቸው መሠረታዊ ፍላጎቶች ባልተሟሉባቸው አንዳንድ ሀገራት ምጣኔ-ሀብታዊ አለመረጋጋት በብዛት የሚስተዋል የጭንቀት መንሥኤ ነው። በአንጻሩ ብዙዎቹ ዜጎቻቸው የቅንጦት ሕይወት በሚመሩባቸው ‹ሥልጡን› ሀገራት ደግሞ፥ ደስታ ይገኝባቸዋል ተብለው የሚጀምሩ የዝሙት፣ የሱስ፣ የዘፈን… የመሳሰሉት እኩይ ተግባራት ከጊዜያት በኋላ እግዚአብሔርን ፍለጋ በሚቃትተውና እውነተኛ ደስታ ምን ማለት እንደሆነ አንጠርጥሮ በሚያውቀው ውሳጣዊ ኅሊናቸው ዕረፍት የለሽ ሙግት የተነሣ ደስታ ሰጪነታቸው አብቅቶ መዳረሻቸው ጭንቀት ይሆናል። በጣም የሚያሳዝነው ደግሞ ለዚህ ኅሊናዊ ምሪት የሚሰጡት መልስ በአብዛኛው አሁንም ተቃራኒውን መሆኑ ነው። ‹‹ለምንድነው የምኖረው?›› ለሚለው ጥያቄያቸው መልሳቸው ‹‹ለምንም!›› የሚል ይሆንና የሕይወታቸውን ፍጻሜ ያበላሸዋል።…

‹‹ለወገኔ ይጠቅማል በማለት ወይም በከንቱ ውዳሴ ምክንያት አንድ እንኳ አታድርጉ›› (ፊልጵ. ፪፥፫)

ወገንተኝነትን አሉታዊ በሆነ መልኩ ስንገነዘበው ለወገን፣ ለዘመድ፣ ለጓደኛ፣ ወይም የራስ ለሚሉት አካል ማድላት ነው፡፡ አያሌ ተቋሟት ዓላማና ግቦቻቸውን በሚገልጡበት ጊዜ ከሚያስቀምጡዋቸው ዕሤቶቻቸው መካከል አንዱ አለማዳላት ነው፡፡ አለማድላት ደግሞ ወገንተኝነትን የሚኮንንና ፍጹም ተቃራኒው የሆነ ታላቅ ዕሤት ነው፡፡ ወገንተኝነት ወገኔ ለሚሉት አካል ጥፋት ሽፋን በመስጠት ይገለጣል፡፡ ቆሜለታለሁ ለሚሉትም አላግባብ ቅድሚያ መስጠት ሌላኛው መገለጫው ነው፡፡

‹‹መስቀል ኀይላችን፣ ጽናታችን፣ቤዛችን፣ የነፍሳችን መዳኛ ነው››

‹‹አይሁድ ይክዱታል፤ እኛ ግን እናምነዋለን፤ ያመነውም እኛ በመስቀሉ እንድናለን፤ ድነናልም››

‹‹ሁሉን መርምሩ፤ መልካሙን ያዙ›› (፩ኛተሰ.፭፥፳)

በምንኖርባት ዓለም መጥፊያውም ሆነ መዳኛውም ከፊት ለፊታችን ነው። ባለንበት ቦታ ሁነን እግዚአብሔር የወደደውን እናደርጋለን ወይም እኛ የወደድነውን እናደርጋለን። የምንሠራቸውን ነገሮች ልንመረምራቸው ይገባል፤ በእግዚአብሔር የተወደደ መሆኑን ማለት ነው። ካልሆነ መጥፊያችንን እያደረግን መሆኑን ማወቅ አለብን።
የስልኮቻችን አጠቃቀም፣ አዋዋላችን፣ አለባበሳችን፣ አመጋገባቸን፣ አነጋገራችን፣ ወዘተርፈ ሃይማኖት እንደሚፈቅድልን ወይስ እንደእኛ ደስታ የሚለውን ሊመረመር ይገባል። እግሮቻችን ወደ ቤተ እግዚአብሔር ከሄዱ ስንት ጊዜ ሆናቸው? እጆቻችን ቅዱሳት መጻሕፍቱን የገለጡበት ጊዜስ? ዐይኖቻችን ከጉልላቱ ላይ መስቀሉን የተመለከትንበት ጊዜስ? አፋችን የእግዚአብሔርን ነገር የተናገርንበት ጊዜስ! ጆሯችን ቃለ እግዚአብሔር የሰማበት ጊዜስ? አንደባታችን (ጉሮሯችን) ቅዱስ ቁርባን የተቀበሉበት ጊዜስ? ሕዋሳቶቻችንን እንደተፈጠሩለት ዓላማ ያዋልንበት ጊዜ መቼ ነው?

‹‹ከክፉ መንገዳችሁ ተመለሱ›› (ኤር.፲፰፥፲፩)

ሥነ ምግባር ሰዎች በዕለት ተዕለት ኑሮችን ውስጥ የምናሳየው ጠባይ ወይም ድርጊት፣ አንድን ነገር ለመሥራትና ላለመሥራት የሚወስኑበት ኅሊናዊ ሚዛን ነው፡፡ በጎ ሥነ ምግባር ክፉ የሆኑ ነገሮችን አስወግዶ ደግ የሆኑትን መምረጥ መሥራት ሲሆን በተቃራኒው ክፉ ሥነ ምግባር ከበጎ ይልቅ ክፉ ነገሮችን መርጦ መሥራት ማለት ነው፡፡ ክፉ የሚለው ቃል የመልካም ነገር ተቃራኒ፣ የበጎ ነገር መጥፋት፣ ሐሰት፣ ኃጢአት፣ በሰው ልጅ ላይ የሚደርስ የሥጋና የነፍስ መከራ ተብሎ ሊተረጎም ይችላል፡፡ ልዑለ ባሕርይ እግዚአብሔር ለሰው ልጆች ክፉና በጎን መለየት እንዲችሉ አስቀድሞ በሕገ ልቡና ከዚያም በሕገ ኦሪት ከዚያም በሥጋ ተገልጦ የሰው ልጅ ሊኖር የሚገባውን ኑሮ ምሳሌ አርአያ ሆኖ አሳይቶናል፡፡

ቅዱስ ቶማስ ዘመርዓስ

ቶማስ ማለት የስሙ ትርጉም ፀሐይ ማለት ነው፡፡ በቶማስ  ስም የሚጠሩ በኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የሚታወቁ በርካታ ቅዱሳን አሉ፡፡ ከነዚህ መካከል ቅዱስ ቶማስ ዘመርዓስ ናቸው፡፡ ቅዱስ ቶማስ ዘመርዓስ ትሩፋትና ገድሉን ሰው ተናግሮ ሊፈጽመው አይችልም፤ እርሱ አስቀድሞ ከልጅነቱ ቅዱሳት መጻሕፍትን የተማረ፣ ገና በወጣትነቱ መንኖ  ገዳም የኖረ፣ በጾም፣ በጸሎት፣ በሰጊድ፣ ቀን እና ሌሊትም በመትጋት ለድኆችና ለምስኪኖችም በመራራት ተጠምዶ የኖረ ነበር፡፡ ቅዱስ ቶማስ ‹‹መርዓስ›› በምትባል አገር የወጣ የንጋት ኮከብ፣ ጻድቅ፣ ገዳማዊ፣ ጳጳስ፣ ሐዋርያ፣ ሰማዕትና ሊቅ ነው፡፡ የእርሱ ሕይወት ኦርቶዶክሳዊ የክርስትና ሕይወትና የጵጵስና የሹመት ሕይወት ምን እንደ ሆነ በትክክል የሚያሳይ ነው፡፡ መርዓስ በምትባል ሀገር ጳጳስ ሆኖ ተሹሞ በእረኝነት ያገለገል ዘንድ የክብር ባለቤት ጌታችን አምላካችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ መረጠው፤ መንጋውንም እንደ ሐዋርያት ጠበቀ፡፡  

የአቡነ ተክለ ሃይማኖት በዓለ ዕረፍት

ጻድቁ አቡነ ተክለ ሃይማኖት ሕይወታቸውን ሙሉ ለእግዚአብሔር በመስጠት፣ እንደ በሬ ተጠምደው፣ እንደ ገበሬ ታጥቀው ይህንን ዓለም ንቀው፣ በጾም በጸሎት ተወስነው በብሕትውና ከመኖራቸው ባሻገር እንደ ቅዱሳን ሐዋርያት ወንጌልን በመላው ኢትዮጵያ እየተዘዋወሩ የሰበኩ፤ በጌታችን አምላካችንና መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ስም ድውያነ ሥጋን በተአምራት፣ ድውያነ ነፍስን በትምህርት የፈወሱ ሐዋርያ ናቸው፡፡ ቅድስት ቤተ ክርስቲያችንም ነሐሴ ፳፬ ቀን የዕረፍታቸውን በዓል በትላቅ ደስታ ታከብራለች፡፡