ሆሣዕና በአርያም

የሰላም ንጉሥ መድኃኔዓለም

ስለ ስምህ ተቀኝተናል ሆሣዕና በአርያም!

በመንግሥትህ አስበኝ!

በሚያስፈራ ግርማህ በምጽዓት ቀን ስትገለጥ

በፊትህ የሚቆም ጠፍቶ ዓለም ሁሉ ሲንቀጠቀጥ

መልካሙን ዘር ከክፉው አበጥረህ ስትለያቸው

በፍርሃት ያርዳል የጽድቅ ፍሬ ለሌላቸው

ለእኔም ጨንቆኛል ዳግም የምትመጣበት

በደሌ ተቆጥሮ በሥራዬ የምመዘንበት

መሠዊያው

በእስራኤል ምድር በሰማርያ ላይ አክዓብ ነገሠ

ጣዖትን አቆመ …መለከትን ነፋ …ለበኣል ደገሠ

የቤተ መቅደሱ መሠዊያው ፈረሰ

የእግዚአብሔር ካህናት ደማቸው ፈሰሰ

በዓይኖችህ ታየዋለህ

በሰማርያ ረኃብ በጸናበት ዘመን የሚቀመስም ጠፋ፤ ከረኃቡ ጽናት የተነሣ እናት ልጇን እስከ መብላት ደረሰች። በእዚያም ሀገር ኤልሳዕ የሚባል የእግዚአብሔር ሰው ነበረ። እንዲህም አለ፤ ነገ በዚህች ከተማ በአንድ ሰቅል አንድ መሥፈርያ መልካም ዱቄት በአንድ ሰቅል ሁለት መስፈርያ ገብስ ይሸመታል። ያኔ ንጉሡ በእግዚአብሔር ላይ ተገዳደረ፤ እንዴት ይቻላልም አለ። የእግዚአብሔር ሰው ኤልሳ እንዲህ አለው፤ “ታየዋለህ እንጅ አትቀምሰውም” ልብን የሚከፍል ንግግር! በረኃብ የቆየች ሀገር ደስ በምትሰኝበት ሰዓት የማይጨበጥ ሕልም ሲሆን ምንኛ ያሳዝናል?  የሶርያ ንጉሥ ሲመኘው የኖረውን ነገር በዓይኑ አየው ግን አልቀመሰውም።  (፪ኛነገ.፯፥፪)

መስቀሉን ስከተል

ሊሄድ በ’ኔ መንገድ

ሊከተለኝ ‘ሚወድ

ራሱን ለሚክድ

አይደንግጥ አይፍራ

አለሁ ከር’ሱ ጋራ

ልሂድ አደን!

ልቤ ተነሣስቶ ጽድቅህን ፍለጋ

ከማዳንህ ጋራ አንተኑ ሊጠጋ

ልሂድ ወደ ዱሩ ከአባቶች ማደሪያ

ከለምለሙ መስክህ ከጽድቅ መነኻርያ

ጨረቃ

እስኪ እንጀምር ከልደቷ

በፍጥረቱ በውልደቷ

ከቀን በዐራተኛ መገኘቷ

በረቡዕ በዐራተኛ

ከተራራ ከፍ ያለች ከፀሐይ መለስተኛ

ምሬሃለሁ በለኝ!

በቀን በሌሊት ለዓይን ጥቅሻ ሳያርፉ

ለምስጋና በትጋት ዘወትር በሚሰለፉ

ስለ መላእክቱ ተማጽኜሃለሁ

በለኝ ምሬሃለሁ

ዘይታቸው ሳይነጥፍ መብራቱን አብርተው ከጠበቁህ ጋራ

ነፍሴን አሰልፋት ከምርጦችህ ተራ

ስለመረጥካቸው ምሬሃለሁ በለኝ

ዳግም ስትመጣ በቀኝህ አቁመኝ!

ማርኩሽ በለኝ!

አንተን ይዛ በተሰደደችው

በርሃ አቋርጣ ግብጽ በገባችው

በድንግል እናትህ በአምስቱ ኀዘኗ

ማርኩሽ በለኝ ስለ ቃል ኪዳኗ!

ሰብእ

ለሰው ሰውነቱ
ከአፈር መስማማቱ
የሸክላ ብርታቱ
እሳት ነው ጉልበቱ
ውኃ ደም ግባቱ
ነበር መድኃኒቱ!