ጾመ ሐዋርያት እና ጾመ ድኅነት

በዚህ ዓመት ጾመ ሐዋርያት ሰኔ ፩፤ ጾመ ድኅነት ደግሞ ሰኔ ፫ ቀን ይጀመራሉ፡፡ በመሆኑም የምንጠቀመው በራሳችን መልካም ተግባር፤ የምንወቀሰውም በራሳችን ኃጢአት መሆኑን ተረድተን ‹ይሄ የቄሶች፤ ይሄ የመነኰሳት ነው› የሚል ሰበብ ሳንፈጥር ሁላችንም በአንድነት ብንጾማቸው ከእግዚአብሔር ዘንድይቅርታ ጸጋና ምሕረትን እናገኛለንና ራሳችንን ለጾም እናዘጋጅ፡፡

የኢየሱስ ክርስቶስ ደም ከኀጢአታችን ሁሉ ያነጻናል፡፡ (፩ኛ ዮሐ.፩፥፯)

የሰው ልጅ ንስሓ ገብቶ ከኀጢአት ነጽቶ ቅዱስ ቊርባንን የሚቀበል ከሆነ ዳግም ሞት የለበትም፡፡ በፍጻሜ ዘመኑ ከዚህ ዓለም ተለይቶ ወደ ወዲያኛው ዓለም በሚሸጋገርበት ጊዜም ወደ ገነት እንጅ ወደ ሲኦል አይወርድም፡፡ ወደ ሲኦል ቢሄድም እንኳ ልትቀበለው አትችልም፤ ምክንያቱም በሕይወተ ሥጋ ሳለ በደመ ክርስቶስ ታትሟልና፡፡

‹‹እመን እንጂ አትፍራ›› (ማር. ፭፥፴፮)

በክርስቶስ ክርስቲያን ለተባልን ለእኛ ለኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ሃይማኖት ተከታዮች እምነት የድኅነታችን መሠረት ነው፤ በፈተናና መከራ ለተሞላው ክርስቲያናዊ ሕይወታችን ለጠላት ከመሸነፍም ሆነ በኃጢአት ከመውደቅ የሚያድነን እንዲሁም በተስፋ ነገን እንድንጠብቅ የሚረዳን እምነታችን ነው፡፡ ዘወትር በጸሎት አምላካችን ድኅነተ ሥጋን እና ድኅነተ ነፍስን ለምንማጸን እርሱ እግዚአብሔር ቸርነቱና ምሕረቱ የበዛ ነው፡፡

‹‹ትፈወሱም ዘንድ እያንዳንዱ ሰው ስለ ሌላው ይጸልይ፤ የጻድቅ ሰው ጸሎት በሥራዋ እጅግ ኃይል ታደርጋለች›› (ያዕ. ፭፥፲፮)

እዚህ ላይ ማስተዋል ያለብን አምላካችንን በሕይወት ዘመናቸው ሁሉ ሌት ከቀን ያለማቋረጥ በጸሎት፤ በጾም እና በስግደት ያገለገሉ ቅዱሳን አባቶቻችንን በማሰብ ለኃጢአተኞች ምሕረትን እንደሚያደርግ ነው፡፡ በተለይም ጻድቁ አባታችን አቡነ እስትንፋሰ ክርስቶስ ተጋድሏቸውን ሲፈጽሙ በተሰጣቸው ቃል ኪዳን መሠረት እኛን ከቸነፈር እንደሚጠብቁን በማሰብ ልንጽናና ይገባል፡፡ …..
እንዲሁም ሕፃኑ ቂርቆስ በሰማዕትነት ባረፈበት ዕለት ‹‹…ስምህ በተጠራበት፣ ቤተ መቅደስህ በታነጸበት ሥዕልህ ባለበት ቦታ ሁሉ የሕፃናት እልቂት፣ የከብት በሽታ፣ የእህል እጦት፣ ረኃብ፣ ቸነፈር አይደርስም›› የሚል ቃል ኪዳን ሰጥቶታል፡፡

‹‹እግዚአብሔር ይቅርታን ይረሳልን? በቁጣውስ ምሕረቱን ዘጋውን?›› (መዝ. ፸፮፥፱)

ብዙዎች በአሁኑ ሰዓት ስጋትና ጭንቀት ላይ ናቸው፤ ነቢየ እግዚአብሔር ዳዊት ‹‹እግዚአብሔር ይቅርታን ይረሳልን? በቁጣውስ ምሕረቱን ዘጋውን?›› ብሎ በጸሎት እንደጠየቀው አዛውንቶችም የዚህ መቅሰፍት ማብቂያ የሚቆምበትን ጊዜ በመመኘት አምላካቸው ስለምን ቸል እንዳለ ሲጠይቁ ይሰማሉ፤ ምሕረትንም እንዲያበዛልን አብዝተው ሲለምኑ ይደመጣሉ፡፡ (መዝ. ፸፮፥፱)

‹‹እምነትም ተስፋ ስለምናደርገው ነገር የሚያስረግጥ፥ የማናየውንም ነገር የሚያስረዳ ነው›› (ዕብ. ፲፩፥፩)

ማንኛውም የሕይወት ውጣ ውረድ ቢያጋጥመን በእምነት ከጸናን የማናልፈው ነገር የለም፡፡ የማንዘለው የችግር እና የመከራ ግንብ፣ የማንሻገረው ባሕር እና መሰናክል አይኖርም፡፡ ነቢየ እግዚአብሔር ቅዱስ ዳዊት በእምነት ከእግዚአብሔር ጋር ከኖርን የሚያስፈራን አንዳች ነገር አለመኖሩን ሲያስረዳ ‹‹በሞት ጥላ መካከል እንኳን ብሔድ፤ አንተ ከእኔ ጋር ነህና ክፉን አልፈራም፤ በትርህና ምርኩዝህ እነርሱ ያጽናኑኛል›› ብሏል፡፡ (መዝ. ፳፪፥፬)

‹‹ድኀነት››

የሰው ልጅ በኃጢአት ምክንያት ያጣውን የተፈጥሮ ጸጋ ክብር በአዲስ ተፈጥሮ እንደገና ለመታደል መብቃቱን ለመግለጽ የሚነገር ልዑል ቃል ‹‹ድኀነት›› ነው፡፡ ድኀነት የሚለው ቃል አዳም በክርስቶስ የታደለውን የሕይወተ ሥጋና ሕይወት ነፍስ፣ በረከተ ሥጋና በረከተ ነፍስ ጸጋ ወይም በሌላ አነጋገር የሞተ ሥጋና የሞተ ነፍስ ድቀት የደረሰበት አዳም በክርስቶስ ኢየሱስ ያገኘው ትንሣኤውና ሕይወት የሚገለጽበት ሕያው ቃል ነው፡፡

‹‹የሱራፌል አምሳላቸው ቅዱስ ያሬድ››

እግዚአብሔር አምላክን ‹‹ቅዱስ ቅዱስ ቅዱስ›› እያሉ በመንበሩ ፊት ቆመው እንደሚያመሰግኑ ሁሉ ኢትዮጵያዊ ማኅሌታይ ቅዱስ ያሬድ ‹‹ቅዱስ ቅዱስ ቅዱስ›› እያለ በመላእክት ቋንቋ ፈጣሪውን በማመስገኑ እና ዜማውን ከእነርሱ በመማሩ በመጽሐፈ ስንክሳር ‹‹አምሳሊሆሙ ለሱራፌል፤ የሱራፌል አምሳላቸው›› ተብሏል፡፡

“በመከራዬ ሳለሁ ወደ አምላኬ ወደ እግዚአብሔር ጮኽሁ” (ትንቢተ ዮናስ ፪፥፫)

በመጀመሪያ ራሳችን “በደለኛው እኔ ነኝ፤ ኃጢአተኛ ነኝ፤” ብለን አምነን መጸጸት አለብን፤ ጸጸትም ወደ ንስሓ ይመራናል፡፡ እግዚአብሔር ልብንና ኩላሊትን የሚመረምር አምላክ ነውና ውስጣችንን ከክፋት ሳናነጻ በሐሰተኛ አንደበት በንጸልይና ምሕረትን ብንለመን ልመናችንን አይቀበለንም፤ ሁሌም እርሱን በመፍራት መኖር እንዳለብን ቃሉ ይገልጻል፤ “ነገር ግን ቀኑን ሙሉ እግዚአብሔርን በመፍራት ኑር” (መጽሐፈ ምሳሌ ፳፫፥፲፯) እንደተባለው እግዚአብሔርን አምላክን በንጹሕ ልቡና ልንማጸን ይገባል፡፡

“የክርስቶስን ሕግ ፈጽሙ” (ገላ. ፮፥፪)

የክርስቶስ ሕግ ፍጻሜ ፍቅር ነው። ፍቅር አንድ ሰው ከሌላው ጋር በየዕለቱ የሚያደርገው ግንኙነት፣ በመተሳሰብ ላይ የተመሠረተ ልባዊ መዋደድና ጥልቅ መንፈሳዊ ጸጋ ነው። በሰዎች መካከል በሚኖረው መልካም ግንኙነት የተነሳ አንዱ ለሌላው የሚያደርገው መልካም ነገር ሁሉ ፍቅር ነው።