ምሬሃለሁ በለኝ!
በቀን በሌሊት ለዓይን ጥቅሻ ሳያርፉ
ለምስጋና በትጋት ዘወትር በሚሰለፉ
ስለ መላእክቱ ተማጽኜሃለሁ
በለኝ ምሬሃለሁ
…
ዘይታቸው ሳይነጥፍ መብራቱን አብርተው ከጠበቁህ ጋራ
ነፍሴን አሰልፋት ከምርጦችህ ተራ
ስለመረጥካቸው ምሬሃለሁ በለኝ
ዳግም ስትመጣ በቀኝህ አቁመኝ!
በቀን በሌሊት ለዓይን ጥቅሻ ሳያርፉ
ለምስጋና በትጋት ዘወትር በሚሰለፉ
ስለ መላእክቱ ተማጽኜሃለሁ
በለኝ ምሬሃለሁ
…
ዘይታቸው ሳይነጥፍ መብራቱን አብርተው ከጠበቁህ ጋራ
ነፍሴን አሰልፋት ከምርጦችህ ተራ
ስለመረጥካቸው ምሬሃለሁ በለኝ
ዳግም ስትመጣ በቀኝህ አቁመኝ!
በጽናትህም ላይ እሠራለሁ መቅደስ
እያለ ሲነግረው ጌታችን ለጴጥሮስ
በምድርም ያሠርኸው በሰማይ ይታሠር
በሰማይ ይፈታ የፈታኸው በምድር
ብሎ ሾሞት ሳለ በክብር ላይ ክብር
መሳሳት አልቀረም አይ መሆን ፍጡር!
ተድላ እና ደስታ ከሞላባት ገነት
ሥርዓተ ጾም ነው የተተከለባት
ደግሞም በሌላ መልክ የሞት ሕግ አለባት
የሕጉን ጽንዐት አዳም ጠነቀቀ
ከእባብም ሽንገላ ራሱን ጠበቀ…
የምጽአት ቀን መቃረብን ሥራችን ሲመሰክር
ክፉ ግብር ሚዛን ደፍቶ በዓለም ግፍ ሲመነዘር
ኃጢአት የወለደችው የጥፋት ቀን እንዲያጥር
ጻድቃንን ባያስቀርልን ሁላችን በጠፋን ነበር
ሥጋን ለነፍስ አስገዝተው በበረኃ ጉያ የከተሙ
ቤተ ክርስቲያን ልጆች አሏት የሚማልዱ ለዓለሙ