ሐዊረ ሕይወት መንፈሣዊ ጉዞ ቁጥር 2

ሐዊረ ሕይወት ቁጥር 2 መንፈሣዊ ጉዞ

ሐዊረ ሕይወት መንፈሣዊ ጉዞ ቁጥር 2

   

“በእንተ ጦማረ ሐሰት”

ግንቦት 13፣ 2003 ዓ.ም

በሐሰት የተሠራጨውን ሰነድ በተመለከተ ከማኅበረ ቅዱሳን የተሰጠ መግለጫ

እምነትና ሥርዓቷ ጸንቶ የቆየውን ቅድስት ቤተ ክርስቲያን ሕልውናዋን ለማሳጣት እና ሐዋርያዊ ተልእኮዋን ለማደናቀፍ ቀን ከሌሊት የሚተጉ አካላት የጥፋት ሤራቸውን ከመጎንጎን እና የተቻላቸውን ሁሉ ከመፈጸም ወደ ኋላ ብለው አያውቁም፡፡ ቅድስት ቤተክርቲያን ሕግና ደንብ አውጥታ በመዋቅሯ አቅፋ እንዲያገለግል አደራና ሓላፊነት የሰጠችው ማኅበረ ቅዱሳንም የጥቃታቸው አንዱ አላማ ነው፡፡ የማኅበሩን ቀና አገልግሎት ለማስቆም ብዙ ጥረዋል፡፡
 
በእግዚአብሔር ፈቃድና ቸርነት የተመሠረተ እንደመሆኑ የቅድስት ቤተክርቲያንን መመሪያ ጠብቆ በአባቶች ምክርና ጸሎት እየታገዘ አገልገሎቱን ከመፈጸም ወደኋላ አይልም፡፡ እነዚህ የቅድስት ቤተክርስቲያንን ሐዋርያዊ አገልግሎት የሚፈታተኑ አካላት የማኅበረ ቅዱሳንን ስም በማጥፋት እንደደከሙት ሁሉ፤ ሰሞኑን የማኅበሩን ማኅተም በተጭበረበረ ሁኔታ / ፎርጅድ/ በመጠቀም፣ "የማኅበሩ የሃያ አምስት ዓመት እቅድ" ነው በማለት የሐሰት ሰነድ አዘጋጅተው በኢንተርኔት ለማሠራጨት እና ለተወሰኑ ብፁዓን አባቶች እንዲደርስ ለማድረግ ሞክረዋል፡፡ ማኅበረ ቅዱሳን አገልግሎቱ ሁሉ ግልጽ ነው፡፡ ባሳለፋቸው አሥራ ዘጠኝ የአገልግሎት ዓመታት እቅድና አፈጻጸሙ በየደረጃው ለሚገኙ የቤተክርስቲያን አካላት እና አባቶች እንዲሁም ለማኅበሩ ማእከላትና አባላት በየወቅቱ በሪፖርት የሚገለጽ ውይይት የሚደረግበት ሲሆን በዚሁ ሁኔታ ተግባራዊ የሚሆን ነው፡፡ ይህ የማኅበሩ አሠራር በተገቢው ሁኔታ ወደፊትም ይቀጥላል፡፡ ሰሞኑን የተሠራጨውን የሐሰት ጽሑፍ በተመለከተ የማኅበሩን መግለጫ እንደሚከተለው አቅርበነዋል፡፡ ሰሞኑን “ድንግል ማርያም” በተባለ የፌስ ቡክ አድራሻ(face book Account) “የማኅበረ ቅዱሳን የረዥም ጊዜ እቅድ” በሚል የተበተነ የሐሰት ጽሑፍ እንዲወጣ (Post) መደረጉ ታውቋል፡፡ ይህ ጽሑፍ በመጨረሻው ላይ የማኅበረ ቅዱሳን የሃያ አምስት ዓመት እቅድ እንደሆነ ይገልፃል፡፡ ለመሆኑ ይህ “ጦማረ ሐሰት” ምንጩ ከየት ነው? ጽሑፉ እንዳመለከተው በውኑ የማኅበረ ቅዱሳን እቅድ ነውን? ይዘቱና ዓላማውስ ምንድን ነው? ማኅበረ ቅዱሳንስ በዚህ ጽሑፍ ላይ ያለው አቋም ምንድን ነው?

ምንጩ ከየት ነው?
ጽሑፉ በራሱ ሥልጣን እየተጣጣረም ቢሆን ለመናገር የሚሞክረው "የማኅበረ ቅዱሳን ነኝ" እያለ ነው፡፡ ነገር ግን በመናገር እና በመሆን መካከል ያለውን ርቀት እንዳይፈራገጥ ባስገነዘው ጣእረ ሞት እንደያዘው የሚይዘውን የሚጨብጠውን ያጣ ወረቀት ነው፡፡ ለዚህም ጽሑፉ ሳያውቀው ምንጩን ሲናገር እናገኘዋለን፡፡ ይሁን እንጂ በመጀመሪያ ምንጩ ማኅበረ ቅዱሳን ሊሆን ይችላልን?

የሚለውን መመልከቱ አስፈላጊ ይሆናል፡፡ ማኅበረ ቅዱሳን ከተመሠረተበት ጊዜ ጀምሮ እቅድ እያቀደ የእግዚአብሔርን አጋዥነት እየለመነ አገልግሎትን ሲያከናውን ቆይቷል፡፡ እቅድ ማቀድ በማኅበሩ ዘንድ እንግዳ ነገር አይደለም፡፡ በጥቂቱ የሃያ ዓመት ልምድም ያለው ማኅበር ነው፡፡ አባላቱም ከመንፈሳዊው አገልግሎት ባሻገር በየተሠማሩበት የሙያ ዘርፍ እቅድ እያቀዱ ራሳቸውን በዘመናዊው አሠራር ያበለጸጉ ከመሆናቸው አንጻር መሠረታዊ የእቅድ አዘገጃጀት እውቀት ያላቸው መሆኑን ልንጠራጠር አንችልም፡፡ የተበተነው ጽሑፍ ያውም ሁለት ከወገብ በታች /ግማሽ ገጽ/ የሆኑ ወረቀቶች ላይ ማኅበሩ የሃያ አምስት ዓመት እቅድ ተብሎ ተዘርዝሯል፡፡ እንዲህ አይነቱ የሃያ አምስት ዓመት እቅድ ማቀድ   በአዘጋጆቹ ዘንድ የተለመደ ይሆናል እንጂ በማኅበረ ቅዱሳን ዘንድ የለም፡፡ የማኅበሩ የአራት ዓመት ስልታዊ እቅድ እንኳን የተዘጋጀው በሃምሳ አምስት ገፆች ነው፡፡

ስልታዊ እቅድ እንደመሆኑ መጠን በዘመናዊው አሠራር የራሱ ቅርጽ (format) አለው፡፡ ቢያንስ ቢያንስ መግቢያ፣ የማኅበሩን ማንነት፣ የማኅበሩ ዓላማ፣ ርእይ፣ ተልእኮ፣ እሴት፣ የባለድርሻ አካላት ትንተና፣ ውጫዊ አካባቢ ትንታኔ፣ እንዲሁም አስፈላጊነቱ ሌሎች ትንታኔዎች ምቹ እና ፈታኝ ሁኔታዎች፣ የምቹ እና ፈታኝ ሁኔታዎች ምዘና፣ ወሳኝ ጉዳዮች፣ ስልታዊ እቅድ ዓላማ፣ ግብና ስልት፣ ዝርዝር የአፈጻጸም መርሐ ግብር እንዲሁም የክትትልና የግምገማ ሥርአት ያለው ሊሆን ይገባል፡፡

በዚህ ቅርጽ መሠረት የማኅበረ ቅዱሳን ስልታዊ /ስትራቴጂክ/ እቅዱን አዘጋጅቶ  ለሚመለከታቸው የቤተ ክርስቲያን አካላት በማቅረብ በእቅዱ መሠረት አገልግሎቱን በመፈጸም ላይ ይገኛል፡፡ ይሁን እንጂ ይህ አሠራሩ ያልተመቻቸው አካላት የጐንዮሽ እቅድ በማቀድ የራሳቸውን የፈጠራ ሥራ አቅርበዋል፡፡ማኅበረ ቅዱሳንን ለመወንጀል ታስቦ የሐሰት ሰነድ (forged document) ተዘጋጅቶ የተበተነበትም ምክንያት ያንን እቅድ አባቶች እንደማያውቁት በማስመሰል ነው፡፡

የፖለቲካ አጠቃቀም
ማኅበሩ በመዋቅሩ ሥር ያሉትን አካላት በራሱ መጥራት የተሳነው አስመስለው ቀርጸውታል፡፡ ለማሳያ የሚሆነውም በዝርዝር እቅዱ ውስጥ በአንድ ላይ "በየንዑሳን ቅርንጫፍ በኩል" የሚል ሐረግ ይገኛል፡፡ ሲጀምር ማኅበሩ ቅርንጫፍ የሚባል ምንም ዓይነት መዋቅር የለውም፡፡  
 
ከዋናው ማእከል ቀጥሎ ያሉት ማእከላት ይባላሉ እንጂ ንዑሳን አይባሉም፡፡ ይህም አጠቃቀሙ ሌላ አካል መሆኑን ያሳያል፡፡ በአስገራሚ ሁኔታ የተበተነው ወረቀት አንድ ተማሪ ክፍል ውስጥ ገብቶ ሲማር ከሚይዘው ማስታወሻ እንኳ ያነሰ፤ እቅድ መባል ካለበት እንኳ የጨነገፈ እቅድ ነው፡፡ ማኅበረ ቅዱሳን ሊያወጣው አይችልም፡፡ በዚህ መስፈርት እንኳን ቢታይ እቅዱ በምንም መለኪያ የማኅበረ ቅዱሳን አለመሆኑን ያረጋግጣል፡፡

ማኅበረ ቅዱሳን ራሱን ሲጠራ ”ማህበረ ቅዱሳን” ብሎ አያውቅም። "እቅድ" የሚለውን ቃል አቅድ የሚለውን ተክቶ ለጥቅም እንዲውል አድርጐም አያውቅም፡፡ እነዚህን የተጠቀመው ጽሑፍ ራሱን እርቃኑን አቁሞ የማኅበረ ቅዱሳን አለመ ሆኑን የገለጠበት ዘርፍ ነው፡፡ ወረቀቱ ስለ እቅድ የሚናገር ከሆነ የተግባራዊነት ዘመኑ ከመቼ እስከ መቼ እንደሆነ እንኳ አለመገለጹ ድንገቴ እንደ ወራጅ ውኃ የፈሰሰ የጥቂቶች አሳብ እንጂ እቅድ አለመሆኑን ያሳብቅበታል፡፡ የስሕተት ሙሻዙር የጠመዘዛቸው አዘጋጆች እንደመሰላቸው እነርሱ ያስቀመጧቸውን በወንጀል ደረጃ የሚፈረጁ አደገኛ አሳቦች በማኅተም አትሞ በቲተር እና በፊርማ አስደግፎ ራሱን ለአደጋ አጋልጦ የሚያስቀምጥ ተቋም በሃያ አንደኛው ክፍለ ዘመን ይገኛል ብሎ ማሰብ ቂልነት ነው፡፡

በተሠራጨው እቅድ ላይ የተቀመጡት አሳቦች አሉታዊ እና አፍራሽ አስተሳሰቦች እንደመሆናቸው መጠን ማኅበሩ የቱንም ያክል ክፉ ነው ተብሎ ቢታሰብ እንኳ እንዲህ ያለ እቅድ በዚህ መልክ አዘጋጅቶ እና አንድ ቦታ አጠራቅሞ ይገኛል ተብሎ አይታሰብም፡፡ ያንን ያክል ክፋት ማርገዝ የቻለ እኩይ ሕሊና ቢኖር እንኳ አካሔዱን እና አቀማመጡን አይጠበብበትም ነበር የሚለው ለአንባቢ የሚተው ውሳኔ ይሆናል፡፡ እነዚህን አካሔዶች ጠቅልለን ስንመለከታቸው ምንጩ ለጊዜው የማኅበረ ቅዱሳንን በመጨረሻም የቅድስት ኦርቶዶክሳዊት ተዋሕዶ ቤተክርስቲያንን ጥፋት ሌት ተቀን ከሚለማመኑ አካላት የተቀዳ ለመሆኑ ከቶውኑ ማን ይመራመራል? መጽሐፍ “በክፋታቸው እየባሱ ይሔዳሉ” እንዳለው የማኅበረ ቅዱሳን መኖር የእግር እሳት ስለሆነባቸው በምን መንገገድ ስሙን ቢያጠፉ ተቀባይነት ሊያገኙ እንደሚችሉ ሁልጊዜ ወጥመድ ያጠምዳሉ፡፡ እስካሁን ድረስ የእግዚአብሔር ቸርነት ከልክሏቸው አልተሳካላቸውም እንጂ የወገባቸው የሐሰት ዝናር ሲያልቅባቸው በማኅበሩ ወንበር ተቀምጠው የሚናገሩ በማስመሰል ማኅበሩ ቤተ ክርስቲያንን ለማጥፋት ተልእኮ እንዳለው አድርገው ሊያቅዱለት ፈለጉ፡፡ ማኅበረ ቅዱሳን ካባ ለብሰው ያቀዱለት እቅድ ግን ከተለመደው ክሳቸው የወጣ አለመሆኑ ነው፡፡

እስካሁን ድረስ ማኅበሩን ለምን ትቃወማላችሁ ሲባሉ ይሰጡት የነበረውን መልስ እቅድ ነው ብለው አቀረቡት እንጂ ምንም አዲስ ነገር አላመጡም፡፡ ስለሆነም በዚህ በጻፉት እቅዳቸው ምክንያት ማንም ሊደነግጥላቸው አይችልም፡፡ በተቻላቸው መጠን የመጨረሻዋን ጥይት ለመተኮስ ሲጥሩ መልሶ ራሳቸውን ወጋቸው፡፡ በተጉበትም መጠን በመጐዳታቸው አሟሟታቸውን ለማሳመር የሐሰት እና የጥፋት እቅድ ለማኅበሩ አወጡለት፡፡ የሚጠባበቁት ውጤት በእነዚያ ወንጀሎች ምክንያት ያቀዱለት አካል እለቱኑ ታንቆ እለቱኑ ሲሞት ለማየት በጉጉት ኮርቻ ላይ ተቀመጡ፤ የፈለጉት ማኅበሩ እነርሱ ጐን ቆሞ ቤተክርስቲያንን አንዲያጠፋላቸው ነበር፡፡

ግን ምን ያደርጋል? እነርሱም ታወቁ ሕልማቸውም መከነ፡፡ ራሱን በራሱ ሲቃረን አንድ  ተቋም ራሱን ሲገልጽ ‘እኛ” በሚል ባለቤት ሊናገር እንደ ሚችል የተረዳ ነገር ነው፡፡ በጽሑፉ ላይ ግን አባቶችን አባላት በማድረግና ”ስብሰባቸው ላይ” የሚል አባባል ተጠቅመዋል፡፡ ስለራሱ እቅድ የሚናገር ሰው ”በስብሰባችን ላይ” ይላል እንጂ ”ስብሰባቸው ላይ” እንዴት ሊል ይችላል? በተጨማሪም ”በራሱ ጠቅላላ ጉባኤ መምራት” በማለት ማኅበሩ ራሱን ”እርሱ” እያለ እንዲጠራ አድርገው ጽፈዋል፡፡ እንዲሁም ”ካህናቱን ለድርጅቱ ሠራተኞች አድርጐ መቅጠር” በሚለው እቅዳቸው ላይ ”እርሱ” ብሎ ራሱን እንዲጠራ አድርገውታል፡፡

ከእነዚህ አገላለጾች የምንረዳው የሆነ አካል ራሱን አስገድዶ የማኅበሩ አካል አድርጐ በመቁጠር ስለማኅበሩ ሆኖ እንዲጽፍ እንደተጨነቀ ያሳያል፡፡ ታዲያ ምን ያደርጋል አልተቻለውም፡፡ ራሱን ጠፍሮ በማሠር ስለማኅበሩ እንዲናገር አሰቃየው እንጂ ስለሌላ ማኅበር እንደሚናገር ተገልጦበታል፡፡ ጸሐፊው ያለ እርሻው የበቀለ ከሌላ ዘር የመጣ ነውና የራሴ ነው ያለውን ማኅበር ”እነርሱ” ”እርሱ” እና ”እኛ” እያለ ጠራው፡፡ ያልሠለጠነ ውሸታም በመሆኑ እንዲጽፍላቸው የቀጠሩትን ሰዎች አጋለጣቸው፡፡ ከእግዚአብሔር ዘንድ ወዴት መሸሸግ ይቻላል? የጨለማው መጋረጃ ተቀደደባቸው፣ ከእነ ተንኮላቸው እጅ ከፈንጅ ተያዙ፡፡ ወዲህና ወዲያ እንዳይሉ በራሳቸው ገመድ ተጠፍንገው ታሠሩ፡፡ እግዚአብሔር ይፍታችሁ ከማለት ውጭ ምን እንላለን?

ማኅበሩ ማኅበሩን ሲቃወም በዕቅዳቸው ውስጥ ማኅበረ ቅዱሳን የሚያሳትማቸውን ኅትመቶች ያለ ኤዲቶሪያል ቦርድ ኅትመት አከናውኖ ማሠራጨት የሚል የተጠላለፈ አሳብ አስቀምጧል፡፡ በመሠረቱ ማኅበረ ቅዱሳን በመዋቅሩ እንዳመለከተው ማንኛውንም ኅትመት ኤዲቶሪያል ቦርዱ ዓይቶት ሲፈቅደው ይታተማል፡፡ ታዲያ እንዴት አንድ ማኅበር የራሱን መዋቅር የጣሰ ለመሥራት ያቅዳል፡፡ አስፈላጊ ሆኖ ካገኘው ቦርዱን ማፍረስ ሲችል እንዴት ስለመጣስ ያስባል። እንዲህ ያለ ዕቅድ ታይቶም ተሰምቶም አያውቅምና ዕቅድ አውጪዎቹ በጣም የተራቀቁ መሆን አለባቸው፡፡ ዕቅዳቸውን ለራሳቸው ጥብቅና ሲያቆሙት ቅድስቲቱን እምነት ለመበረዝ የተነሡ የተሐድሶ ኦርቶዶክስ ዓላማ አራማጆች ስውር ተልኮአቸው በአሁኑ ወቅት ስለተነቃባቸው ከገቡበት አዙሪት ለመውጣት ሲፍጨረጨሩ ይታያሉ፡፡

ከዚህም መንገድ አንዱ ተሐድሶ የሚባል የለም የሚል መፈክራቸውን ማስተጋባት ነው፡፡ ዕቅድ ተብየውም ይህንኑ የተከተለ ሳያውቀው በስውር ዓላማቸው የተቃኘ የተነረተ የበሽታ ሆድ ሆኖባቸዋል፡፡ ስለሆነም ከዕቅዱ መካከል በአንዱ ላይ ታላላቅ የቤተክርስቲያን መሪዎችና ተሐድሶዎች /ፖለቲከኞች/ ናቸው በማለት ከምዕመኑ ሰላማዊ ቅብብል እንዳይኖራቸው የሚል ይገኛል /ቃላቱ እነርሱ እንዳስቀመጧቸው የተቀመጡ ናቸው/። በዚህ ዕቅድ ላይ ሁለት ዋና ዋና ነጥቦችን ማስተዋል እንችላለን፡፡አንደኛው ተሐድሶን ፖለቲከኛነት ጋር ለመቀላቀል መታሰቡ ሲሆን ሁለተኛው ግን ታላላቅ የቤተክርስቲያን መሪዎች ያሏቸውን የሚመለከት ነው፡፡ ተሐድሶ ማለት የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲየንን ሙሉ በሙሉ ወደ ፕሮቴስታንት ጐራ ለመክተት አቅዶ የሚሠራ ሲሆን ፖለቲካኛ ደግሞ ሌላ ለዕቅድ አዘጋጆች ግን ተሐድሶና ፖለቲካ ተቀላቅሎባቸዋል፡፡ እውን  ተቀላቅሎባቸው ይሆንን? መልሱ ለአንባቢው የሚተው ነው፡፡ በሌላ በኩል ደግሞ ታላላቅ የቤተክርስቲያኗ መሪዎችን ማኅበረ ቅዱሳን ስማቸውን እንደሚያጠፋ ያመላክታል፡፡ ታላላቆችማ ታላላቆች ናቸው፡፡እነርሱን የሚቃወም ማንነቱ ግልጽ ነው፡፡ ስም ማጥፋትም ወንጀል ነው፡፡ ማኅበረ ቅዱሳን ግን ተሐድሶ የሆኑትን ተሐድሶ ናችሁ ከማለት አስያፈገፍግም፡፡ ይህንን ሲያደርግ በማስረጃ እንጂ በተራ አሉቧልታ አይደለም፡፡ ነገር ግን ታላላቆችን አባቶች የሚነኩትን ማኅበሩም ዝም  አይላቸውም ተልኳቸው ይታወቃልና፡፡ ይሁን እንጂ ሊያስተላልፉ የፈለጉት ተሐድሶ የለም የሚለውን የዘወትር የጨለማ መጋረጃቸውን ለመሆኑ ማን ሁለት ጊዜ ያስባል? ድንጋይ ይቧጥጣሉ እንጂ መጋለጣቸው አይቀርም፡፡ ይህ ሁሉ የሐሰት ደበሎ ይገለጣል፡

የጽንሰ ሐሳብ ችግር

ከዝርዝር ዕቅዳቸው አንዱ ባልተጠኑ ትምህርቶች የቤተርክስቲያኗን ምዕመናን ደጋፊ ማድረግ ይላል። አንድ ጤናማና የሚያስብ አእምሮ ያለው ሰው ይህንን አባባል እንዴት ይረዳዋል? ብሎ መገመት እጅግ ቀላል ይሆናል፡፡ ዕቅድ እያቀደ ያለ አንድ አካል እንዴት ባልተጠና ትምህርት ሌላውን ሊያሳምን ይችላል? ዕቅዱን ያቀዱት ሰዎች የሰለቻቸው ይመስላል፡፡ ማኅበረ ቅዱሳን የግቢ ጉባኤያት /የከፍተኛ ትምህርት ተቋማትን ተማሪዎችን/ የሚያስተምረው በተጠና ሥርዐተ ትምህርት መሆኑን ያወቁ እንዴት ይህን ሊሉ ቻሉ? በርግጥም ደክሟቸው መሆን አለበት፡፡

የጽሑፉ ዓላማ

 ማኅበረ ቅዱሳን ከተለያዩ የቤተ ክርስቲያን የቁርጥ ቀን ማኅበራትና ልጆች ጋር በመቀናጀት በአሁኑ ሰዓት ፀረ ተሐድሶ እንቅስቃሴ እያደረገ ይገኛል፡፡ በዚህም ምክንያት ማዕበሉ እያንጓለለ የለያቸው ያሉ የተደራጁ  የሃይማኖት ጠላቶች ማምለጫ እስኪያጡ ድረስ አጣብቂኝ ውስጥ ገብተዋል፡፡ የተዋሕዶ ምዕመናንን እየሰለቿቸው መጥተዋል፡፡ በመሸማቀቅ በቁማቸው አልቀዋል፡፡ ከመጠን በላይ በመደንገጣቸው ምክንያት ሳያስቡት የመጣባቸውን እውነት ለመጋፈጥ የሚያስችል መንፈሳዊ ተክለ ሰውነት አጥተዋል፡፡  ስለሆነም አቋራጭ የመሰላቸው የጨነገፈ ስልት ነድፈዋል፡፡ በዋነኛነትም የሞት ሽረት ትግል ለማድረግ አስበዋል፡፡

በዚህም መንገዳቸው አንዱ የማኅበሩን ስም በድብቅ ሆኖ ማጥፋት ነው፡፡ እውነተኞች ሰዎች ከሆኑ ማንነታቸውን ገልጠው ፊት ለፊት በያዙት መረጃ በታገሉ ነበር፡፡ ለዚህ ያልታደሉ የመልካም ዘር ፀሮች በመሆናቸው መደበቁን መርጠዋል፡፡ ተደብቆ ውጭ ማኅበረ ቅዱሳን ሊያስበው ከቶውኑ የማይፈልገውን ያስቡለታል፡ ፡ “አዛኝ ቅቤ አንጓች” እንደሚባለው ሆኖባቸው በዚህ ስልት ማኅበሩን ለማጥቃት ሞክረዋል ራሳቸው ጽፈው ሊሰሙን ይችላሉ ብለው ለሚያስቧቸው አካላት ጽሑፉን ለመበተን ሞክረዋል፤ ይህንን ማድረጋቸውም አንድም አባቶችን ንቀዋቸዋል አለበለዚያም ተዳፍረዋል፡፡

ይህንን ከደረጃ ወጥቶ ጊዜ ወስዶ የተንኮታኮተ ጽሑፍ ዕቅድ ብለው ይዘው መዞራቸው በትክክል ማንነታቸውን ይገልጥባቸዋል፡፡ በየትኛውም መመዘኛ ማኅበረ ቅዱሳንን የማይመስል ወዘና የሌለው ወረቀት ብቅ ማድረግ ማንነታቸውን ገልጠዋል፡፡ በዝምታ ሊታለፉ አይገባቸውም፡፡

ማጠቃለያ
ይህንን ጽሑፍ ያሰራጩት አካለት እነማን ሊሆኑ እንደሚችሉ ማንም ሰው መገመት ይችላል፡፡ ከመገመትም አልፎ አገኘሁ ብሎ ማኅበሩን ለማጥላላት የሚጠቀምበት ሁሉ እንዳለ ይታወቃል፡፡ ተቀባዮችም የሰጪዎችን ማንነት ያውቃሉ፡፡ እንዲያውም ከማብራሪያ ጋር እንደተቀበሉ ይታመናል ፡፡

ስለሆነም፡-

1. ይህ የሐሰት ጽሑፍ የደረሳቸው አካላት ሰዎችን በማጋለጥ ሊተባበሩ ይገባል፤
2. ማኅበሩ እነዚህን አካላት በሕግ መጠየቅ ይፈልጋል፡፡ ስለሆነም ቅዱስ ሲኖዶስ የእነዚህን ሰዎች ማንነት አጣርቶ ፍትሐዊ ውሳኔ እንዲሰጥን እንፈልጋለን፤

3. ይህ ጽሑፍ የደረሳቸሁ ምዕመናን በሐሰት ሥራ እንዳትታለሉ እናሳስባለን። አስፈላጊ ሆኖ ካገኙትም ወደ ማኅበሩ ጽ/ቤት በመምጣት ተገቢውን ውይይት ማድረግ እንደሚችሉ እንጠቁማለን።

የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዐተ ጉባኤ ዛሬ ተጀመረ፡፡

ግንቦት 10፣ 2003ዓ.ም


በርክበ ካህናት የሚደረገው የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዐተ ጉባኤ ዛሬ ተጀመረ። ጉባኤውን ተከትሎ የተለያዩ እንቅስቃሴዎች እየተደረጉ ነው፡፡

 
ወደ 1000 የሚጠጉ የሐዋሳ ከተማ ምዕመናን አዲስ የተመደቡትን የሀገረ ስብከቱ ሥራ አስኪያጅ ሊቀ ካህናት ጌታቸው ዶኒን ሹመት በመቃወም በሀገረ ስብከታቸው የተፈጠሩ ችግሮች የመጨረሻ እልባት እንዲሰጥበት የተለያዩ መፈክሮችን በመያዝ በመንበረ ፓትርያርክ ቅድስተ ቅድሳን ማረያም ገዳም በመገኘት አቤቱታቸውን አቅርበዋል፡፡  ከቅዱስ ሲኖዶስ መክፈቻ ጸሎት በኋላ ለቅዱስነታቸው እና ለብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳት ጥያቄያቸውን ያቀረቡት ምዕመናኑ «በምልዐተ ጉባኤው አጀንዳ ተደርጎ ሊያዝ እንደሚችል ቃል ተገብቶልናል» ሲሉ በቅድስት ማርያም ቤተ ክርስቲያን ለተሰበሰበው ምእመን በተወካያቸው አማካይነት ገልጸዋል፡፡

ከሓዋሳ የመጡ ምእመናን አስፈላጊውን የሕግ አግባብነት ተከትለው ቢመጡም ባልታወቀ ምክንያት ዱከም ላይ ታግተው የቀሩ ምእመናን እንዳሉ አስተባባሪዎች ገልጸዋል፡፡

በሰ/ት/ቤቶች ማ/መምሪያ ማኅበረ ቅዱሳንም የቅዱስ ሲኖዶስ ጉባኤ በአጀንዳ ሊያያቸው ይገባል ያላቸውን ጉዳዮች በቀን 9/9/03 ዓ.ም በቁጥር ማ.ቅ.ሥ.እ.መ/17/02/ለ/03 በጻፈው ደብዳቤ አቅርቧል፡፡ ለቅዱስ ሲኖዶስ ጽሕፈት ቤት እና በግለባጭ ለሁሉም ሊቃነ ጳጳሳት በላከው ደብዳቤ በማኅበሩ ላለፉት 19 ዓመታት የተሠሩ ሥራዎች እንዳሉ ሆነው በአሁኑ ወቅት ግን ለቤተ ክርሰቲያን እድገትና መልካም አሠራር እንቅፋት የሆኑ ችግሮች  መኖራቸውን በአጽንኦት ይገልጻል፡፡

ወቅታዊውን የተሐድሶ መናፍቃን ዘመቻ፣ ቅዱስ ሲኖዶስ ከዚህ በፊት ያሣለፋቸውን ውሳኔዎች ተፈጻሚነትን፣ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን ትውልድን የማፍራት ጉዳይ ይኸውም የሕፃናትና የወጣቶች ሰ/ት/ቤቶች ሥርዓተ ትምህርትና የማደራጃ መምሪያ ኃላፊዎችን ችላ ባይነት፣ የማኅበሩን ስም ለማጥፋት እየተንቀሳቀሱ ስላሉ አጽራረ ቤተ ክርስቲያን እንዲሁም ለቅዱስ ሲኖዶስ አባልነትና የሚቀርቡና የሚሾሙ ኤጲስ ቆጶሳትን ጉዳይ ይኸውም ወቅቱ የተሐድሶ መናፍቃን በቤተ ክርስቲያኗ መዋቅርና የሓላፊነት ቦታ ለመግባት ከፍተኛ ርብርብ የሚያደርጉበት ስለሆነ ቅዱስ ሲኖዶስ ለዚህ ጉዳይ ጥንቃቄ እንዲያደርግ የሚያመለክቱ አጀንዳዎች በአጀንዳነት ተይዘው ውሳኔ ሊሰጥባቸው ይገባል በማለት እንደልጅነታችን ሀሳባችንን እናቀርባለን ሲል ለቅዱስ ሲኖዶስ ጽ/ቤት የተጻፈው ደብዳቤ ያሳስባል።


 


በተያያዘም እነዚህንና ከወቅቱ ሁኔታ ጋር የቀረቡ ሌሎች ተያያዥ ጉዳዮችን በተመለከተ በወቅታዊው የስምዐ ጽድቅ ልዩ እትም ሠፋ ያሉ ዘገባዎች ቀርበዋል።

ቅዱስ ሲኖዶስንና መንፈሳዊና አስተዳደራዊ ልዕልናውን፣ የወቅታዊውን የተሐድሶ መናፍቃን እንቅስቃሴ፣ እንዲሁም አጽራረ ቤተ ክርስቲያን፣ በማኅበረ ቅዱሳን የውሸት /forged/ ማኅተም «የማኅበረ ቅዱሳን የረጅም ጊዜ ዕቅድ» በሚል ያዘጋጁትን እና በክስ መልክ ለፓትርያኩ ያቀረቡትን የሐሰት ጦማርና ሌሎችንም ወቅታዊ ጉዳዮች በተመለከተ ሰፋ ያለ ዘገባ በመያዝ ወጥታለች፤ የስምዐ ጽድቅ ልዩ እትም።

ቤተ ክርስቲያን የማትነጥፍ መንፈሳዊት ጥገት ሆና ከምታፈሰው መንፈሳዊ ሐሊብ /ወተት/ ምእመኖቿ እንዲጠቀሙ የቅዱስ ሲኖዶስ መንፈሳዊና አስተዳደራዊ ልዕልና መከበር ወሳኝ ነው።

ቤተ ክርስቲያንም የቅድስና ዘውዷንና የክብር አክሊሏን ከራሷ ሳታወርድ ልዕልናዋ እንዳለ ሁሉ የቅዱስ ሲኖዶስ ውሳኔዎች መከበር አለባቸው ስትል ስምዐ ጽድቅ ጋዜጣ በልዩ እትሟ አስነብባለች።


የማኅበሩ ሰብሳቢ ቀሲስ ዶ/ር ሙሉጌታ ሥዩም

ቅዱስ ሲኖዶስ ጠንካራ ውሳኔ ያሳልፋል ተብሎ ይጠበቃል

ግንቦት 10/2003 ዓ.ም.

በቤተክርስቲያኒቱ አጠቃላይ ሁኔታ ላይ የሚመክረው የቅዱስ ሲኖዶስ ጉባኤ በቀጣይ በቤተክርስቲያኒቱ አገልግሎት መጠናከርና በገጠሟት ችግሮች ላይ መፍትሔን የሚሰጥ ጠንካራ ውሳኔ ያሳልፋል ብሎ እንደሚያምን ማኅበረ ቅዱሳን አስታወቀ፡፡ የማኅበሩ ሰብሳቢ ቀሲስ ዶ/ር ሙሉጌታ ሥዩም እንዳስታወቁት፤ ዘንድሮ ከግንቦት 10 ቀን ጀምሮ የሚካሔደው ዓመታዊ መደበኛ የቅዱስ ሲኖዶስ ጉባኤ በእግዚአብሔር አጋዥነት እና በመንፈስ ቅዱስ የሚመራ በመሆኑ ጠቃሚ ሀሳቦች የሚነሡበት፤ ለቅድስትቤተክርስቲያን የሚበጁ ጠንካራ ውሳኔዎች የሚተላለፉበት እንደሚሆን ማኅበረ ቅዱሳን በፅኑ ያምናል፡፡
 
«በቅድስት ቤተክርስቲያኒቱ ውስጥ ቅዱስ ሲኖዶስ ያለው ቦታና ልዕልና ከፍተኛ ነው፤ ስለዚህም የቤተክርስቲያኒቱን ዶግማና ቀኖና ከማስጠበቅ፣ በየጊዜው የሚያጋጥሟትን ችግሮችና ፈተናዎች ላይየማኅበሩ ሰብሳቢ ቀሲስ ዶ/ር ሙሉጌታ ሥዩም ውሳኔዎችን ከማሳለፍ አንፃር የጉባኤው ውጤት በጉጉት ይጠበቃል» ያሉት ሰብሳቢው፤ ይህ ይሆን ዘንድ ማኅበሩ ምኞቱን ይገልጣል ብለዋል፡፡ በአሁኑ ወቅት የቤተክርስቲያኒቱን ሥርዓት፣ዶግማ እና ቀኖናዋን እንዲሁም ማንነቷን የሚሸረሽር ትልቅ የተሐድሶ እንቅስቃሴ መኖሩን የጠቆሙት ቀሲስ ዶ/ር ሙሉጌታ፤ በዚህ ላይ የሲኖዶሱ ውሳኔ ወቅታዊነት ያለው ነው የሚል እምነት እንዳላቸው ተናግረዋል፡፡
በፀረ ቤተክርስቲያን ኃይሎች መንፈሳዊ ተቋማትና ገዳማትን የመበረዝ፣ ውስጧንም የመቀየርና ማንነቷን የማጥፋት ሰፊ ሥራ እየሠሩ መሆኑን ጠቅሰው በእነዚህና በመሳሰሉት የቤተ ክርስቲያኒቱ እንቅፋቶች ላይ ጉባኤው መክሮ የሚያሳልፈው ውሳኔ ጠቃሚ እና ተስፋ ሰጪ  እንደሚሆንም እምነታቸውን ገልጠዋል፡፡ ውሳኔውን ተከትሎ ለማስፈፀሚያነት የሚወጡ መመሪያዎችንና ደንቦችን በአግባቡ የመከታተልና የመቆጣር ሓላፊነትም የቅዱስ ሲኖዶስ መሆኑን ጠቅሰው፤ አፈጻጸሙ ላይ ማኅበሩ የቤተክርስቲያኒቱ አካል እንደመሆኑ መጠን የበኩሉን አስተዋጽኦ ያደርጋል ብለዋል፡፡

እንደ ቀሲስ ዶ/ር ሙሉጌታ ሥዩም ገለጻ፤ የቅዱስ ሲኖዶስ ጉባኤ ውሳኔዎችን እንደ ቅድስት ቤተክርስቲያን አካልነቱ ከመፈጸም እና ከማስፈጸም በተጨማሪ ማኅበሩ ባለው የኅትመት ውጤቶች ማለትም በስምዐ ጽድቅ ጋዜጣ፣ በሐመር መጽሔት እና በሌሎች የኤሌክትሮኒክ ሚዲያ ለምእመናን የማድረስ ሓላፊነቱን ይወጣል፡፡ ማኅበሩ በቅዱስ ሲኖዶስ መመሪያና ደንብ መሠረት የተዋቀረ በመሆኑ ለቤተክርስቲያኒቱ ያለውን አጋዥነት አሁንም በተግባር ማረጋገጡን እንደሚቀጥል የጠቀሱት ቀሲስ ዶ/ር ሙሉጌታ በአባቶች ምክር፣ ምርቃትና ቡራኬ የሚመራ መሆኑ አገልግሎቱን እንዳገዘው ተናግረዋል፡፡ የቅዱስ ሲኖዶስ ውሳኔዎችን የማኅበሩ አባላትም ሆኑ ምእመናን አክብረው ተግባራዊ እንዲያደርጉም ጥሪ አቅርበዋል፡፡

«እርሳቸው የያዙት መንገድ ሙሉ በሙሉ የኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያንን ማዳከም ነው፡፡ » ማኅበረ ቅዱሳን

 ግንቦት 9/2003ዓ.ም
ማኅበረ ቅዱሳን ተመሥርቶ በሰ/ት/ቤቶች ማደራጃ መምሪያ ሥር አገልግሎት ከጀመረ አንስቶ ወደ 10 የሚጠጉ የመምሪያ ኃላፊዎች ተፈራርቅዋል፡፡ እስከ አሁን ምንም ያልተባለለት የማኅበሩና ማደራጃ መምሪያው ግንኙነት፣ የአሁኑ የመምሪያው ኃላፊ አባ ሠረቀብርሃን ከመጡ ከ6 ዓመት በፊት ጀምሮ፣ ችግሮች እየገጠሙት እንደሆነ ይነገራል፡፡ ማኅበሩም አሁን ያሉት የመምሪያው ኃላፊ አላሠራኝ አሉ በማለት ይወቅሳል፡፡ ይህንን በተመለከተ ከማኅበሩ ዋና ጸሐፊ ዲ/ን ሙሉጌታ ኃ/ማርያም ጋር ቆይታ አድርገናል፡፡ መልካም ንባብ፡፡
 
    ቅዱስ ሲኖዶስ ባጸደቀውና በተሻሻለው መተዳደሪያ ደንብ መሠረት የሰንበት ትምህርት ቤቶች ማደራጃ መምሪያና የማኅበረ ቅዱሳን ግንኙነት ምን መምሰል አለበት?

የማኅበሩ መተዳደሪያ ደንብ በ1994 ዓ.ም በቅዱስ ሲኖዶስ ምልዐተ ጉባኤ በጸደቀው መሠረት ማኅበሩና ማደራጃ መምሪያው የሚያከናውኗቸው ተግባራት በግልጽ ተቀምጠዋል፡፡ የማኅበሩ ተግባርና ኃላፊነት፥ ማኅበሩ ለማደራጃ መምሪያው ማድረግ የሚገባው ነገር፥ ምን መሥራት እንዳለበት በግልጽ ተቀምጠዋል። በተለይ ማኅበሩ የበላይ ተጠሪው ማደራጃ መምሪያው እንደመሆኑ የሚሠራቸውን ዕቅዶች የማሳወቅ፣ ዕቅዶችንም ካሳወቀና በጠቅላላ ጉባኤው ላይ እንዲገኘ አድርጎ አስተያየት እንዲሰጥ ካደረገ በኋላ አስተካክሎ ያንን ማቅረብና ወደ ሥራ መግባት፥ ወደ ሥራ ከገባ በኋላ በየ6 ወሩ የአፈጻጸም ሪፓርት ማቅረብ የሚሉ ነገሮች ናቸው የተካተቱት፥ ይህ እንግዲህ የመጀመሪያውና ትልቁ ነገር ነው፡፡

ከዚያ ሪፖርት ተነሥቶ ማደራጃ መምሪያው በሚሰጠው ግብረ መልስ /Feed back/ እና መመሪያ መሠረት እየተነጋገረ ወደ ማስተካከያ ተግባሩ ይሄዳል ማለት ነው፡፡
 
የአንድ ተቋም ተጠሪነት ሲባልም ከዚያ ያለፈ አይደለም፡፡ ሙሉ በሙሉ እቅድ ላይ የሚሳተፍ፥ የተሠራውን ሥራም የማቅረብ ነው፡፡

ከዚያም ውጭ በአብዛኛው የማደራጃ መምሪያው በማኅበሩ አገልግሎት ላይ ድጋፍ የማድረግ ነገር ነው ያሉት፥ ለምሳሌ ማኅበሩ ከጠቅላይ ቤተ ክህነትና ከሌሎች ሦስተኛ አካላት ጋር የሚያደርገው ግንኙነት ችግር ቢገጥመው በማደራጃ መምሪያው ከዚያም አልፎ በጠቅ/ቤ/ክ አማካኝነት እነዚያ ግንኙነቶች እንዲስተካከሉና እንዲሰምሩ ይደረጋል፡፡

ማኅበሩ የባንክ አካውንት ሲከፍት በራሱ ስም ነው። የማኅበሩ ሕጋዊ ሰውነት ደግሞ በቤተ ክርስቲያኑ ነው፡፡ ይሄን አካውንት ደግሞ ቀጥታ ወደ ባንክ ቤት በመሄድ ራሱ አይከፍትም ። ማደራጃ መምሪያው ቢጽፍለትም እንኳን አይከፍትም፡፡ ስለዚህ ማኅበሩ ለማደራጃ መምሪያው ደብዳቤ ይጽፋል፡፡ እነዚህ… እነዚህ አካውንቶች ይከፈቱልኝ በማለትም ይጠይቃል፡፡ ከዚያም ማደራጃ መምሪያው ለጠቅላይ ቤተ ክህነት ይጽፋል፡፡ በዚያ መሠረት ይከናወናል፡፡ እንደገናም ማኅበሩ ከመንግሥት አካላት ሆነ መንግሥታዊ ካልሆኑ ተቋማትም ግንኙነት ፈልጎ ችግር ቢገጥመው ወይም ሕጋዊ ሰውነቱ ላይ ጥያቄ ቢኖራቸው፣ ይሄ የሚፈታው በቤተ ክርስቲያን በኩል ነው፡፡ ቤተ ክርስቲያን ደግሞ ይሄን ለማሳለጥ የመደበችው ማደራጃ መምሪያው ነው፡፡

ስለዚህ በሚሠሩት ሥራዎች በሙሉ እየተገኘ መመሪያዎችን የመስጠት፣ የማሳለጥ /facilitation/ ሥራዎችን የመሥራት፣ ሀገረ ስብከቶችና ጠቅላይ ቤተ ክህነት አስፈላጊው ትብብር እንዲያደርግ ኃላፊነት የተሰጠው ለማደራጃ መምሪያው ነው፡፡

በዚህ ዓይነት ግንኙነት ማደራጃ መምሪያው ለማኅበሩ የሚሠራው አለ፡፡ ማኅበሩ ለማደራጃ መምሪያው የአገልግሎት ማኅበር ስለሆነ ሪፖርት ነው የሚያቀርብለት፡፡ ሌላ ምንም ሊያደርግለት አይችልም፡፡

ስለሆነም ግንኙነታቸው እንዲህ በግልጽ የተቀመጠ ነው። በማንኛውም ተቋም የበላይና የበታች እንዴት እንደሚሠራ እንደተቀመጠው የተቀመጠ ነው፡፡

•    በመተዳደሪያ ደንቡ አንቀጽ 9 ቁጥር 1 መሠረት ማደራጃ መምሪያው ማኅበረ ቅዱሳን የሚያበረክተውን አገልግሎት በቅርብ ይከታተላል፣ ይቆጣጠራል፣ ተገቢውን መመሪያ ይሰጣል ይላል። ይህን እንዴት ነው ማኅበሩ የሚተረጉመው?

ማኅበሩ በዕቅድ የሚመራ ማኅበር ነው፡፡ ዕቅድ አለው በዚያ መሠረት ሥራውን ይሠራል፡፡ ማኅበሩ ጠቅላላ ጉባኤ ሲያደርግ የማደራጃ መምሪያው ኃላፊ በተገኙበት እያንዳንዱ አንቀጽ፥ እያንዳንዱ በጀት እያንዳንዱ ዕቅድ እያንዳንዱ አካሄድ ይታያል፤ ይገመገማል፡፡ የመጨረሻውን ዕቅዱን ዶክመንት ለማጽደቅ እንኳን ሦስት ቀን ይፈጃል፡፡ በዚያን ጊዜ ተገኝተው በእያንዳንዱ ጉዳይ ላይ መመሪያ ይሰጣሉ ማለት ነው፡፡ በነገራችን ላይ ከአባ ሠረቀ በፊት የነበሩ መምሪያ ኃላፊዎች በሙሉ በጠቅላላ ጉባኤ እየተገኙ መመሪያ ይሰጡ ነበር፤ ይከታተሉ ነበር፤ ምን እንደተወሰነ ያውቃሉ፡፡ ከዚያ በኋላ ደግሞ በተወሰነው መሠረት የ6 ወር ሪፖርት ሲቀርብላቸው ይሄ ለምን ተሠራ? ይሄ ለምን አልተሠራም? ይሄ ለምን ቀረ? ብለው ያያሉ በማኅበሩ ጽህፈት ቤት እየተገኙ የማኅበሩን የጽህፈት ቤት አሠራር ይጎበኛሉ፤ ይመለከታሉ። እርሳቸው ግን በ6 ዓመት ውስጥ ጽህፈት ቤቱን እንኳን አይተውት አያውቁም፡፡ እንዲመጡ ቢጋበዙም እኔ አውቃለሁ በማለት ነው እዛው ቁጭ የሚሉት፡፡ ይሄንን የመምሪያው ምክትል ኃላፊም የማኅበሩን ጽህፈት ቤት ጎብኝቶ ምንድን ነው የሚሠራው? እንዴት ነው የሚሠራው? ምን አገልግሎት ነው ያለው? ምን ድካም ነው ያለው? የሚሉትን ነገሮች አይቶ አያውቅም፡፡ እነዚህን ሰዎች በግድ ጎትቶ ማምጣት አይቻልም፡፡ ይሄ የእነርሱ ኃላፊነት ነው። በቅርብ ለመገኘት ይከታተላል ይቆጣጠራል ማለት በዕቅዱ በሪፓርቱ ብቻም አይደለም፡፡ በአካልም የመስክ ጉብኝቶችን በማድረግ እየተገኘ ማስተማር መመሪያ መስጠት የእነርሱ ኃላፊነት ነው። ይሄንን ከዚያ በፊት የመምሪያ ኃላፊ የነበሩት እነ ሊቀ ካህናት ኃይለ ሥላሴ አዲስ አበባ ብቻ አይደለም፤ ከማዕከላት ጋር ይወያዩ ነበር፡፡ በግቢ ጉባኤያት ተገኝተው ያስተምሩ፣ ይመክሩ፣ በርቱ ይሉ ነበር፡፡ እነዚህ ሰዎች ግን የት ቦታ ማኅበረ ቅዱሳን እንዳለ፥ ምን እንደሚሠራ አያውቁም፡፡ 

አሁንም ለቅዱስ ሲኖዶስ በቅርቡ የምናቀርበው ጥያቄ ኃላፊነታቸውን ያልተወጡ ሰዎች ስለሆኑ ውሳኔ ይሰጥልን ይሆናል፡፡ ይሄንን ጥያቄ አሁንም ከ 6 ዓመት በኋላ በድጋሜ እናቀርባለን፡፡ የማደናቀፍ ሥራ ብቻ ነው እየሠሩ ያሉት እንጂ አልተቆጣጠሩም፣ አልመሩም አልተከታተሉምና ሊመራ የሚችል አካል ለእኛ ብቻ አይደለም፥ በኢትዮጵያ ለሚገኙ ለመላው ሰንበት ትምህርት ቤት ያስፈልጋል፤ የሚል ጥያቄ ለማቅረብ በዝግጅት ላይ ነው፡፡

•    ማኅበረ ቅዱሳን አሁን ያሉት የመምሪያው ኃላፊ አላሠራኝ አሉ በማለት ይወቅሳል።  እንዴት ነው አላሠራ ያሉት? ከዚያ በፊት ከነበሩት የማደራጃ መምሪያ ኃላፊዎች ጋር የነበረው ግንኙነት ምን ይመሥል ነበር?

በቤተ ክርስቲያን ውስጥ ካሉት መምሪያዎች አንዱ የሰንበት ትምህርት ቤት ማደራጃ መምሪያ ነው። በ1956ዎቹና 1960ዎቹ የሰንበት ትምህርት ቤት ማደራጃ መምሪያ ሲቋቁምና ሲዋቀር፥ በተለይ በ1960ዎቹ ወደ ተግባር ሲመጣ፥ የተሰጠው ኃላፊነት ሕፃናትንና ወጣቶችን እንዲያስተምር ነው፡፡ በዚህ የማስተባበርና የማደራጀት ሥራ እንዲሠራም ነው፡፡ በእያንዳንዱ አጥቢያ ላይ ሰንበት ትምህርት ቤትና የወጣቶች ክፍል እንዲኖር የማስቻል ሥራ ነው የሚሠራው፡፡ በዚህ መሠረት ሲሠራ ቆይቶ፣ ከዩኒቨርሲቲ የተመረቁ በዩኒቨርሲቲ የተማሩ ወጣቶችን ይዞ ሲመጣ፥ የት ቦታ ነው መግባት ያለበት የሚለውን በማሰብ፥ ማኅበሩ ራሱ ነው በማደራጃ መምሪያው ስር ብደራጅና ቁጥጥር ቢደረግብኝ ይሻላል በማለት የሄደው፡፡ ስለዚህ በወቅቱ የነበሩትን የማደራጃ መምሪያ ኃላፊዎች ማኅበሩ አነጋገረ፣ እነርሱም ፈቃደኞች ሆኑ። በዚህ ምክንያት ማኅበረ ቅዱሳን በሰንበት ትምህርት ቤት ማደራጃ መምሪያ እውቅና ተሰጥቶት ግንቦት 2 ቀን በ1984 ዓ.ም ይፋ ሆነ። ስለዚህ ተጠሪው /አለቃው/ ማደራጃ መምሪያው ሆነ ማለት ነው፡፡ በጊዜው የነበሩት ኃላፊዎች አንድ ዓመትም አልሠሩ ከኃላፊነት ተነሱ፡፡ ቀጥለው ከነበሩት ኃላፊዎች ጋር በመግባባት መንፈስ ሥራዎችን ቀጠለ፡፡ እንዲህ እያለ ማኅበረ ቅዱሳን እስከ 1998 ዓ.ም ወደ 10 የሚሆኑ የመምሪያ ኃላፊዎች ሲፈራረቁ ቆይተዋል፡፡ ከሁሉም የማደራጃ መምሪያ ኃላፊዎች ጋር በመግባባት በትብብር ነው የሠራው። ስህተቶች ሲኖሩ የሚያርሙ መመሪያዎች ሲያስፈልጉ መመሪያ የሚሰጡ፣ የሥራ ትብብሮች ሲኖሩ የሚተባበሩ ለአገልግሎት ከአንድ ቦታ ወደ ሌላ በመሯሯጥ የሚሠሩና የምናስታውሳቸው የመምሪያ ኃላፊዎች ተሹመዋል፡፡ እግዚአብሔር ይመስገን በምንኩስናው የነበሩት ብዙዎቹ ወደ ጵጵስና ማዕረግ ደርሰዋል፡፡ ከእነዚህ ሁሉ ማኅበሩ እንደ አባትና ልጅ እንደ አለቃና ታዛዥ በመሆን ነው ሲሠራ የነበረው፡፡

አባ ሠረቀ ብርሃን የዛሬ 6 ዓመት ነው ወደ ማደራጃ መምሪያ በኃላፊነት የመጡት፡፡ ወደ ቦታው ከመጡበት ከመጀመሪያው ቀን ጀምሮ፤ እኔ የማኅበረ ቅዱሳንን ሰነዶች አይቻለሁ እስከ ዛሬ የሚሠራው ሥራ ልክ አይደለም፡፡ ኃላፊዎችም ልክ አልሠሩም በማለት ነው የጀመሩት፡፡ የመጀመሪያው አስተያየታቸውም እስከ አሁን የነበሩት የመምሪያ ኃላፊዎች ማኅበረ ቅዱሳንን በትክክል አልመሩትም፡፡ ኃላፊነታቸውንም አልተወጡም ከእንግዲህ በኋላ እኔ ነኝ የምወጣው ብለው ነው የጀመሩት፡፡

በዚህም የተነሣ ልክ እንደተቀመጡ የማኅበሩን አባላት ዝርዝር መረጃ ላኩልኝ ነበር ያሉት። ማኅበረ ቅዱሳን ከ120,000 በላይ የከፍተኛ ትምህርት ተቋም ተማሪዎችን አስተምሮ አስመርቋል። ሁሉን አባል አድርጎ ባይዝና ባይመዘግብም፥ ብዙዎች እንኳ ሳይመዘገቡ እኛ የማኅበረ ቅዱሳን አባላት ነን የሚሉ እጅግ ብዙ ናቸው፡፡ እነዚህ በሙሉ ስም ዝርዝራቸውን በHard copy /በጽሑፍ ተባዝቶ/ እንዲሄድላቸው ነው የአባ የመጀመሪያ ጥያቄ፡፡ እንግዲህ ማኅበሩ ከአገር ውጭ፣ ከውስጥም እስከ ገጠር ያሉትን አባላት ዝርዝር እንዲያመጣ ነው የተፈለገው፡፡

አሁን ጥያቄው፥ ምንድን ነው ጥቅሙ? እንዲህ ዓይነት መመሪያስ አለ ወይ? የሚለው ነው። ይሄ አላስፈላጊ ነው፤ ባይሆን የአመራሩን ዝርዝር እንላክ፤ የሚል ሐሳብ ስናነሣ ይሄ በፍጹም አይሆንም፤ ዝርዝራቸውን ካላገኘን አሉ። በተጨማሪም ሌሎችን በፍጹም ከኃላፊነት ጋር ያልተገናኙ ጥቃቅንና ከቁጥጥር ጋር ያልተገናኙ ጥያቄዎችን ያቀርባሉ፡፡ እኛም እንደዚህ አይደለም በማለት እንመልሳለን፡፡ በተቀመጡ 6 ወር ባልሞላ ጊዜ ውስጥ ወደ 5 ደብዳቤ ነው ለማኅበረ ቅዱሳን አከታትለው የጻፉት። ስለዚህ ግንኙነታችን በጣም የማይሆን የደብዳቤ ልውውጥ ሆኖ ሲገኝ፥ አንድ ዓመት እንኳ ሳይሠሩ ወደ ቅዱስ አባታችን አቤቱታ አቀረብን። በአካልም በመገኘት «በመምሪያ ኃላፊነት የተመደቡት አባት ተባብሮ ከማሠራት ይልቅ ሥራ እያደናቀፉ ነው ያሉት፥ ለእኛ ብቻ ሳይሆን አጠቃላይ በኢትዮጵያ የሚገኙትን ሰንበት ትምህርት ቤቶች ለማደራጀት ብቃት የላቸውም፥ ስለዚህ ከኃላፊነት ተነስተው ሌላ ሰው ይመደብልን ቅዱስነትዎ የሚያምኑበትን ሲያሠራና ሊሠራ የሚችል ሰው ይመድቡልን» ብለን ጥያቄአችንን አቀረብን፡፡ ቅዱስነታቸው “እናንተ ብዙ ሰዎችን ማሳመን የምትችሉ፣ አንድ ደካማ መነኩሴ ይነሣ ብላችሁ ጥያቄ ማቅረብ የለባችሁም ይሄ ከእናንተ ደረጃ በታች ነው፡፡ ስለዚህ አሳምኑ” የሚል ሐሳብ ነው የሰጡን። በዚህ ጊዜ «በቅዱስ አባታችን በተቀመጡ በ6 ወራቸው 5 ደብዳቤ ጽፈዋል፡፡ ስለዚህ ደብዳቤ መጻፍ ነው ሥራቸው የምንሰጣቸውንም መልሶች እየሰሙና በአግባቡ እየመሩን አይደለም፡፡” የሚል ጥያቄ አቅርበናል፡፡ አሁን ላይ ሆነን ስናየው የዛሬ 6 ዓመት ይሄን ጥያቄ ማቅረባችን ትክክል ነበር፡፡ በወቅቱ ገና አጀማመራቸው ማኅበረ ቅዱሳንን የመቆጣጠር ሳይሆን የማቆም ዕቅድ ነው ያላቸው ይሄን ደግሞ በይፋ እየሠሩት እንደነበር አይተናል፡፡

እንግዲህ ከዚያ በኋላ ኃላፊው ማንኛውም ጥናትና ማኅበረ ቅዱሳንን የሚመለከት ነገር ወደ ቅዱስነታቸው ሲያቀርቡ፥ ለማኅበረ ቅዱሳን ግልባጭ አያደርጉም፤ በስውር ነው የሚጽፉት፡፡ ከ25 ገጽ ያላነሰ ጥናት የሚባል ነገር ከሌሎች የተሐድሶ ቡድንና የሃይማኖት አበው አባላት ጋር በመሆን ጥናት የሚመስል ነገር አቅርበዋል፡፡ ባቀረቡት ጥናት ላይም ማኅበረ ቅዱሳን የሚለው ክፍል አያስፈልግም፡፡ ወጣቶች በሙሉ በአንድ ተጠቃለው መመራት አለባቸው፡፡ ሐመርና ስምዐ ጽድቅንም እኛ እናዘጋጃለን፤ እኛ እንረከበው፡፡ የከፍተኛ ትምህርት ተቋም ተማሪና የሰንበት ተማሪ ብሎ መከፋፈል አያስፈልግም። በአንድነት ወጣቶችን ሰብስበን ልናስተምር እንችላለን፡፡ ለዚህ የሚያሰፈልጉ ወደ 300 የሚጠጉ የነገረ መለኮት /theology/ ምሩቃንን ከነበጀቱ ይመደቡልን፡፡ ጠቅላላ እኛ እናስተምራለን፡፡ የሚል ጥያቄ የዛሬ 4 ዓመት ነው ያቀረቡት፡፡ ያ ጥናት በወቅቱ ባለመመለሱ ተከታታይ ደብዳቤ ለቅዱስነታቸው ጽፈዋል፡፡ እነዚያ ደብዳቤዎችም፥ ተስፋ ቆርጫለሁኝ ስለዚህ ወደ ትምህርት መመለስ አለብኝ፡፡ እሠራለሁ ብዬ ነበር የመጣሁት፥ ስለዚህ ተግባራዊ እየሆነልኝ አይደለም ያለው የሚል አቤቱታ ያዘለ ደብዳቤ ሲያቀርቡ ቆይተው በአሁኑ ወቅት ያለን ግንኙነት ከተሐድሶ ማንሠራራት ጋር ተያይዞ የቤተክርስቲያኒቷን አደረጃጀት በውስጥም በውጭም እየያዙ ሲመጡ አሁን በትብብር የሚሠራበትና አንድ ላይ ሆነው የሚያጠቁበት ደረጃ ላይ ነው የደረሱት። በዚህ ምክንያት ማኅበረ ቅዱሳን ላይ ተደጋጋሚ የሆኑ ደብዳቤዎችን የመጻፍ፣ የማይሆኑ ትዕዛዞችን የማዘዝ፣ ተፈጻሚ ሊሆኑ የማይችሉ መመሪያዎችን የማስተላለፍ፣ ሥራ የማገዝና ተፈጻሚ እንዲሆኑ የማቀላጠፍ ሳይሆን የማደናቀፍ የማቆም፣ የኦርቶዶክሳዊት ቤተ ክርስቲያን ስብከተ ወንጌል እንዳይካሄዱ እንቅፋት የመፍጠር፣ ወጣቶች እንዲማሩ ሳይሆን እንዲበተኑ የማድረግ ሥራዎች ነው እየተሠሩ ያሉት በዚህ በጣም እናዝናለን፡፡

የእኛን ሥራ የመደገፍ ይቅርና የተመደቡበትን ሰንበት ትምህርት ቤቶችን እንኳ ዘወር ብሎ ለማየትና አንዱም ቦታ ላይ የማስተማሪያ መጻሕፍትም ይሁን መምህራን ተመድበው የሌለበት ቦታ ነው። አሳዛኝ በሆነ ሁኔታ ትውልዱን የሚመራው ክፍል እንደዚህ ሆኖ ይገኛል፡፡ እንግዲህ ያለን ግንኙነት ይሄንን ይመስላል፡፡
•    የማደራጃ መምሪያው ኃላፊ ማኅበረ ቅዱሳን በቤተ ክርስቲያን አገልግሎት ላይ ከፍተኛ ስጋት እየተፈጠረ እንደሆነ በተለያዩ መገናኛ ብዙሃን እየገለጹ ይገኛሉ፡፡ እውነት ሥጋት ነው? እርሳቸው እንዲህ የገለጹት በምን ምክንያት ይመስልዎታል፡፡

ለአባ ሠረቀ ማኅበረ ቅዱሳን ለቤተ ክርስቲያን ከፍተኛ አደጋ አለው፡፡ ቤተ ክርስቲያኒቷን እየተካት ነው። የማኅበረ ቅዱሳን አወቃቀርና አደረጃጀት አጠቃላይ ቤተ ክርስቲያኒቷን መዋቅር የተመለከተ ነው፡፡ ይኸውም ማለት እንግዲህ በቅዱስ ሲኖዶስ የተሰጠውን መዋቅር ነው እንዲህ እያሉ ያሉት። ቅድም እንደገለጽኩት 25 ገጽ ጥናት ለቅዱስ ፓትርያርኩ ሲያቀርቡ፣ በጥናቱ ውስጥ ለማኅበረ ቅዱሳን የተሰጠው መተዳደሪያ ደንብ በቂ አይደለም፥ ቅዱስ ሲኖዶስ ተሳስቷል ነው የሚለው፡፡ እንዲህ ዓይነት መተዳደሪያ ደንብ ለማኅበረ ቅዱሳን መሰጠት አልነበረበትም፤ ስለዚህ ስህተት ተፈጽሟል፤ ይሄ ስህተት መታረም አለበት፡፡ ለመታረም ደግሞ ደንቡ ይሻሻል ሳይሆን ጭራሽ መቆም አለበት የሚል አስተሳሰብ ነው፡፡ ስለዚህ ቅዱስ ሲኖዶስን ነው የሚወቅሰው። እንዲያውም መተዳደሪያ ደንቡ ማደራጃ መምሪያውን ለማኅበረ ቅዱሳን ሎሌ አድርጎታል፥ ጭራሽ ጉዳይ አስፈጻሚ አድርጎታል እንጂ አለቃነቱን የሚያሳይ አይደለም በሚል ነው የቅዱስ ሲኖዶስን ውሳኔ እየተቃወሙ ያሉት፡፡

ይሄን እንዳለ ትተነው ለቤተ ክርስቲያኒቱ አደጋ ነው በማለት የሚያስቀምጡት የራሳቸውን ሥጋትና አስተሳሰብ ነው፡፡ ማኅበረ ቅዱሳን ለቤተ ክርስቲያኒቱ አጋዥ ነው፡፡ ክፍተቷን የሚሞላ የሚደግፍ ነው፡፡ ምዕመናን እንዳይበተኑ በተለይም የከፍተኛ ትምህርት ተቋም ተማሪዎች እንዳይበተኑ እያደረገ ነው፡፡ ይሄንን አባ ሠረቀ ብርሃን አዛብቶ በማቅረብ ቤተ ክርስቲያኒቷን እየተካ ነው፡፡ የሚል የራሳቸውን የሥጋት ስሜት ሌሎቹም ላይ ለመጫን ነው፡፡

እንደማነጻጸሪያ የሚያቀርቡት የማኅበረ ቅዱሳንን አወቃቀርና የቤተ ክርስቲያኒቷን አወቃቀር ነው፡፡ እርሳቸው በራሳቸው የተሳሳተ መንገድ ነው እያቀረቡት ያለው፡፡ ለምሳሌ የማኅበረ ቅዱሳን ጠቅላላ ጉባኤ ከቅዱስ ሲኖዶስ ጋር እኩል ነው፤ የማኅበረ ቅዱሳን ሥራ አመራር ጉባኤ የቋሚ ሲኖዶስ ጉባኤ አቻ ነው፤ የማኅበረ ቅዱሳን ሥራ አስፈጻሚ ጠቅላይ ቤተ ክህነት እንደማለት ነው በማለት ራሳቸው ፈጥረው ነው ያቀረቡት፡፡ እኛ ጋር የሌሉ ክፍሎችን ሁሉ እያነጻጸሩ ነው ማኅበረ ቅዱሳን ለቤተ ክርስቲያኒቷ አደጋ ነው፤ እየተካትም ነው፡፡ እያለ የሚል አስተሳሰብ የሚያንጸባርቁት፡፡ ስለዚህ ይሄ አስተሳሰብ ሙሉ በሙሉ የአባ ሠረቀ ነው፡፡

አባ ሠረቀ ይሄንን ስጋት ከየት አመጡት? ከተባለ ከዓላማቸው አኳያ ነው፡፡ በፍጹም የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያንን የማሳደግና ወጣቶችን የመሰብሰብ የማስተማር ፍላጎት የላቸውም። ቤተ ክርስቲያኒቷ እንድትጠናከር እየሠሩ ነው ማለትም አይቻልም፡፡ ተግባሮቻቸውም የሚያሳዩት የኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን ወጣቶች፣ የሰንበት ትምህርት ቤት ወጣቶች፣ የከፍተኛ ትምህርት ተቋም ተማሪዎች ትምህርታቸውን እንዳይማሩ የሚሰጠውን የስብከተ ወንጌል አገልግሎት ማስቆም ነው፡፡ ይሄ በምንም ዓይነት ምክንያት የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ተልዕኮ ማስፈጸም ነው ተብሎ አይታመንም፡፡ ማኅበረ ቅዱሳንም በዚህ አያምንም፡፡ እርሳቸው የያዙት መንገድ ሙሉ በሙሉ የኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያንን ማዳከም ነው፡፡ ትውልድ የማሳጣት ሥራዎችን የመሥራት ነው፡፡ ይሄ ደግሞ የሌሎች ተልዕኮ ነው። ስለሆነም ሌላ የተጫኑት ተልዕኮ አለ ብለን ነው የምናምነው፡፡ ከሌሎች የተጫኑት ቤተ ክህነቱን የማዳከም ተልዕኮ አላቸው። የማኅበረ ቅዱሳን ሥራ ቤተ ክርስቲያኒቷን የሚያጠናክር ከሆነ፥ ማኅበረ ቅዱሳንን ማቆም ቤተ ክርስቲያኒቷ እንዳትጠናከር አንድ እርምጃ ብለው ስለሚያስቡ በተቻላቸው መጠን ስም በማጥፋት ለቤተ ክርስቲያኒቷ ስጋት ነው በማለት ማቅረብና የሁሉንም ትኩረት እንዳያገኝ የማድረግ ሥራ ነው የሚሠሩት። በዚህ ተግባር ላይ ተሠማርተው ነው ያሉት በአሁኑ ወቅት፡፡
•    ሌላው የሚነሳው ጉዳይ፣ መስከረም 12 ቀን 2002 ዓ.ም ከመንግሥት ባለሥልጣናት፣ ከሊቃነ ጳጳሳትና ከቅዱስ ፓትርያርኩ ጋር በተደረገው ስብሰባ ላይ ማኅበረ ቅዱሳንን በመክሰስ ሂደት ላይ እርሳቸው አንድ ተሳታፊ እንደነበሩ ይነገራል፡፡ በወቅቱ ሁኔታው እንዴት ነበር? የእሳቸው ሚናስ ምንድን ነበር?

በእርግጥ በአጋጣሚ አልተገኘሁም፡፡ የመስከረም 12 ጉባኤ ከመደረጉ በፊት መኖሩን አናውቅም ነበር፡፡ ነገ ጠዋት እንድትገኙ ነው የተባለው፡፡ እኔ በሰማሁትና በነበሩት ሪፓርቶች ሁኔታ፥ በጉባኤው ላይ አባ ሠረቀ ብርሃን ዋነኛው የጉባኤው ከሳሽ ሆነው ነው የቀረቡት፡፡ ሁሉም እንደሚያስታውሰው በወቅቱ ማኅበረ ቅዱሳን የተከሰሰው በሁለት ጉዳዮች ነው፡፡ በፓለቲካ ውስጥ ገብቷልና የቤተ ክርስቲያን አስተዳደር ውስጥ ጣልቃ ገብቷል የሚል ነው፡፡ ሁለቱም ምንም ዓይነት መሠረት የሌላቸው ናቸው። ማኅበረ ቅዱሳን ፖለቲካ ውስጥ ገብቷል ያሉት በተለያዩ ጊዜ የተጻፉ ዘገባዎችን በማንሣት ጥፋተኛ እንደሆነ ለማሳየት ነው የተሞከረው፡፡ ይሄ የጽሑፍ ሥራ ነው፡፡ እነዚህ ጽሑፎች ሙሉ በሙሉ ሲተረጎሙ ምንም ዓይነት አንድምታ /impact/ አይኖራቸውም ብሎ ማለት ላይቻል ይችላል፡፡     ነገር ግን ሆን ተብሎ የፖለቲካ አቅጣጫ ውስጥ ለመግባት የተሠራ ሥራ አይደለም። ትምህርት የማስተማር፣ ስብከተ ወንጌልን የማስፋፋት፣ ቅድስት ቤተ ክርስቲያንን የመጠበቅ፣ ሠላም እንዲኖር የማድረግ ኃላፊነቶችን እንደ ዓላማ አድርጎ ነው የሚሠራው። ዳሩ ግን እነዚህን በመያዝና ጉዳዩን መንግሥት በልዩ ትኩረት እንዲያየው ለማድረግ በማሰብ ከስም ማጥፋት ተግባሮች እንደ አንዱ ሆኖ የቀረበው ነው። ማኅበረ ቅዱሳን ሲጀመር ጀምሮ የስም ማጥፋቶች ሲሠሩ ነበር፤ በተለይ በቤተ ክርስቲያን ጠላቶች፡፡ ካለፉት 5 እና 6 ዓመታት ወዲህ የአባ ሠረቀ ወደዚህ ኃላፊነት መምጣት ይሄንን የስም ማጥፋት ዘመቻ የበለጠ ለማጧጧፍ ጉዳዩን መንግሥትም እንደ አደጋ እንዲያየው ለማድረግ የተጠቀሙበት ዘዴ ነው፡፡ ዓላማቸውንም ለማሳካት ሌላ ኃይልን በሙሉ የማሰባሰብ ነው፡፡ ልክ ጌታን ሮማውያን እርምጃ እንዲወሰዱበት በአይሁድ በፖለቲካ እንደተከሰሰው። ያልሠራውን ሠራ ግብር እንዳይከፍል ከልክሏል ሲባል እንደነበረው። አሁንም ተመሳሳይ የስም ማጥፋት ዘመቻና ቤተ ክርስቲያንን የማሳደድ ዘመቻ ነው ያለው፡፡ በዚህ ምክንያት ነው ማኅበረ ቅዱሳን የተከሰሰው እንጂ፥ በእንደዚህ ዓይነት አቋም ማኅበረ ቅዱሳን በምንም ዓይነት መልኩ በፖለቲካ ጣልቃ ገብነት የለውም፥ አይኖረውም። ይሄ በመተዳደሪያ ደንቡ የተገለጠ ነው።

የቤተ ክርስቲያን አስተዳደር ላይም ቢሆን ቅዱስ ሲኖዶስ እስከሚያጸድቀው ድረስ ማኅበረ ቅዱሳን ጣልቃ አይገባም የሚል አንቀጽ ነበረው፡፡ የአባቶች ኮሚቴ ሲነጋገር፥ ቅዱስ ሲኖዶስ ሲያጸድቅም፥ ‹‹ግቡም አትግቡም›› የሚል እዚህ ቦታ ላይ አያስፈልግም። አስፈላጊ ሲሆን ማኅበረ ቅዱሳን ቤተ ክርስቲያንን በአስተዳደር መርዳት ይኖርበታል። መደገፍ ይኖርበታል። ‹‹ደንቤ አይፈቅድልኝም›› እያለ ዳር ቆሞ ማየት የለበትም በማለት ቅዱስ ሲኖዶስ በምልዐተ ጉባኤ ሲያጸድቅ ይሄን አንቀጽ አስተካክሎ ነው ያጸደቀው። ይሁን እንጂ ማኅበረ ቅዱሳን ካለው ልምድ በመነሣት በቤተ ክርስቲያን አስተደደር ላይ ‹‹እከሌ ይሾም፣ እከሌ ይውረድ እገሌ እንዲህ ነው›› የሚል ነገር አንስቶም አያውቅም። እስከ ዛሬው ሰዓት ድረስ ‹‹ደንቤ ይከለክለኛል፤ አይፈቅድልኝም›› በሚል መንገድም ሄዶ አያውቅም።
 
በ2002 ዓ.ም የተደረገው ስብሰባ ምን ማለት እንደሆነ ራሱ ግልጽ አይደለም። ምን አልባት በቅዱስ ሲኖዶስ ሲነሱ የነበሩ ውዝግቦችን መሠረት አድርጎ ይሆናል፡፡ በዚያን ጊዜም ቢሆን ማኅበር ቅዱሳን አቋሙ ግልጽና ግልጽ ነው። ቅዱስ ሲኖዶሱ በሚወስነው ውሳኔ ይሄዳል የሚል ነው። ያን ሁሉ ውዝግብ የፈጠረው ማኅበረ ቅዱሳን ነው የሚል ስሜት በአባቶቻችንና በሌሎች ሰዎች ለማሳደር የተወጠነ ነው። እንኳን በቅዱስ ሲኖዶስ ጉዳይ ይቅርና በአንድ አጥቢያ ጉዳይ ማኅበረ ቅዱሳን ጣልቃ ገብቶ አያውቅም፡፡ የመግባትም ፍላጎት የለውም። ትልቁ የስብከተ ወንጌል ጉዳይ እንጂ የገንዘብና የአስተዳደር ነገር ዋነኛ ጉዳይ ነው ብሎ አስቦበት አያውቅም።

ሌላው በአባ ሠረቀና በሌሎችም የቀረበው ክስ የኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን ምእመናን ከአክራሪዎች እንዲጠበቁና ራሳቸውን እንዲከላከሉ በንቃት ዙያቸውን እንዲያዩ፣ የተጎዳውን በመርዳት በኩል እንዲተባበሩ፣ ቤታቸው የተቃጠለባቸውን እንዲሠሩ፣ የተጎዳ ተጎድቶ እንዳይቀር ሁሉም እንዲነሳሳ የሚያደርጉ መልእክቶችን በስምዐ ጽድቅ ጋዜጣና በሐመር መጽሔት ላይ በ1999 ዓ.ም አክራሪዎች ባደረሱት ጥቃት ምክንያት የጻፍነውን በማንሳት፥ ‹‹ይሄ ቀስቅሷል›› የሚል ከሌላ አካል አይደለም ከራሳችን የቤተ ክርስቲያን አካላት ከአባ ሠረቀና ከሌሎች አካላት በዚያው ዕለት ቀርቦ ነበር፡፡ 

ለተነሱት ጉዳዮች በሙሉ ብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳትም ሁሉም በቂ መልስ ሰጥተዋል። ካጠፋም ማኅበረ ቅዱሳንን እኛ ነው የምንመክረው፤ በቅዱስ ሲኖዶስ ነው የምንመክረው። ከእኛ አቅም በላይ አይደለም የሚል ሐሳብ ተንጸባርቆ ነው የዛን ቀን ስብሰባዎቹ የተደመደሙት። ስለዚህ ያን እንደሌላ ድልና ውጤት በመቁጠር ማኅበረ ቅዱሳንን ለመወንጀልም ስሙን ለማጥፋት የሚሄድበትና የዚያን ጊዜም እድል ተሰጥቶት አልታረመም በሚል ነው እየከሰሱት ያሉ።

•    የተሃድሶ መናፍቃን እንቅስቃሴ ለመግታት ዘመቻ የተያዘበት ወቅት ነው፡፡ ዳሩ ግን ኃላፊው የግለሰቦችን ስም መዋቅር ሳይጠብቅ ተሃድሶ መናፍቅ ወዘተ እያለ ያመጣል የተለያዩ ጉዳዮችን ያነሣል? በሚል ክስ ያቀርባሉ ስለዚህ ክስ ማኅበሩ ያለው አቋም ምንድን ነው?

ከዚህ በፊት በግልጽ ፕሮቴስታንት መሆናቸው የታወቁ፥ በቅድስት ሥላሴ መንፈሳዊ ኮሌጅ ገብተው የነበሩና የተባረሩ አሉ። አንዱ ‹‹ዲ/ን›› ሙሉጌታ ወ/ገብርኤል የሚባል ነው። ይህ ግለሰብ እዛው ኮሌጅ ውስጥ በመባረር በሂደት ላይ እያለ፣ ከወጣ በኋላም «ማኅበረ ቅዱሳን ወይስ ማኅበረ ሠይጣን›› የሚል መጽሐፍ ጻፈ። ለመጽሐፉ ሰነድ የወሰደው ከማደራጃ መምሪያው ነው። እርሱንም የሰጡት አባ ሠረቀ ብርሃን ናቸው። የእርሱ ማሳተም ብቻ አይደለም ቁም ነገሩ፤ ከዚያ በኋላ የመጽሐፉ ስርጭት ላይም ተሳታፊ ነበሩ። እኛ አስቁሙ ብለን ደብዳቤ ስንጽፍላቸው ማቆም አልቻሉም። በዚህም የተነሣ ከተሐድሶ መናፍቃን ጋር ያላቸው ጥምረት እጅግ በጣም የጠበቀ ሆኖ እናገኘዋልን። ሌሎችንም ተጨማሪ ማስረጃዎች ማቅረብ ይቻላል፡፡ 

አሁን የተሃድሶ መናፍቃን እንቅስቃሴ እየጠነከረ በሄደበት ወቅት ላይ ለማደራጃ መምሪያና ሌሎች ብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳት በተገኙበት ገለጻ አድርገናል። አባ ሠረቀ ግን በእኛ መርሐ ግብር ላይ አይገኙም። ቢጋበዙም አይመጡም። ማኅበሩ በሚያዘጋጃቸው መርሐ ግብሮች ላይ ጥናቶች ላይ አይገኙም። ስለዚህ እኛ ለሊቃነ ጳጳሳት ሳናሳውቅ ለቅዱስ ሲኖዶስ ሳናሳውቅ ሥራዎችን አልሠራንም። እንቅስቃሴውንም በሚመለከት ከ10 በላይ ለሚሆኑ /ተጨማሪ?/ ሊቃነ ጳጳሳት አሳውቀናል። በጽሑፍም ከ25 በላይ ለሚሆኑ ሊቃነ ጳጳሳት አሳውቀናል። እንግዲህ በቀጣይነት ወደ ቅዱስ አባታችን ገብተን ለማሳወቅ ፕሮግራም ይዘን ባለንበት ወቅት ነው የተሃድሶ መናፍቃኑ ቡድኑ ማዋቅሩን ዙርያውን በመያዝ ወደ ኋላ በመጎተት የስም ማጥፋት ዘመቻዎችን በማኅበሩ ላይ በማካሄድ ከቅዱስነታቸው ጋር ለማጣላትና ለማራራቅ ሙከራዎችን የሚያደርጉት። እኛ አሁን በቅዱስነታቸው መመሪያ ሰጭነት በዚህ በተሕድሶ ጉዳይ ላይ ቤተ ክርስቲያን መፍትሔ ታገኛለች የሚል እምነት አለን፡፡ 

ማደራጃ መምሪያውም ‹‹እኔ ነኝ ማወቅ ያለብኝ። ማንም ሰው መስማት የለበትም።›› የሚለው ይሄ ስሕተት ነው። የአፈጻጸም ሪፓርት አይደለም የምናቀርበው፥ ጥናት ነው ያቀረብነው፡፡ ዓውደ ጥናት ላይ የመንግሥትም መንግሥታዊ ያልሆኑ ባለስልጣናትም ሌሎችም ሰዎች በተገኙበት ጥናት ይቀርባል። ይሄ እንደ አንድ ግኝት፣ ጥናትና እንቅስቃሴ የሚቀርብ እንጂ እኔ ሳላምንበት የሚለው ያልታየ አዲስ አካሄድ ነው። የማደራጃ መምሪያውም በተለይ አባ ሠረቀ ብርሃንም ይሄን ጥናት ደግፈው ይጓዛሉ የሚል እምነትም የለንም። የዓላማ ጉዳይ ስለሆነ ከዚህ በተጻራሪ ቆመው ነው ያሉት። ስለሆነም ጥያቄያቸው እኔ ሰምቼ ለምን አላስቆምኩትም ነው እንጂ፥ ጥናትን ለማቅረብ የግድ የማደራጃ መምሪያው ፈቃድ የሚያስፈልገው ሆኖ አይደለም፡፡ አሁንም በጥናትና ምርምር ማዕከላችንም ሆነ በሌሎች ብዙ ጥናቶችን እናቀርባለን። እነዚህ ጥናቶች በዓመት ዕቅድ ተይዞላቸው የሚቀርቡ ናቸው። የተሐድሶ መናፍቃን እንቅስቃሴ ግን ቤተ ክርስቲያኒቷን ከፍተኛ የሆነ አደጋ ላይ እየጣለ ያለ ጉዳይ ስለሆነ በዚህ ጉዳይ ላይ ብፁዓን አባቶች አይተው፣ ሰምተውት ሕዝቡም ማወቅ አለበት የሚለውን ሐሳብ ሰጥተውበትና እነርሱም በጽሑፍ ደርሷቸው ተረድተውት የቀጠልነው ነው። ቅዱስ አባታችን ጋርም አሁንም እስከ ሲኖዶስ ስብሰባ ባለው ጊዜ ውስጥ በተቻለ መጠን ጉዳዩን ተረድተውት አውቀውት የእነዚህን ሰዎች ተንኮልና አካሄድ እንዲያስቆሙ ለማድረግ አሁንም ጥረታችንን እየቀጠልን ነው፡፡
•    ምንም እንኳን ቀሲስ ዶ/ር ሙሉጌታ በ2002 የሥራ ክንውን ሪፖርታቸው ቢገልጹትም አሁንም በኃላፊው መግለጫ ላይ ማኅበረ ቅዱሳን ሂሳቡን ኦዲት አያስደርግም? የባንክ ሂሳቡንም ለማደራጃ መምሪያው ለማሳወቅ ፍቃደኛ አይደለም የሚል ይገኝበታል ስለዚህ ምን ይላሉ? 

በእውነቱ ቅድም እንደጠቀስኩት ማኅበረ ቅዱሳን የሚከፍተው የሂሣብ አካውንት በሙሉ በጠቅላይ ቤተ ክህነት ታውቀው የሚከፈቱ ናቸው፡፡ ሂሣቡን አያሳውቅም የሚለው ሩቅ ላለ ሰው አስደንጋጭ የሆነ የውሸት ክስ ነው፡፡ ሙሉ በሙሉም ሐሰት ነው፡፡ በጠቅላይ ሥራ አስኪያጅ ፊርማ ከዚህ በፊት በነበሩት መምሪያ ኃላፊዎች ጥያቄ ለጠቅላይ ሥራ አስኪያጅ እየቀረበ የሚከፈተውን የባንክ አካውንት ማኅበረ ቅዱሳን ምስጢር አድርጎ እንደያዘው ሁሉ የባንክ አካውንቱን አያሳውቅም ማለት ምዕመናንን ለማስደንገጥ የታሰበ ነው፡፡ ምዕመናንም ለገዳማትም ለሌሎች አገልግሎቶችም የምትሰጡትን ገንዘብ ለእኛ እያሳወቀ አይደለም በማለት ስም ለማጥፋትና አስደንግጦ ወደ ኋላ ዘወር ለማድረግ የታሰበ ነው እንጂ የማኅበረ ቅዱሳን አካውንት ይታወቃል። ከዚያም በፊትና ከብፁዕ አቡነ እስጢፋኖስ ጀምሮ የነበሩት ጠቅላይ ሥራ አስኪያጆች ናቸው ደብዳቤ ጽፈው ፈቅደው የባንክ አካውንት የሚከፈተው እኔ አላውቀውም የሚሉ ከሆነ የጠቅላይ ቤተ ክህነት መዝገብ ቤትን ማየት በቂ ነው።

ሁለተኛው ኦዲት አያስደርግም ለሚለው በማኅበሩ መተዳደሪያ ደንብ የተቀመጠው፣ የማኅበሩ ኦዲትና ኢንስፔክሽን በየዓመቱና በየጊዜው የማኅበሩን ኦደት ይሠራል ኢንስፔክት ያደርጋል፤ የሚል ደንብ በቅዱስ ሲኖዶስ ተሰጥቶታል። አስፈላጊ ሆኖ ሲገኝ የማኅበሩ ሥራ አመራር ጉባኤ በውጭ ኦዲተር የማኅበረ ቅዱሳንን ሂሣብ ኦዲት እንዲደረግ ያደርጋል። ማኅበሩ ዓለም አቀፍ እውቅና ባላቸው የውጭ ኦዲተሮች፣ በመንግሠት የምሥክር ወረቀት የተሰጣቸው /licensed የሆኑ/፣ ግብር የሚከፈሉ፣ በሥራቸውም ጥፋት ቢያጠፉ ሊጠየቁ በሚችሉ ኦዲተሮች አስመርምሯል። ለወደፊትም ያስመረምራል። ይሄንንም ሪፖርት ለጠቅላይ ቤተ ክህነት፣ ለማደራጃ መምሪያውና ለሚመለከታቸው አካላት አስገብቷል። የማኅበረ ቅዱሳንን የኦዲት ሪፖርት አሠራር ውድቅ ሊያደርግ የሚችል አላየሁበትም በማለት አሳውቋል። ስለዚህ ይህ በሆነበት የማኅበረ ቅዱሳን ሂሣብ አይታወቅም አይደረግም ማለት በጣም ከፍተኛ የሆነ ስም የማጥፋት ሥራ ነው። ወይም ስለ ኦዲት ያለመረዳት ችግሮች አይኖርም ብለን አናስብም፡፡
•    ይሄ አለመግባባት ችግር እስከመቼ ይቀጥላል? ማኅበሩስ አቋሙ ምንድን ነው? 

በእነዚህ ስም የማጥፋት ዘመቻዎችና ሁኔታዎች ማኅበረ ቅዱሳን አይደናገጥም። ማኅበሩ የተመሠረተው የቤተ ክርስቲያኒቷን ክፍተት ለመሙላት፣ ድጋፍ ለማድረግ ነው። ሁላችን የሰበካ ጉባኤ አባላት ነን፣ የሰንበት ትምህርት ቤትም አባላት ነን፣ አጥቢያ አለን፣ ቤተ ክርስቲያን አለችን አናስቀድሳለን፣ እንቀድሳለን፣ እናስተምራለን አገልግሎትም እናገኛለን ከአንድ ምእመን የሚጠበቀውን አገልግሎት እንሰጣለን። ማኅበረ ቅዱሳን የመጣው ተጨማሪ ሥራዎችን ለመሥራት፣ ተጨማሪ ጊዜ ለመስጠት፣ ተጨማሪ ጉልበት ለመሥጠት፣ ተጨማሪ ገንዘብ ለማውጣት ነው እንጂ ሌላ ምንም ጥቅም ኖሮት አይደለም። ቤተ ክርስቲያን ተጨማሪ ሥራ ለምን ያስፈልጋታል ከተባለ የዛሬ 20 ዓመትም፥ 25 ዓመትም የነበሩት ችግሮች ዛሬም አልተፈቱም። ገዳማት እየተዘጉ ነው ያሉት፣ ስብከተ ወንጌል በአግባቡ እየተሥፋፋ አይደለም፡፡ ሰንበት ትምህርት ቤቶች ሥርዓተ ትምህርት የላቸውም። ሰንበት ትምህርት ቤት የተቋቋመባቸውና ያልተቋቋመባቸው ቢታዩ 25% አይሆኑም፣ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ተማሪዎችን ለማስተማር አካል ያስፈልጋል እነዚህ ናቸው ማኅበረ ቅዱሳንን እንዲመጣ ያደረጉት። 

ይሄ በራሷ በቤተ ክርስቲያኒቷ መዋቅር ለምን አልተሠራም? ካልን ወደ ዘመናዊው ጊዜ ስንመጣ ያልተለወጡ የተወሰኑ ነገሮች አሉ። ስልት /Strategy/ የለም፣ ዕቅድ የለም፤ በእነዚህ ሥራዎች ላይ መሥራት አልተጀመረም። ከዚያም ይልቅ ሥራን ማደናቀፍ በጣም ትልቅ ሥራ ሆኖ ነው የምንመለከተው። አጠቃላይ የቤተ ክርስቲያኒቷን አስተዳደር አካሄድ አሠራር በተቀናጀና ዕቅድ ባለበት ሁኔታ ለመምራት በጣም ብዙ ሥራዎች ይቀራሉ። ከሚሠሩ ይልቅ የሚያደናቅፉ በጣም ብዙ እንዳሉ እናውቃለን። ቤተ ክርስቲያኒቷንም የማዳከም ሥራ የሚሠሩ ብዙ እንዳሉ እናውቃለን። ይሄን ሠርታችኋል በርቱ ከመባል ይልቅ አቁሙ አቁሙ እንደምንባል ጥንትም እናውቃለን ስንጀምርም እንዲያ ነበር ዛሬም ያው ነው። 

ፈተና ሳይኖር ደግሞ መንፈሳዊ አገልግሎት ሊቀጥል አይችልም ይህ ከሰው ብቻ የሚመነጭ ሳይሆን ከራሱ ከጥሩ ነገር ጠላት ከዲያብሎስም የሚመነጭ ነው። ፈተና ምንም አያስፈልግም ካልን የምንሠራው መንፈሳዊ አገልግሎት /ሥራ/ አይደለም ማለት ነው። ስለዚህ የምንሠራው ሥራ መንፈሳዊ ሥራ ነው። መንፈሳዊ ሥራ ደግሞ የሠይጣን ፈተና አለበት። ሥራችንን እንድናቆም ይፈልጋል እስከ ዛሬ ሲታገለን ቆይቋል ዛሬም ደግሞ አጠንክሮ ይታገላል። የበለጠ በጠነከርን ቁጥር የበለጠ ፈተና ይመጣል። ይሄንን ከቅዱሳት መጻሕፍት እናውቃለን ከታሪክ እናውቀዋለን። ከራሳችንም ሕይወት እናውቃለን። በመሆኑም ይሄ ፈተና እስከመቼ ይቀጥላል ካልን፥ አገልግሎታችን አስከቀጠለ ድረስ ይቀጥላል። ፈታኞቹ ወደ ልቦናቸው ተመልሰው ወደ ሥራ ሲገቡ ሠይጣን ሌላ ፈታኝ ያዘጋጃል። አባ ሠረቀ እንኳን ቢያቆሙና ወደ ትክክለኛው የቤተ ክርስቲያን አገልግሎት ቢመለሱ ሰይጣን ሌላ ፈታኝ ያመጣል ይሄ እስከ ክርስቶስ ምጽአት ድረስ የማይቀር ጉዞ ነው። ስለዚህ ይሄ መቼ ይቆማል ብለን የሚቆምበትን ቀን ተስፋ አናደርግም፤ የሚቆመውም መንፈሳዊ አገልግሎታችንን ስናቆም ነው። ስለዚህ ይሄንን ይዘን እንሄዳለን።

ነገር ግን ይሄ ፈተና የሚቀጥል ነው ብለን ችላ ማለት የለብንም። በእኛ በኩል ማድረግ የሚገባንን በሙሉ እናደርጋለን “ከእንግዲህ ከማኅበሩ ጋር አልሠራም” የሚል ደብዳቤ ጽፈዋል። “ማኅበሩ የሚሰጠውን ደብዳቤ በሙሉ አልመልስለትም” በማለት ለጠቅላይ ቤተ ክህነት አቤቱታ አቅርበዋል። ይሁን እንጂ አሁንም ማኅበሩ ጥያቄ ያቀርብላቸዋል። እንደማይመልሱም እየታወቀ ትክክለኛ መንገድ ተከትለን እንሄዳለን። ስንመልስላቸው አልተመለሰልንም ብለው ያቀርባሉ እኛም መልሰን እንመልስላቸዋለን። ሁል ጊዜም ግን ለፋይል እንዲመቻቸው ‹‹አልተመለሰልኝም፣ አልታዘዘኝም፣ አልታዘዘኝም›› ነው የሚሉት። እኛ ግን እየታዘዝን፣ እየታዘዝን እንቀጥላለን። እየተቀበልን መፈጸም የሚገባንን እንቀጥላለን። 

አሁን በመሠረቱ ማኅበረ ቅዱሳን ከፍተኛ ገንዘብ እንዳለው ያስወራሉ። የምዕመኑ ገንዘብም ወደዚህ እንደመጣ አድርገው ይናገራሉ። ስለዚህ የመቀራመትና የመውሰድ ስሜት ነው ያላቸው። ማኅበረ ቅዱሳን ገንዘብ የለውም፤ አንዳንድ ዕቅዶችንም እየሰረዘ ነው የሚሠራው ባንክ አካውንቱን አያሳውቅም ይላሉ እንጂ ባንክ አካውንቱን ማየት ይችላሉ። በማኅበረ ቅዱሳን በየወሩና በየሁለት ወሩ በምትሰበስብ ገንዘብ ሥራ እየሠራን ነው የምንቀጥለው። እዚህ የሚሰጠው አገልግሎት በአበልና በደመወዝ የተንበሸበሹ አድርገው ነው የሚያስቡት። ይሄ በሙሉ ግን የተሳሳተ ነው። ስለዚህ ከፍተኛ ገንዘብ አለና ያንን ገንዘብ እንቆጣጠራለን የሚል ስሜት እንዳለ አንዳንድ ፍንጮችን እያየን ነው። ስለዚህ ማኅበረ ቅዱሳን ጋር ያለውን ግልጽ አሠራር አሁንም የበለጠ ግልጽ እያደረገ አባቶችም እንዲረዱ እያደረግን፥ ለቅዱስ ሲኖዶስም እያሳወቅን እንቀጥላለን። በተለይም በአሁኑ ሲኖዶስ የመናፍቃንን እንቅስቃሴ ጉዳይ እና ለዚህ ተባባሪ ሆነው እየሠሩ ያሉትን የመምሪያው ኃላፊዎች ጉዳይ አጀንዳ ሆኖ እልባት መስጠት አለበት ብለን እናስባለን። ውሳኔ ያገኛሉ ብለንም እናስባለን። ማኅበረ ቅዱሳንም በተሰጠው መተዳደሪያ ደንብ መሥራት አለመሥራቱን ቅዱስ ሲኖዶስ ራሱ ማረጋገጥ የሚችለው ጉዳይ ነው። በየሀገረ ስብከቱ ከአባቶች ጋር ነው የምንሠራው አየር ላይ አይደለም እየሠራን ያለነው። የማኅበሩን አገልግሎት ብፁዓን አባቶች አቅም አላቸው ሥልጣኑም የቅዱስ ሲኖዶስ ነው። መወሰን የሚችለውም ቅዱስ ሲኖዶስ ነው ብለን እናምናለን።
•    በመጨረሻም ቀረ የሚሉት ካለ?

በሚጻፉና በሚባሉ በሚሰራጩ የውሸት ፕሮፓጋንዳዎችና የስም ማጥፋት ዘመቻዎች ምእመናንም ሆኑ የማኅበሩ አባላት መረበሽ የለባቸውም። የፈለገ ያህል ፈተና ቢመጣ ደግሞ ፈተና እንደሚኖር ማወቅ አለባቸው፡፡ ከፈተና የራቀ አገልግሎት የለም። ስለዚህ የሚነሡትን ነገሮች በሙሉ በመከታተልና በማወቅ ለግንዛቤ ከመያዝ ባሻገር፥ ሥራን ለማቆም አገልግሎትን ለመተው ማሰብ የለባቸውም። በእልህም ደግሞ ወደ ሌላ መጥፎ ተግባር ውስጥ መግባት የለባቸውም፤ ይገባሉ ብዬም አልጠብቅም፡፡ ሁል ጊዜም በትክክለኛና በሕጋዊ መንገድ ቤተ ክርስቲያንን ለማገልገል ዛሬም ወደፊትም ጠንካራ ሆኖ መንቀሳቀስ ይጠበቅባቸዋል። ከዚህ የበለጠ ፈተና ሠይጣን ሊያመጣባቸው ይችላል። ሙሉ በሙሉም የማኅበሩ አገልግሎት በከፍተኛ ሁኔታ የማደናቀፍ ሥራ ሊፈጥር ይችላል ብለን ብናስብ እንኳን ይሄ በሙሉ የሠይጣን ፈተና መሆኑን አውቀን ከመንፈሳዊ አገልግሎታችን ምንጊዜም ቢሆን ወደኋላ ማለት የለብንም። በአጥቢያችን፣ በወረዳችን፣ በሀገረ ስብከታችን ቤተ ክርስቲያንን በማገልገል ትጉዎች መሆን ነው ያለብን፤ ለስም አይደለም የምንሠራው፣ ለማኅበረ ቅዱሳንም አይደለም የምንሠራው ለቤተ ክርስቲያናችን ነው። የምንሠራው በተጨማሪም አጽራረ ቤተ ክርስቲያንን ነቅተን መጠበቅና ምላሽ ለመስጠት ዝግጁዎች መሆን ይጠበቅብናል:: ይሄን ነው ለማስተላለፍ የምወደው፡፡
•    እግዚአብሔር ይስጥልን፡፡

እኔም እግዚአብሔር ይስጥልኝ፡፡

ሆሣዕና (የዐቢይ ጾም 8ኛ ሳምንት)

የሆሣዕና ዋዜማ /የቅዳሜ ማታ/ መዝሙር (ከጾመ ድጓ)
ወእንዘ ሰሙን በዓለ ፋሲካ ቀርቡ አርዳኢሁ ለአምላከ ጽድቅ ኀበ ደብረ ዘይት ሙራደ ዓቀብ ሀገረ እግዚአብሔር ወተቀበልዎ ሕዝብ ብዙኃን አዕሩግ ወሕፃናት ነሢኦሙ አዕፁቀ በቀልት እንዘ ይብሉ ሆሣዕና በአርያም ተፅዒኖ ዲበ ዕዋል ቦአ ሀገረ ኢየሩሳሌም በትፍሥሕት ወበሐሴት ይሁቦሙ ኃይለ ወሥልጣነ።

ትርጉም“የፋሲካ በዓል ሳምንት ሲቀረው የእውነተኛ አምላክ ደቀ መዛሙርት የእግዚአብሔር ሀገር ወደ ሆነችው ደብረ ዘይት ቁልቁለት ሲደርሱ ወደ እርሱ ለመታዘዝ ቀረቡ፤ ብዙ ሕዝብ፣ ልጆችና ሽማግሌዎችም የዘንባባ ዝንጣፊ ይዘው ሆሣዕና በአርያም እያሉ ተቀበሉት፣ በአህያ ተጭኖ ኃይልና ሥልጣንን ይሰጣቸው ዘንድ በፍጹም ደስታ ኢየሩሳሌም ገባ” ማለት ነው።

 
መልዕክታት
ዕብ.8÷1-ፍጻ. ከተናገርነውም ዋናው ነገር ይህ ነው፤ በሰማያት በግርማው ዙፋን ቀኝ የተቀመጠ እንዲህ ያለ ሊቀ ካህናት አለን። (ተጨማሪ ያንብቡ)
 

1ኛ ጴጥ.1÷13 ስለዚህ የልቡናችሁን ወገብ ታጥቃችሁና ነቅታችሁ ኑሩ፤ ኢየሱስ ክርስቶስም ሲገለጥ የምታገኙትን ጸጋ ፈጽማችሁ ተስፋ አድርጉ፡፡  (ተጨማሪ ያንብቡ)
ግብረ ሐዋርያት
የሐዋ.8÷26-ፍጻ. የእግዚአብሔር መልአክም ፊልጶስን ተናገረው፤ እንዲህም አለው÷ “በቀትር ጊዜ ተነሣና በደቡብ በኩል ከኢየሩሳሌም ወደ ጋዛ በሚያወርደው በምድረ በዳው መንገድ ሂድ፡፡” ተነሥቶም ሄደ፡፡  (ተጨማሪ ያንብቡ)
 
ምስባክ
 

መዝ.80÷3 “ንፍሑ ቀርነ በዕለተ ሠርቅ፡፡ በእምርት ዕለት በዓልነ፡፡ እስመ ሥርዓቱ ለእስራኤል ውእቱ፡፡”

 

ትርጉም፦ በመባቻ ቀን በታወቀችው በዓላችን ቀን መለከትን ንፉ፤ ለእስራኤል ሥርዐቱ ነውና÷

ወንጌል
ዮሐ.12÷1-11 ፋሲካ ከሚውልበት ከስድስተኛው ቀን አስቀድሞ ጌታችን ኢየሱስ ከሙታን ያስነሣው አልዓዛር ወደ ነበረበት ወደ ቢታንያ መጣ፡፡ (ተጨማሪ ያንብቡ)
 
የሌሊተ ሆሣዕና መዝሙር (ከጾመ ድጓ)
ወ።

ትርጉም፦“።

 
 
ምስባክ
 

መዝ.117÷26 “ቡሩክ ዘይመጽእ በስመ እግዚአብሔር ባረክናክሙ እምቤተ እግዚእብሔር፡፡ እግዚእብሔር እግዚእ አስተርአየ ለነ፡፡”

 

ትርጉም፦ በእግዚአብሔር ስም የሚመጣ ቡሩክ ነው፤ ከእግዚአብሔር ቤት መረቅናችሁ፡፡ ጌታ እግዚአብሔር ተገለጠልን፤

ወንጌል
ሉቃ.19÷1-11 ጌታችን ኢየስስም ወደ ኢያራኮ ገብቶ በዚያ ያልፍ ነበር፡፡ እነሆ÷ የቀራጮች አለቃ ስሙ ዘኬዎስ የተባለ አንድ ሰው ነበር፤ (ተጨማሪ ያንብቡ)
 
ዘነግህ/በጊዜ ዑደት ውስተ ቤተ መቅደስ።/መዝሙር(ከጾመ ድጓ)
ወ።

ትርጉም፦“።

 
 
ምስባክ
 

መዝ.121፥1 “ተፈሣሕኩ እስመ ይቤሉኒ ቤተ እግዚእ ብሔር ነሐውር። ወቆማ እገሪነ ውስተ አዕፃድኪ ኢየሩሳሌም ኢየሩሳሌምሰ ሕንፅት ከመ ሀገር።”

 

ትርጉም፦ ወደ እግዚአብሔር ቤት እንሂድ ስላሉኝ ደስ አለኝ፡፡ ኢየሩሳሌም ሆይ÷ እግሮቻችን በአደባባዮችሽ ቆሙ፡፡ ኢየሩሳሌምስ እንደ ከተማ የታነጸች ናት፡፡

ወንጌል
ማቴ. 20፥29-ፍጻ. ከኢያሪኮም በወጣ ጊዜ ብዙ ሰዎች ተከተሉት፡፡ እነሆ÷ ሁለት ዕውራን በመንገድ አጠገብ ተቀምጠው ነበር፤ (ተጨማሪ ያንብቡ)
ምስባክ
መዝ.147÷1 ትሴብሖ ኢየሩሳሌም ለእግዚአብሔር፡፡ ወሰብሒዮ ለአምላክኪ ጽዮን እስመ አጽንዐ መናስግተ ኆኃትኪ፡፡
 

ትርጉም:- ኢየሩሳሌም ሆይ÷ እግዚአብሔርን አመስግኚ÷ ጽዮንም ሆይ÷ አምላክሽን አመስግኚ፤ የደጆችሽን መወርወሪያ አጸንቶአልና÷ ልጆችሽንም በውስጥሽ ባርኮአልና፡፡
 
ወንጌል
ማር. 10፥46-ፍጻ. ወደ ኢያሪኮም ገባ፤ ከኢያሪኮም በወጣ ጊዜ፥ ደቀ መዛሙርቱ ከእርሱ ጋር ነበሩ፤ ብዙ ሰውም ነበረ፤ (ተጨማሪ ያንብቡ)
ምስባክ
መዝ.117፥27 ግበሩ በዓለ በትፍሥሕት በኃበ እለ ያስተሐምምዎ
 
ትርጉም፦ ጌታ እግዚአብሔር ተገለጠልን፤ እስከ መሠዊያው ቀንዶች ድረስ በሚያስተነትኑበት በደስታ በዓልን አድርጉ፡፡
ወንጌል
ሉቃ. 18፥35-ፍጻ. (ተጨማሪ ያንብቡ)
ምስባክ
መዝ. 67፥34
 
ትርጉም፦
ወንጌል
ማቴ. 9፥26-ፍጻ. (ተጨማሪ ያንብቡ)
 
መዝሙር ዘምዕዋድ አርእዩነ ፍኖቶ
አርእዩኖ ፍኖቶ ወንሑር ቤቶ እስመ እምጽዮን ይወጽእ ሕገ ወቃለ እግዚአብሔር እምኢየሩሳሌም ንሣለማ ለመድኃኒትነ በትፍሥሕት ተቀበልዋ ለታቦት እስመ ዋካ ይእቲ ወብርሃን

ትርጉም“።

 
መዝሙር ሰመያ አብርሃም
ሰመያ አብርሃም ወይቤላ ዛቲ ዕለት በዓለ እግዚአብሔር ንፍሑ ቀርነ በዕለት ሠርቅ በዕምርት ዕለት በዓልነ ሶበ ተዘከርናሃ ለጽዮን

ትርጉም“።

 
መዝሙር ወትቤ ጽዮን
ወትቤ ጽዮን አርኅው ሊተ አናቅጸ ይባኡ ሕዝብ ብዝዙኃን ወያዕትቱ ዕብነ እምፍኖት ለንጉሥ  ለወልደ ዳዊት ንጉሦሙ ለእስራኤል ውእቱ ይብሉ ሆሣዕና በአርያም

ትርጉም“።

 

መዝሙር ባርኮ ያዕቆብ

ባረኮ ያ ዕቆብ ለይሁዳ ወልዱ ወይቤሎ ሀሎ ንጉሥ ዘይወጽ እ እምኔከ ዘየሐጽብ በወይን ልብሶ ወበደመ አስካል ሰንዱኖ ንጉሦሙ ውእቱ ይብሉ ሆሣዕና በአርያም

ትርጉም“።

 
መልዕክታት
ዕብ. 9÷11-ፍጻ. ክርስቶስ ግን ለምትመጣይቱ መልካም ነገር ሊቀ ካህናት ሆኖ÷ የሰው እጅ ወደ አልሠራት÷ (ተጨማሪ ያንብቡ)
 

1ኛጴጥ.4÷1-12 ክርስቶስ ስለ እኛ በሥጋው ከተሰለቀ÷ እናንተም ይህቺን ዐሳብ ጋሻ አድርጋችሁ ኑሩ፤ በሥጋዉ መከራ የተቀበለ ከኀጢአት ድኖአልና፡፡ (ተጨማሪ ያንብቡ)
ግብረ ሐዋርያት
ሐዋ.28÷11-ፍጻ. ከሦስት ወር በኋላም በዚያች ደሴት ወደ ከረመችው ወደ እስክንድርያ መርከብ ወጣን፤ በዚያች መርብ ላይም የዲዮስቆሮስ ምልክት ነበረባት፤ ይኸውም “የመርከበኞች አምላክ” የሚሉት ነው፡፡ (ተጨማሪ ያንብቡ)
 
ምስባክ
 

መዝ.8÷2 “እምአፈ ደቂቅ ወሕፃናት አስተዳሎከ ስብሓተ፡፡ በእንተ ጸላዒ፡፡ ከመ ትንሥቶ ለጸላዒ ወለገፋዒ፡፡”

 

ትርጉም፦ ከሕፃናትና ከሚጠቡ ልጆች አፍ ምስጋናን አዘጋጀህ፡፡ ስለ ጠላት÷ ጠላትንና ግፈኛን ታጠፋው ዘንድ፡፡

ወንጌል
ዮሐ.5÷11-31 እርሱም መልሶ÷ “ያዳነኝ እርሱ፡- አልጋህን ተሸክመህ ሂድ አለኝ” አላቸው፡፡ አይሁድም÷ (ተጨማሪ ያንብቡ)
 
ቅዳሴ
Normal 0 false false false EN-US X-NONE X-NONE MicrosoftInternetExplorer4 Normal 0 false false false EN-US X-NONE X-NONE

ቅዳሴ ዘጎርጎርዮስ

መዝሙሩንና ምንባባቱን በዜማ ለማዳመጥ ይህን ይጫኑ

ዐሥራ አምስተኛው ዙር ሐዋርያዊ የጉዞ መርሐ ግብር በተሳካ ሁኔታ ተጠናቀቀ፡፡

በደረጀ ትዕዛዙ
ማኅበረ ቅዱሳን የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያንን ትክክለኛ አስተ ምህሮ ለምእመናን ለማዳረስ ከሚጠቀምባቸው መርሐ ግብሮች አንዱ የሆነውና በደቡብ ኢትዮ ጵያ ቦረና ጉጂ ሊበን ዞኖች ሃገረ ስብከት የተካሔደው  የአሥራ አምስተኛው ዙር ሐዋርያዊ ጉዞ በተሳካ ሁኔታ ተጠናቀቀ፡፡ እንዲህ ያለ መርሐ ግብር በተከታታይ ሊካሔድ እንደሚገባ የአካባቢው ምእመናን ቿይቀዋል፡፡
በማኅበሩ ትምህርትና ሐዋርያዊ አገልግሎት ዋና ክፍል አዘጋጅነት ከየካቲት 11- 20 2003 ዓ.ም ድረስ የተካሔደው ይኸው መርሐ ግብር ቦረና ጉጂ ሊበን ዞኖች ሀገረ ስብከት የሚገኙ አምስት ከተሞችን የሸፈነ መሆኑን የመርሐ ግብሩ አስተባባሪ ዲ/ን ምትኩ አበራ ተናግረዋል፡፡

አራት መምህራንና አሥራ ሰባት ዘማሪያንን እንዲሁም ሌሎች አባላትን ያካተተው ይኸው የልኡካን ቡድን ይዞት ከተነሣው ተልእኮ አንጻር የተሻለ አገልግሎት ሰጥቶ መመለሱን የገለጡት አስተባባሪው በዚህም ምእመናኑ እጅግ ተደስተዋል ብለዋል፡፡

በሐዋርያዊ ጉዞው ትክክለኛውን የቤተክ ርስቲያን ትምህርት እና ዝማሬ ወደ ምእመናኑ ማድረስ ዋና ዓላማው አድርጎ የተንቀሳቀሰው ይኸው የልኡካን ቡድን፤ በሀገረ ስብከቱ በሚገኙ ክብረ መንግሥት፣ ሻኪሶ፣ ዋደራ፣ ቦሬ እና ነገሌ ቦረና ከተሞች በሚገኙ አምስት አብያተ ክርስቲያናት እንዲሁም በምእምናን ጥያቄ መሠረት ከዕቅድ በላይ በሁለት አጥቢያ አብያተ ክርስቲያንም አገልግሎቱን ሰጥቷል ብለዋል፡፡ በዚህም የሐዋርያዊ ጉዞው ቡድን ከሕዝቡ ተቀባይነትን፣ ከበሬታንና ፍቅርን አግኝቶ መመለሱን አስረድተዋል፡፡

ትምህርተ ወንጌሉ በአማርኛና በኦሮምኛ ቋንቋዎች መሰጠቱ ምእመናን ቃለ እግዚአብሔርን በአግባቡ እንዲረዱ ያስቻለ ከመሆኑም በተጨማሪ የልኡካን ቡድኑ አባላት የሆኑ ካህናት በቅዳሴ እና በዓመታዊ ክብረ በዓል ወቅት የቤተ መቅደስ አገልግሎት መስጠታቸው አገልግሎቱን ይበልጥ የተሳካ እንዲሆን አግዟል ብለዋል፡፡

የልኡካን ቡድኑ ከቤተክርስቲያኒቱ የስብከተ ወንጌል ሐዋርያዊ ተልእኮ መምሪያ ፈቃድ ይዞ በሕጋዊነት ተንቀሳቅሷል፡፡ ሆኖም በአንዳንድ ከተሞች በዓላማቸው የተሐድሶ እንቅ ስቃሴውን ለማራመድ በሚጥሩ ግለሰቦች መርሐ ግብሩን የማደናቀፍ አዝማሚያ አጋጥሞት አንደነበር ዲያቆን ምትኩ አበራ ተናግረዋል፡፡ ይሁንና በቤተክርስቲያኒቷ ሥርዓትና መመሪያ መሠረት የሚካሔድ ሕጋዊ አገልግሎት ስለሆነ የፈቃድ ወረቀቱን ለሕጋዊ አካላት በማሳየት እና ከየደብሩ ሓላፊዎች እና ከምእመናኑ ጋር በመነጋገር መርሐ ግብሩ ሳይስተጓጎል ከተጠበቀው በላይ የተሳካ ሆኖ መጠናቀቁን አብራርተዋል፡፡

መርሐ ግብሩ በተካሔደባቸው አካባቢዎች ከቤተክርስቲያን ሥርዓትና መመሪያ ውጪ የሚንቀሳቀሱ ሰባክያንና ዘማሪያን ስፍራውን ደጋግመው በመጎብኘታቸው ትክክለኛውን የቤተክር ስቲያኒቱን አስተምህሮ ሳያገኙ መቆየታቸውን የአካባቢው ምእመናን ለልኡካን ቡድኑ አባላት ሲገልጡ እንደነበር የተናገሩት ዲ/ን ምትኩ፤ መርሐ ግብሩ በተከታታይ ሊካሔድ እንደሚገባ መጠየቃቸውንም አስረድተዋል፡፡
ማኅበሩ በእነዚህ አካባቢዎች መዋቅሩን በማጠናከር የቅድስት ቤተክርስቲያንን ሥርዓትና መመሪያ አክብረው ከሚንቀሳቀሱ መምህራነ ወንጌል እና ዘማሪያን ጋር በመተባበር ደጋግሞ ወደ ስፍራው ሐዋርያዊ ጉዞ ማድረግ ይገባል፡፡ በዚህ አካባቢ ትኩረት ሰጥቶ በተከታታይ የተጠናከረ አገልግሎት መስጠትና ትምህርተ ወንጌል የተጠማውን ሕዝብ በማስተማር የቅድስት ቤተክርስቲያንን ተልዕኮዋን ይበልጥ ውጤታማ ለማደረግ መነሣሣት እንደሚያስፈልግ ዲ/ን ምትኩ ተናግረዋል፡፡

 
 /ምንጭ፦ ስምዐ ጽድቅ ከመጋቢት 1-15 ቀን 2003 ዓ.ም/
kidusuraeal.jpg

የደብረ ጽጌ ቅዱስ ዑራኤል ቤተ ክርስቲያን አካባቢ ወጣቶች መንፈሳዊ የአገልግሎት ማኅበር ዓመታዊ በዓሉን አከበረ፡፡

በኅሩይ ባየ
በአዲስ አበባ ሃገረ ሰkidusuraeal.jpgብከት በደብረ ጽጌ ቅዱስ ዑራኤል አጥቢያ ዐሥራኹለት ቀበሌዎች የሚኖሩ ወጣት የቤተ ክርስቲያን ልጆች የካቲት 20 ቀን 2003 ዓ. ም በደብረ ፅጌ ቅዱስ ዑራኤል ቤተ ክርስቲያን የሰንበቴ አዳራሽ መንፈሳዊ የአገልግሎት ማኅበራቸው የተመሠረተበትን አንደኛ ዓመት አከበሩ፡፡ 
ቁጥራቸው ከአንድ ሺሕ በላይ የሆኑት እነዚህ ወጣቶች በአንድ ዓመት ቆይታቸው በየወሩ በተለያዩ አዳራሾች እየተሰበሰቡ ኦርቶዶክሳዊ የሃይ ማኖት ትምህርት ሲማሩ መቆየታቸውን የማኅበሩ ሰብሳቢ ወጣት ተስፋዬ አዳነ ገልጧል፡፡
 
«የቤተ ክርስቲያንን ሥርዓት በጠበቀና በተደራጀ መልኩ፤ ትምህርተ ሃይማኖትን ለመማርና በመልካም ሥነ ምግባር ቅድስት ቤተ ክርስቲያንን ለማገልገል መዋቅርና አሠራሯን ጠብቆ በቤተ ክርስቲያን ቅጽር ግቢ መሰባሰብ የበለጠ ጠቀሜታ እንዳለው ይታመ ንበታል፡፡ ስለዚሀ በአጥቢያችን በደብረ ጽጌ ቅዱስ ዑራኤል ቤተ ክርስ ቲያን እየተገኘን መሰብሰብ ጀምረናል፡፡» ሲል የገለጠው ወጣት ተስፋዬ አዳነ፤ ወጣቶቹ በየሳምንቱ በአቅራቢያቸው ቤተ ክርስቲያን እየተገኙ ስብከተ ወንጌል መርሐ ግብሮችን እንደሚከታተሉና በወር አንድ ጊዜ ደግሞ በደብረ ጽጌ ቅዱስ ዑራኤል ቤተ ክርስቲያን አጠቃላይ ጉባኤያቸውን በማካሔድ የመዝሙር ጥናት እንዲሁም የመጽሐፍ ቅዱስ ትምህርት እንደሚማሩ ተናግሯል፡፡

ማኅበሩ በ2002 ዓ. ም ተመሥርቶ አገልግሎቱን መስጠት ከጀመረበት ጊዜ አንሥቶ በርካታ መንፈሳዊ ተግባ ራትን እያከናወነ ይገኛል፡፡ ከተከናወኑት ተግባራት መካከል ጥቂቶቹ በእስር ቤት ያሉ ወገኖቻችን በዓል ጥምቀትን አስበው እንዲውሉ የምሣ ግብዣ ማዘጋጀት፤ የቤተ ክርስቲያን ዓመታዊ በዓላት ኦርቶዶክሳዊ ትውፊቶችን ሳይለቁ እንዲከበሩ የግንዛቤ ማስጨ በጪያ ትምህርት ማካሔድ፤ ወጣቶች በቤተ ክርስቲያን ሥርዐት መሠረት ታቦተ ሕጉን አጅበው የንግሥ በዓላትን እንዲያከብሩና የሚጠበቅባቸውን አገል ግሎት እንዲያበረክቱ በማድረግ ካከናወኗቸው ተግባራት ጥቂቶች እንደሆኑ በዕለቱ የቀረበው ሪፖርት ያስረዳል፡፡

ማኅበሩ በቀጣዩ የሥራ ጊዜ ካቀዳቸው ተግባራት ዋናዋናዎቹ፤ በቤተ ክርስቲያናችን የተቀጣጠለውን ውጫ ዊና ውስጣዊ ፈተና ለመቋቋም ዋናው መሣሪያ ጸሎት ስለሆነ በሳምንት አንድ ቀን የማኅበር ጸሎት ማድረስ፤ በተጀመረው የዐቢይ ጾም ወራት እያንዳንዱ የማኅበሩ አባል ቁርሱን ለነዳያን እንዲሰጥ ማድረግ፤ በምግብና በልብስ እጦት ምክንያት ከእናት ቤተ ክርስቲያናቸው ወደ ሌላ የእምነት ተቋም እንዳይፈልሱ አሳዳጊ አልባ የሆኑ ሕፃናትን እና ጧሪ ያጡ አረጋውያንን በግልና በቡድን መርዳት፤ በትምህርተ ሃይማኖት እውቀት ማነስ ምክንያት ወጣቶች በነጣቂ ተኩላ እንዳይወሰዱ ከአጥቢያቸው የሰበካ ጉባኤ እና ከሰንበት ትምህርት ቤት ጋር በመተባበር የቤተ ክርስቲያንን ትምህርተ ሃይማኖት ሥርዐት፣ ታሪክና ትውፊት ትምህርቶች እንዲከታተሉ ሁኔታዎችን ማመቻቸት እና በቤተ ክርስቲያን ከፍተኛ አስተዋጽኦ ያበረከቱ ደጋግ አባቶችን በዓለ ልደታቸውን እና ዕረፍታቸውን ማክበር በሁለት ወር አንድ ጊዜ የሚታተም መንፈሳዊ መጽሔት ማዘጋጀት ዋና ዕቅዳቸው መሆኑን ወጣት ተስፋየ አዳነ ገልጧል፡፡

 
/ምንጭ፦ ስምዐ ጽድቅ ከመጋቢት 1-15 ቀን 2003 ዓ.ም/