ፍቅር ኃያል!

በመዝሙርና ሥነ ጥበባት ክፍል

ጥቅምት ፳፮፤፳፻፲፮ ዓመተ ምሕረት

ፍቅር ኃያል ፍቅር ደጉ

ወልድን ሳበው ከጸባኦት ከማዕረጉ

ፍቅር ደጉ ወልድን ሊያነግሥ በመንበሩ

በአንድ ጥለት በየዘርፉ በአንድ ጸና ማኅበሩ

ቃልም ከብሮ የዘውድ አክሊል ተቀዳጅቶ

ከምድር ላይ ከፍ…ከፍ…ከፍ…ብሎ ታይቶ

ተሠየመ በመስቀል ላይ…የነገሥታት ንጉሥ አብርቶ

በዚያች ልዩ ዕለት…ቀን ቡሩክ ቀን ፈራጅ

በዓለ ሢመቱ ሲታወጅ

ኀዘኑም ደስታውም በረከተ

ፍቅር ኃያል ፍቅር ሞተ!