በፊትህ ናት
በኀምሳኛው ዕለት መንፈስ ቅዱስ ሲያድርባቸው
በ፸፪ የተለያየ ዓይነት ቋንቋቸው
ሲናገሩ ተገረሙ አሕዝቡ ሰምተው
በእግዚአብሔር ሥራ እጅግ ተደንቀው
የወንጌሉን ቃል ሲረዱ ተነክቶ ልባቸው
ሦስት ሺህ ነፍሳትም ተጠመቁ አምነው…
በኀምሳኛው ዕለት መንፈስ ቅዱስ ሲያድርባቸው
በ፸፪ የተለያየ ዓይነት ቋንቋቸው
ሲናገሩ ተገረሙ አሕዝቡ ሰምተው
በእግዚአብሔር ሥራ እጅግ ተደንቀው
የወንጌሉን ቃል ሲረዱ ተነክቶ ልባቸው
ሦስት ሺህ ነፍሳትም ተጠመቁ አምነው…
ከጸሐፊው ማስታወሻ…
አባቴ ሲጠራ ሲነሣ ሰማሁኝ
የአብራኩ ክፋይ የቀለሙ ልጅ ነኝ
አባቴን አታንሳው እኔ እበቃለሁኝ
አባትህ ተረት ነው ብለህ ለጠየከኝ…
ጨረቃ ደም ሆነች፤ ፀሐይም ጨለመ
ከዋክብት ረገፉ፤ ሐኪሙ ታመመ
ልዑል ተዋረደ፤ ጌታ ሎሌ ሆነ
ፈጣሪ ሠራው ፍጡሩ በየነ…
በአንዲት ፍሬ ቅጠል ሕይወትን አጥቼ
ርስቴን ተነጠኩ የሞት ሞትን ሙቼ
በግዞት ተነዳሁ በድቅድቅ ጨለማ
ወደ ፍዳ መንደር ወደ ሞት ከተማ…
