ምሬሃለሁ በለኝ!

በቀን በሌሊት ለዓይን ጥቅሻ ሳያርፉ

ለምስጋና በትጋት ዘወትር በሚሰለፉ

ስለ መላእክቱ ተማጽኜሃለሁ

በለኝ ምሬሃለሁ

ዘይታቸው ሳይነጥፍ መብራቱን አብርተው ከጠበቁህ ጋራ

ነፍሴን አሰልፋት ከምርጦችህ ተራ

ስለመረጥካቸው ምሬሃለሁ በለኝ

ዳግም ስትመጣ በቀኝህ አቁመኝ!

ማርኩሽ በለኝ!

አንተን ይዛ በተሰደደችው

በርሃ አቋርጣ ግብጽ በገባችው

በድንግል እናትህ በአምስቱ ኀዘኗ

ማርኩሽ በለኝ ስለ ቃል ኪዳኗ!

ሰብእ

ለሰው ሰውነቱ
ከአፈር መስማማቱ
የሸክላ ብርታቱ
እሳት ነው ጉልበቱ
ውኃ ደም ግባቱ
ነበር መድኃኒቱ!

አንተ ጽኑ አለት ነህ

በጽናትህም ላይ እሠራለሁ መቅደስ

እያለ ሲነግረው ጌታችን  ለጴጥሮስ

በምድርም ያሠርኸው በሰማይ ይታሠር

በሰማይ ይፈታ የፈታኸው በምድር

ብሎ ሾሞት ሳለ በክብር ላይ ክብር

መሳሳት አልቀረም አይ መሆን ፍጡር!

ግእዝ ዘኢትዮጵያ

እፎ ኃደርክሙ…

ተናገረው ይውጣ እንጂ አንደበትህ አይዘጋ
የአባቶችህ መገለጫ ዜማቸውን አትዘንጋ

አብረን እንዘምር!

ጌታ ተወለደ በትንሿ ግርግም፤

በከብቶቹ በረት ከድንግል ማርያም፡፡

እርሷም ታቀፈችው የተወደደ ልጇን፤

ሰማይና ምድር የማይወስነውን፡፡

ዕግትዋ ለጽዮን

እጅግ ያስጨንቃል የጠላት ሰበቃው ኵናቱ

እሥራኤላዊነት ካሕዛብ መለየቱ

በሺህ ቢደበደብ አይታክት እውነቱ

ኢሥራኤል ቢወረር ጽዮን አምባይቱ!

ቸሩ እረኛዬ

ሰላምን ስሻ በአንተ አምኜ
በጭንቅ በነበርኩበት እጅጉን አዝኜ
በዚህች በከንቱ ዓለም በጨለማ ሆኜ
ፈጥነህ ደረስክልኝ ሆነኸኝ አጽናኜ

ጽኑ ተስፋ

ተድላ እና ደስታ ከሞላባት ገነት
ሥርዓተ ጾም ነው የተተከለባት
ደግሞም በሌላ መልክ የሞት ሕግ አለባት
የሕጉን ጽንዐት አዳም ጠነቀቀ
ከእባብም ሽንገላ ራሱን ጠበቀ…

ስለጥቂቶች

የምጽአት ቀን መቃረብን ሥራችን ሲመሰክር

ክፉ ግብር ሚዛን  ደፍቶ በዓለም ግፍ ሲመነዘር

ኃጢአት የወለደችው የጥፋት ቀን እንዲያጥር

ጻድቃንን ባያስቀርልን ሁላችን በጠፋን ነበር

ሥጋን ለነፍስ አስገዝተው በበረኃ ጉያ የከተሙ

ቤተ ክርስቲያን ልጆች አሏት የሚማልዱ ለዓለሙ