Arega_42_X_30_Ca__q100

የሰለሞን ምቅናይ ምስል ወድምጽ /ቪሲዲ/ ተመረቀ

ኅዳር 6/2004 ዓ.ም

በፈትለወርቅ ደስታ

Arega_42_X_30_Ca__q100በኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ በሰ/ት/ቤቶች ማደራጃ መምሪያ ማኅበረ ቅዱሳን “የሰለሞን ምቅናይ በተክሌ ዝማሜ በሚል ርእስ የተዘጋጀ ምስል ወድምጽ /ቪሲዲ/ ቅዳሜ ኅዳር 2/2004 ዓ.ም በጠቅላይ ቤተ ክህነት አዳራሽ ተመረቀ፡፡

በምረቃው ላይ ብፁዕ አቡነ ሰላማ የአክሱም ጽዮን ሊቀ ጳጳስ፣ ብፁዕ አቡነ እንድርያስ የደቡብ ጐንደር ሊቀ ጳጳስና ሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያንና ተጋባዥ እንግዶች ተገኝተዋል፡፡

የማኅበሩ ሰብሳቢ ቀሲስ ዶ/ር ሙሉጌታ ስዩም በምረቃው ላይ የመክፈቻ ንግግር ያደረጉ ሲሆን ቤተ ክርስቲያን የራሷ የሆነውን የዜማ፣ የአቋቋም ሥርዓት ጠብቃ በእንዲህ ዓይነት መልኩ ለምእመናን እንዲዳረስ ማኅበሩ የበኩሉን ድርሻ እንደሚወጣና ወደፊትም ከዚህ በተሻለ መልኩ እንደሚሠራ ገልፀዋል፡፡ ብፁዕ አቡነ እንድርያስም በዕለቱ “ምቅናይ” በሚል ርዕስ ሰፋ ያለ ትምህርት ሰጥተዋል፡፡ አያይዘውም ይህ የቤተ ክርስቲያን ቅርስና ሀብት ዜማ ዝም ብሎ የተገኘ ሳይሆን ሊቃውንቱ እድሜያቸውን ሙሉ ሲማሩት የኖሩት መሆኑንና ይህን የቤተ ክርስቲያን ሀብት ደግሞ በእንዲህ ዓይነት መልኩ ለትውልድ የማስረከብ ኃላፊነት የሁሉም የቅድስት ቤተ ክርስቲያን ልጆች ኃላፊነት መሆኑን ተናግረዋል፡፡

298135_242419749145401_100001321341150_593861_1645855864_n

በዕለቱ በየኔታ ተክሌ ሲራክ አማካይነት በተክሌ አቋቋምና ዝማሜ ታሪክ ላይ ጥናታዊ ጽሑፍ የቀረበ ሲሆን ይህ የተክሌ ዝማሜ በደብረ ታቦር ኢየሱስ ገዳም እስከ አሁን ድረስ የተክሌ አቋቋም ጉባኤ ምስክር ሆኖ እንደሚያገለግል ገልጸዋል፡፡

በመጨረሻም ብፁዕ አቡነ እንድርያስ ይህ ጅማሮ ጥሩ መሆኑን ገልፀው ይህ ዝማሜ የሊቃውንቱ ቢሆንም ለእይታ የበቃው በማኅበረ ቅዱሳን አማካይነት መሆኑና ማኅበሩም በዚህ ዙሪያ ከፍተኛ ኃላፊነትን ወስዶ የድርሻውን እየተወጣ እንደሆነ ገልጸው ነገር ግን ገና አልተነካም ወደፊት ብዙ ይጠበቃል ብለዋል፡፡

ቪሲዲው የተዘጋጀው በማኅበረ ቅዱሳን በሙያ አገልግሎት እና አቅም ማጎልበቻ  ክፍል ዘርፍ ፕሮጀክት ተጠንቶና ሊቃውንቱ መክረውበት ነው፡፡

ከትርፍ ነፃ የሆኑ የምስልና የድምጽ ሲዲዎች እንደሚሠራጩ ተገለጠ፡፡

በዲ/ን ኅሩይ ባየ
ቀን 05/03/2004ዓ.ም.

በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን በሰንበት ትምህርት ቤቶች ማደራጃ መምሪያ ማኅበረ ቅዱሳን በኤሌክትሮኒክስ ሚዲያ ክፍል የተዘጋጁ 3 ሺህ የሚሆኑ የምስልና የድምጽ ሲዲዎች ኅዳር 8 ቀን 2004 ዓ.ም በማኅበሩ ጽ/ቤት እንደሚሠራጭ የምክረ ሐሳቡ አስተባባሪ ኢንጂነር ሙሉጌታ ጌትነት አስታወቁ፡፡

ኢንጅነር ሙሉጌታ እንደገለጡት የምስልና የድምጽ ሲዲዎችን ለማግኘትና ለማሠራጨት ምንም ዐይነት ትርፍ ታሳቢ ሳይደረግ የሲዲውን ዋጋ ብቻ በመሸፈን ማግኘት ይቻላል፡፡ በማያያዝም የሥርጭቱ ዋና ዓላማ ስብከተ ወንጌልን በተፋጠነ መንገድ ለምእመናን ማዳረስ ሲሆን በገበያ ላይ የሚገኙት የምስልና የድምጽ ሲዲዎች የምእመናንን ምጣኔ ሀብት የሚጎዱ በመሆናቸው በቀላሉ ቃለ እግዚአብሔር የሚስፋፋበትን መንገድ ለማመቻቸት፣ የተሐድሶ መናፍቃን ስሑት ትምህርቶች በሕዝበ ክርስቲያኑ ሰርገው ስለገቡ ትክክለኛ ኦርቶዶክሳዊ አስተምህሮ ያላቸውን የስብከት ሲዲዎች ምእመናን እንዲያገኙና ስለ ሃይማኖታቸው እንዲያውቁ ለመደገፍ፣ በከተማ የሚኖሩ ጥቂት ምእመናን የመካነ ድር አገልግሎት ተጠቃሚዎች ቢሆኑም አገልግሎቱ ውድና ዝቅተኛ ፍጥነት ስላለው የምስልና የድምጽ ዝግጅቶችን መመልከትና መስማት ስለማይችሉ ችግሩን አስወግዶ ተደራሽነትን ለማስፋፋት እንዲቻልና የቪሲዲ አገልግሎት ከገጠር እስከ ከተማ እየተስፋፋ በመምጣቱ ንጹህ የቤተ ክርስቲያን ትምህርቶችን ለሁሉም እንዲዳረስ ለማድረግ እንደሆነ አስተባባሪው አስገንዝበዋል፡፡

ስርጭቱ እስከ ሦስት ዙር የሚቀጥል ሲሆን በመጀመሪያው ዙር ለአዲስ አበባ ምእመናን ይከፋፈላል፡፡ በሁለተኛውና በሦስተኛው ዙር የሚከናወኑት ስርጭቶች ደግሞ ከአዲስ አበባ ውጭ ወደ ማእከላትና ግንኙነት ጣቢያዎች እንደሚላኩ ለማወቅ ተችሏል፡፡ ስርጭቱን በተመለከተ ራሱን የቻለ ኮሚቴ እንደተዋቀረም ተጠቁሟል፡፡

የምስልና የድምጽ ትምህርቶች የተዘጋጁት በማኅበረ ቅዱሳን የምስልና የድምጽ ክምችት ክፍል በተለያዩ ዘመናት የተቀረጹ የሊቃውንት ትምህርቶች፣ በኤሌክትሮኒክስ ሚዲያ ክፍል በተለያዩ መርሐ ግብሮች የተቀረጹና በአዲስ አበባ ራጉኤል ቤተ ክርስቲያን ሰ/ት/ቤት የተቀረጹ ትምህርቶች እንደሆኑ ተገልጧል፡፡ ዝግጅቱ ከትርፍ ነፃ በሆነ መልኩ ተዘጋጅቶ የሚሠራጭ በመሆኑ ምእመናን በቀላሉ እንዲጠቀሙበት ማኅበሩ ጥሪውን ያስተላልፋል ሲሉ አስተባባሪው አሳስበዋል፡፡

VCD-Advertisment

ታላቅ የቪሲዲ ምርቃት

አዘጋጅ፡- በኢ/ኦ/ተ/ቤተ ክርስቲያን ሰ/ት/ቤቶች ማደራጃ መምሪያ ማኅበረ ቅዱሳን ሙያ  አገልግሎትና አቅም ማጎልበቻ ዋና ክፍል
ቦታ፡-ጠቅላይ ቤተ ክህነት አዳራሽ
ሰዓት፡- ቅዳሜ ኅዳር 02/03/2004 ዓ.ም ከቀኑ 7፡30 ጀምሮ

 

VCD-Advertisment

commitiee

30ኛው አጠቃላይ ሰበካ መንፈሳዊ ጉባኤ ተጀመረ

{gallery count=1 width=350 height=300 counter=1 links=0 alignment=center animation=3000}smg30{/gallery}

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን 30ኛው መደበኛ መንፈሳዊ ጉባኤ ጥቅምት 7 ቀን 2004 ዓ.ም በመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት የስብከተ ወንጌል አዳራሽ ከጠዋቱ 3 ሰዓት በብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ጳውሎስ ጸሎተ ቡራኬ ተጀምሯል፡፡

 

የ48ቱ አህጉረ ስብከት ሊቃነ ጳጳሳት በከፊል የተገኙ ሲሆን ሁሉም የሀገር ውስጥ ሥራ አስኪያጆች ፣የመንበረ ፓትሪያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት የመምሪያ ሓላፊዎች ፣በሀገር ውስጥና በውጭ ሀገር የሚገኙ የአድባራትና ገዳማት አስተዳዳሪዎች ፣ በኢትዮጵያ የስብከተ ወንጌልና ሐዋርያዊ ተልዕኮ መምሪያ ፣ የሕፃናትና ቤተሰብ ጉዳይ ድርጅት፣ የልማትና ክርስቲያናዊ ተራድኦ ኮሚሽን ሓላፊዎች የጉባኤው ተሳታፊዎች ናቸው።

የመንበረ ፓትርያርክ ቅድስተ ቅዱሳን ማርያም ገዳም ካህናት “ስምዐነ አምላክነ ወመድኃኒነ ተስፋሆሙ ለኩሎሙ አጽናፈ ምድር” የሚለው የዳዊት መዝሙር ተሰብኮ “በምድር የምታስሩት በሰማይ የታሰረ ይሆናል በምድርም የምትፈቱት በሰማይ የተፈታ ይሆናል፡፡…. ሁለት ወይም ሦስት በስሜ በሚሰበሰቡበት በዚያ በመካከላቸው እሆናለሁና” የሚለው የማቴዎስ ወንጌል ምዕራፍ 18 ቁጥር 18 በቅዱስነታቸው ተነቧል፡፡

 

ቅዱስነታቸው በጸሎተ ወንጌል ጉባኤውን ባርከው ከከፈቱ በኋላ በሰጡት ቃለ ምእዳን ሰው መግባባት የሚችለው እግዚአብሔር በሰጠው አእምሮ ሲጠቀምበትና በፈሪሃ እግዚአብሔር ሲኖር ነው። ፈሪሃ እግዚአብሔር ካለ ሰላም፣ ፍቅር፣ መግባባት፣ መዋደድና መከባበር ይኖራል ብለው በሰላማዊ መንገድ ሓላፊነትን መወጣት እንዲገባ አሳስበዋል፡፡

ቅዱስ ፓትርያርኩ አያይዘው በ2003 ዓ.ም በሞት የተለዩንን ብፁዕ አቡነ በርናባስን፣ ብፁዕ አቡነ ይስሐቅንና ብፁዕ አቡነ ሚካኤልን በጸሎት እናስባቸው ብለው ጸሎት አድርሰዋል፡፡

 

ሊቀትጉሃን ኃይለ ጊዮርጊስ ዳኜ፣ መጋቤ ሰናያት አሰፋ ስዩም፣ ሊቀ ስዩማን ራደ አስረስ፣ ንቡረ እድ ተስፋዬ ተወልደና መጋቤ ሐዲስ ይልማ ቸርነት የአቋም መግለጫ ረቂቅ እንዲያዘጋጁ ብፁዕ አቡነ ፊልጶስ ለጉባኤው አቅርበው ጉባኤው የተመረጡትን አርቃቂዎች በሙሉ ድምጽ አሳልፈዋል፡፡commitiee

 

ከረፋዱ 4 ሰዓት ጀምሮ ለ45 ደቂቃ ያህል የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ጽ/ቤት አጠቃላይ ሪፓርት በብፁዕ አቡነ ፊልጶስ የጠቅላይ ቤተ ክርህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ፣ የኢሉባቡርና ጋምቤላ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስና በንቡረ እድ ኤልያስ አብርሃ የጠቅላይ ቤተ ክህነት ምክትል ሥራ አስኪያጅ ቀርቧል፡፡ ከመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ሪፖርት ቀጥሎ የትግራይ ማዕከላዊ ዞን /አክሱም/ ሀገረ ስብከት ሪፖርት መቅረብ የነበረበት ቢሆንም የጋምቤላ ሀገረ ስብከት ሥራ አስኪያጅ ለሌላ ተልእኮ ወደ ሱዳን ሀገረ ስብከት መሔድ እንዲችሉ ፈቃድ ጠይቀው ቅድሚያ ሪፖርታቸውን አቅርበዋል፡፡

 

በጠዋቱ መርሃ ግብር የትግራይ ማዕከላዊ ዞን፣ የሲዳማ፣ የሰሜን ጎንደር፣ የምሥራቅ ሀረርጌ፣ ሀገረ ስብከት ሪፖርት ቀርቧል፡፡ ከሰዓት በኋላ በተያዘው መርሃ ግብር ከቀኑ 8 ሰዓት እስከ 11፡30 ድረስ የጅማ ዞን ሀገረ ስብከት፣ በትግራይ ክልል ሀገረ ስብከት የመቀሌ፣ የኢሊባቡር፣ የድሬዳዋ፣ የጋሞጎፋ፣ የሰሜን ወሎ፣ የባሌ፣ የደቡብ ጎንደርና የምሥራቅ ወለጋ አህጉረ ስብከት ሪፖርት ቀርቧል፡፡

 

ረቡዕ ጥቅምት 8 ቀን 2004 ዓ.ም ከጠዋቱ 3 እስከ 6፡30 በነበረው መርሐ ግብር የአርሲ፣ የትግራይ ምሥራቅ /አዲግራት/፣ የምዕራብ ጎጀም፣ የከፋ ቦንጋ፣ የሰሜን ሸዋ፣ የአሶሳና የደቡብ ወሎ ሀገረ ስብከት ሪፖርት ቀርቦ እንዳበቃ የቆሜ አቋቋም ሊቃውንት ወረብ አቅርበዋል፡፡

 

በሊቃውንቱ የቀረበው ወረብ እንደተጠናቀቀ የምሥራቅ ሸዋ ሀገረ ስብከት ፣ የምሥራቅ ጎጃም፣ የምዕራብ ሐረርጌና የትግራይ ደቡባዊ ዞን /ማይጨው/ አህጉረ ስብከት ሪፖርት በንባብ ተሰምቷል፡፡

 

ከሰዓት በኋላ በተያዘው መርሃ ግብር የደቡብ ኦሞ፣ የሰሜን ምዕራብ ሸዋ የሰላሌ ሀገረ ስብከት የሐዲያና ስልጤ፣ የዋግ ሕምራ፣ የምዕራብ ሸዋ፣ የአፋር፣ የአዊ ዞን፣ የሶማሊያ፣ የምዕራብ ወለጋ፣ የትግራይ ሰሜናዊ ምዕራብ ዞን ሽሬ ሀገረ ስብከትና የትግራይ ሰሜናዊ ምዕራብ ዞን ሽሬ ሀገረ ስብከትና የጉራጌ ሀገረ ስብከት ሪፖርት ከቀረበ በኋላ ውይይት ተካሒዷል፡፡

 

30 ዓመት ያስቆጠረው የሰበካ መንፈሳዊ ጉባኤ ካሳለፈው ረዥም ጉዞ ጋር ሲነጻጸር የሚጠበቅበትን ውጤት እያስመዘገበ እንዳልሆነ በመንበረ ፖትርያርክ ጠቅላይ ጽ/ቤት የቀረበው ሪፓርት ያስረዳል፡፡

 

አጠቃላይ ጉባኤው እስከ ጥቅምት 11 ቀን 2004 ዓ.ም የሚቀጥል ሲሆን ለቤተ ክርስቲያን የሚጠቅሙ ውይይቶችና የውሳኔ ሐሳቦች እንደሚቀርቡበት ይጠበቃል፡፡

ቤተ ክርስቲያን የደረሰችበት ወቅታዊ ሁኔታ

ዲ/ን ታደሰ ወርቁ

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን በሰማያዊ ሥርዓት በምድር ያለች ሰማያዊት ተቋም ነች፡፡ በምድር ያለነውን ልጆቿን በሰማያዊው ሥርዓት በምድር አዘጋጅታ በሰማይ የምታኖር ናት፡፡ “አሐቲ” ተብላ የምትጠራ የክርስቲያኖች መገናኛ በመሆኗ ወደሷ ለሚመጣው ሁሉ በረኛ፣ ጥበቃ፣ ከልካይ፣ አሰናካይ የሌለባት ነፃ እልፍኛችን ናት፡፡ እንዲሁም ከበሉ መራብ፤ ከጠጡ መጠማት የሌለበት ሰማያዊውን መና፣ በሰማያዊ ሥርዓት የምታስገኝልን አማናዊ የእናት ጓዳ በመሆኗ መታመኛችንና መመኪያችን ናት፡፡
ከሁሉ ይልቅ ቤተ ክርስቲያን በማይነዋወጥ ወለድ ዋሕድ በሚለው መሠረተ እምነት፤ ነቢያት፣ ሐዋርያት ሊቃውንት ስለወልድ ዋሕድ በአስተማሩት ትምህርት መሠረት ላይ የታነፀች እውነተኛ የሕግና የትክክለኛ ሥርዓት መገኛ ናት፡፡ በየጊዜው የነበረው ፈተና የውስጥና የውጭ ጠላቶቿ ጥቃት አስተዳደራዊ ጉዞዋን ቅርቃር ውስጥ የከተተው ቢሆንም የዘመኑን ተልእኮዋን ለማሳካት በቂ ነበር፡፡
ይሁን እንጂ ቤተ ክርስቲያን አሐቲ፣ ሐዋርያዊት፣ ኩላዊት ሁና ሳለች በጥቂቶች ከላሽነት የተነሣ የውጭና የሀገር ውስጥ ሲኖዶስ በሚል ተከፋፍላለች፡፡ ተቋማዊ አስተዳደራዊ ፋይናንሳዊ ቀውስ ውስጥ ገብታለች፡፡ የዚህ ድምር ውጤትም የምእመናንን ሕሊናም እየከፈለ፣ እያደማም ይገኛል፡፡
ቤተ ክርስቲያን በአስተምህሮዋ በአስተዳደሯ፣ በፋይናንስ አያያዟና አጠቃቀሟ የከፋና ውስብስብ ጊዜ ጠየቅ ችግሮችና ፈተናዎች ተጋርጠውባታል፡፡ አንዳንዶቹ ፈተናዎችና ችግሮች ሥር የሰደዱ አዝማናትን ያስቆጠሩ ናቸው፡፡ አንዳንዶቹ ደግሞ ዘመንና መስክ ወለድ ናቸው፡፡ ሌሎቹ ደግሞ እንደ ቅዱሳት መጻሕፍት ከኅልፈተ ዓለም በፊት ይቆማሉ ተብሎ የሚታሰቡ አይደሉም፡፡ ቢያንስ ቢያንስ ግን ለዘመንና መስክ ወለድ ችግሮቻችን መፍትሔ ማፈላለግ የዘመናችን የቤተ ክርስቲያኒቱ ላአላይና ታህታይ መዋቅር መሪዎች ተናጥላዊና የወልዮሽ ሓላፊነት ነው፡፡
እናም በፈቃደ እግዚአብሔር፣ በአባቶቻችን የመንፈስ ልዕልናና ጽናት ተጠብቆ የቆየው የቤተ ክርስቲያኒቱ መሠረተ እምነት፣ ሥርዓተ አምልኮ፣ ትውፊት ለመጪው ትውልድ ያለ እንከን መተላለፍ የሚችለው፣ በጉልህ የሚታዩትን አስተምህሯዊ ቅሰጣ፣ የአስተዳደር፣ የፋይናንስ አያያዝና አጠቃቀም ችግሮችን ማረም፣ ማስተካከል፣ ሥርዓታዊና ሕጋዊ መሠረት ማበጀት ስንችል ብቻ ነው፡፡
ይህ ሆኖ እንድናይ ደግሞ በታሪክ መስታወትነት ወደ ኋላ ሔደን አሁን ያለንበትን ከአለፈው ጋራ በማዛመድ ከየት ተነሥተን ያለንበት ደረስን? ወዴትና በምን ያህል ፍጥነት እየመራን ነው? ምን ዓይነት የመፍትሔ አቅጣጫዎችን በምን ያህል ፍጥነት ብናስቀምጥ የተጋረጠብንን አደጋ እንቀንሳለን? ለሚሉት መሠረታዊ ጥያቄዎች ተግባራዊና ተጨባጭ ምላሽ መስጠት ያስፈልጋል፡፡
እነዚህን ሦስት መሠረታዊ እና የነባራዊው ሁኔታ ነጸብራቅ የሆኑትን ጥያቄዎች ከግንዛቤ በማስገባት ጽሑፉን በሦስት ዓበይት ክፍሎች ለማቅረብ መርጠናል፡፡ በመጀመሪያው ክፍል ቤተ ክርስቲያኒቱ እስከ አምስተኛው መቶ ክፍለ ዘመን ዘመናት በሚለው ርእስ ሥር ከየት ተነሥተን ያለንበት ደረስን? የሚለውን ጥያቄ ለመመለስ እንሞክራለን፡፡ በሁለተኛው ክፍል ደግሞ ቤተ ክርስቲያናችን አሁን ያለችበት ነባራዊ ሁኔታ በሚለው ርእስ ሥር ወዴትና በምን ያህል ፍጥነት እያመራን ነው? የሚለውን ጥያቄ ከምንገኝበት ነባራዊ ሁኔታ ጋር በማዛመድ ለማየት እንጥራለን፡፡ በሦስተኛውና የመጨረሻው ክፍል የመፍትሔ አቅጣጫ ጥቁምታ በሚለው ርእስ ሥር በሁለቱ ቀደምት ክፍሎች ትንታኔ ላይ በመመሥረት ምን ዓይነት የመፍትሔ አቅጣጫዎች፣ በምን ያህል ፍጥነት ብናስቀምጥ የተጋረጡብንን አደጋዎች እንቀንሳለን? የሚለውን ጥያቄ ለመመለስ እንሞክራለን፡፡

ቤተ ክርስቲያኒቱ እስከ አምስተኛው መቶ ክፍለ ዘመን
ቤተ ክርስቲያኒቱ የነበረችበት ታሪካዊ ሁኔታ /Historical condition/ ጥርት ባለ እና በተስተካከለ ገጽታ ለመረዳት ተልእኮዋን እንደ አንድ ማንጸሪያ /parameter/ መጠቀሙ አስፈላጊ ነው፡፡ ቤተ ክርስቲያን ምድራዊውን ሰው በሰማያዊ ሥርዓት ወደ ሰማያዊ ኑሮ እንድታሸጋግር ከመሥራቿና ራሷ ከሆነው ክርስቶስ ሦስት መሠረታዊ ተልእኮ ተሰጥቷታል፡፡ በወልድ ዋሕድ መሠረተ እምነት ማጥመቅ፣ ማጽናትና መከታተል ናቸው፡፡ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያንን ታሪካዊ ሁኔታ የምንፈትሸውም አንዱ ከእነዚሁ ተልእኮዎቿ ተነሥተን ነው፡፡

ቤተ ክርስቲያን በኢትዮጵያዊ ጃንደረባና በሶሪያዊው ፍሬምናጦስ ዘመን

ዶክተር ሥርግው ሐብለ ሥላሴ “The Religious Life In Ethiopia” በሚል ርእስ እ.ኤ.አ. በ1970 በአቀረቡት የጥናት ወረቀታቸው ላይ እንዳመለከቱት፣ የክርስትና ሃይማኖት ወደ ኢትዮጵያ የገባበት መንገድ ከሌላው ዓለም በእጅጉ ይለያል፡፡ በሌላው ዓለም ክርስትና የተጀመረው ከተርታው ሕዝብ ነው፡፡ በመንግሥት የታወቀና የተረዳ ሃይማኖት አልነበረም፡፡ በእኛ ሀገር ግን የመጀመሪያዎቹ አማኞች ከተርታው ሕዝብ አይደሉም፡፡ ነገሥታቱና መኳንንቱ ከነቤተሰቦቻቸው ነበሩ፡፡ ሃይማኖቱም ብሔራዊ ሃይማኖት ነበር፡፡ እንዲህ ዓይነቱ ክስተት በሌሎች የዓለም ሀገሮች የክርስትና ታሪክ ውስጥ አልሆነም፡፡ በኢትዮጵያ ግን ሆኗል፡፡ የኢትዮጵያ ሕዝብ ክርስቲያን የሆነውም በዚህ ሁኔታ ነው፡፡
የክርስትና ሃይማኖት አገባብ ብቻ ሳይሆን የቤተ ክርስቲያኒቱም አደረጃጀት ከሌላው ዓለም እንዴት እንደሚለይ ዶክተር ሥርግው ሐብለ ሥላሴ በዚሁ የጥናት ወረቀታቸው ሲገልጹ፤ “…. የቤተ ክርስቲያኒቱ አደረጃጀትም ከሌላው የክርስትና ዓለም የተለየ ነበር፡፡ ክርስትናን ያስተዋወቀው የመጀመሪያ ሰው ሶሪያዊው ፍሬምናጦስ ነው፡፡ ይሁንና ከእርሱ በኋላ አስተዳደሩ ይመራ የነበረው በኢትዮጵያውያን አልነበረም፡፡ በግብጻውያን ጳጳሳት ሆኖ ቀጥሏል፡፡ ኢትዮጵያም በአንድ ጳጳስ ብቻ እንድትመራ በሕግ ደንግገዋል፡፡ በዚህ መልኩ ኢትዮጵያውያን ለአንድ ሺሕ ስድስት መቶ ዘመን በአንድ ግብጻዊ ጳጳስ ሥር እንዲወሰኑና ተጨማሪ አስተዳደራዊ ነፃነት እንዳይኖራቸው ተደርጓል” በማለት ነበር፡፡
በእርግጥ ክርስትናው የገባበት መንገድና የቤተ ክርስቲያኒቱ የአደረጃጀት መነሻ ከላይ የታሪክ ተመራማሪው ዶክተር ሥርግው እንደአስቀመጡት ቢሆንም ክርስትና ወደ ኢትዮጵያ የገባውና ወይም ኢትዮጵያና የክርስትና ሃይማኖት የተዋወቁት መጽሐፍ ቅዲስ እንደሚያስረዳው / ሐዋ.8፥26-40/ ሐዋርያው ፊልጶስ ኢትዮጵያዊውን ጃንደረባ ባጠመቀው ጊዜ ነው፡፡ ይህም የሆነው ከጌታ ልደት በኋላ በ34 ዓ.ም ነው፡፡
ብፁዕ አቡነ ጎርጎርዮስ የሸዋ ሊቀ ጳጳስ የነበሩት “የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ታሪክ” በተባለው መጽሐፋቸው ከላይ በጠቀስነው አግባብ የኢትዮጵያና የክርስትና ሃይማኖት ትውውቅ ከአሰፈሩ በኋላ፣ በኢትዮጵያ ክርስትና ውስጥ የፍሬምናጦስ /አባ ሰላማን/ ሚና ሲገልጹ፤ “ኢትዮጵያዊው /ጃንደረባው/ ተጠምቆ ወደ ሀገሩ ከተመለሰ በኋላ አዲሱን ሃይማኖት ለሀገሩ ሕዝብ አስተምሯል፡፡ የመጀመሪያው የኢትዮጵያ ጳጳስ ፍሬምናጦስ /አባ ሰላማ/ ሥርዓተ ክርስትናን በትምህርት ያጠናከረው ኢትዮጵያዊው ጃንደረባ በመሠረተው ነው፡፡ ፍሬምናጦስ ጵጵስናውን ተቀብሎ ከተመለሰ በኋላ በኢትዮጵያ የክርስትናን ሥርዓት አስፋፈቶ ሰበከ፤ የክህነትና የቁርባንን ሕግ አጠናከረ፡፡ በኢትዮጵያ ግዛት በሙሉ የወንጌልን ትምህርት ለማዳረስ የሚረዱ ቀሳውስትንና ዲያቆናትን ሾመ፤ ቅዱሳት መጻሕፍትን ከሱርስት፣ ከዕብራይስጥና ከጽርእ ወደ ግእዝ ቋንቋ መለሰ፡፡ በዚህ አኳኋን በ330 ዓ.ም ክርስትና የኢትዮጵያ ብሔራዊ ሃይማኖት ሆነ” ይላሉ፡፡
ዲያቆን ዳንኤል ክብረት “የሐዋርያነት ሥራ በኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን አጭር መግቢያ” በሚለው የጥናት ወረቀቱ እንዳመለከተው ኢትዮጵያዊው ጀንደረባ ከአክሱም ቀጥሎ ኑብያን፣ ከኑብያም በኋላ ቀይ ባሕርን ተሻግሮ በየመንና በፐርሽያ ወንጌልን ሰብኳል፡፡
ከእርሱም በኋላ ደግሞ በአራተኛው መቶ ክፍለ ዘመን አንድ ሊቅ በአምስተኛ መቶ ክፍለ ዘመን በሊቢያ የኢትዮጵያን ሰዎች ማየቱን ገልጧል፡፡ በአቡነ ሰላማ ከሣቴ ብርሃን ዘመንም አባታችን ወደ ኑብያ፣ አኑኖ እና መርዌ አምስት ቆሞሳትን ልከው እንደነበረ መረጃዎች ይጠቁማሉ፡፡ አብርሃና አጽብሐ ክርስትናን ተቀብለው ከተጠመቁ በኋላ በሸዋ፣ በጎጃም ብሎም እስከ ጋሞ ጎፋ ብርብር ማርያም ድረስ ወንጌል ሰባክያን እየተላኩ ወንጌልን አስተምረዋል፡፡
የታሪክ ተመራማሪው ዶክተር ሥርግው ሐብለ ሥላሴ “The Establish event of the Ethiopian church” በሚል ርእስ ባቀረቡት የጥናት ወረቀታቸው ላይ፤ ከላይ በአቡነ ጎርጎርዮስ የተገለጠውን ዘመነ ፍሬምናጦስ በኢትዮጵያ ክርስትና ውስጥ ያለውን ታሪካዊ ቦታ ሲያብራሩ፤ “የክርስትና ሃይማኖት እንደመንግሥታዊ ሃይማኖት መተዋወቁ በኢትዮጵያ ታሪክ ወሳኝ ነጥብ መሆኑን ያሳያል” ካሉ በኋላ “ክርስትና በሀገሪቱ የሚያካትተው ንጹሕ ሃይማኖታዊ ክስተቶችን ብቻ አይደለም፡፡ በሁሉም ሀገራዊ ኑሮ ላይ ዘርፈ ብዙ ሚና አለው፡፡ ቤተ ክርስቲያኒቱ ሃይማኖታዊ ብቻ ሳትሆን ለበርካታ ዘመናት የአገሪቱ ሕዝብ የባህል፣ የፖለቲካና ማኅበራዊ ኑሮ ግምጃ ቤት መሆኗን ያሳያል” ይላሉ፡፡
ዘመነ ቅዱስ ፍሬምናጦስ በኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲየን መንበረ ጵጵስና ታሪክ ውስጥ ያለውን ሀገራዊና ዓለም አቀፋዊ ፋይዳ ብፁዕ አቡነ ጎርጎርዮስ “የኢትዮጵያ ኦርቶዶክሪስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ታሪክ” በሚለው መጽሐፋቸው “ከርሱ /ከቅዱስ ፍሬምናጦስ/ ጀምሮ የኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን በመንበረ ጵጵስና ከሌሎች ጥንታውያን አብያተ ክርስቲያናት ጋር እኩል ሆነች፡፡” ብለው ሲገልጹ “የኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን ትናንትናና ዛሬ” በሚል ርእስ በቤተ ክርስቲያኒቱ የሊቃውንት ጉባኤ የተዘጋጀው መጽሐፍ ደግሞ “…. ቅዱስ ፍሬምናጦስ በዚህ ሁሉ ሥራው ከሣቴ ብርሃን ሰላማ የሚል ቅጽል ተሰጠው፡፡ ከእርሱ ጀምሮ የኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን በመንበረ ጵጵስና ደረጃ ታወቀች” በማለት ነው፡፡

የኢትዮጵያን ዕሥራ ምዕት ምክንያት በማድረግ በቤተ ክርስቲያኒቱ ሊቃውንት “የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስትያን ታሪክ ከልደተ ክርስቶስ እስከ 2000 ዓ.ም” በሚል ርእስ የተዘጋጀው መድበል ይህንኑ ሐሳብ ሲያጠናክር፤ “ቅዱስ አባ ሰላማ ከዚያን ጊዜ ጀምሮ መንበረ ጵጵስናውን አክሱም ላይ አድርጎ በሀገራችን የወንጌልን ብርሃን በሰፊው ስለገለጠ ከሣቴ ብርሃን ተባለ” ይልና “በዚሁ በአራተኛው መቶ ክፍለ ዘመን የኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን በዓለም አቀፍ ደረጃ የታወቀች ብሔራዊት ቤተ ክርስቲያን ለመሆን መብቃቷን ታሪክ ያስረዳል” ይላል፡፡

የኢትዮጵያን ታሪክ ስንመለከት የአንድም ሐዋርያ ደም ሳታፈስ፣ የአንድም ሰማዕት አጥንት ሳትከሰክስ ኦርቶዶክሳዊት ሃይማኖትን የተቀበለች ሀገር ነች፡፡ ይኼ እንዲሆን ደግሞ ከሕዝባችን ጨዋነት ባሻገር የመንግሥት እና ቤተ ክህነት ግንኙነትም ወሳኝ ታሪካዊ አጋጣሚም ነበር፡፡ ቀደም ብሎ የንግሥተ አዜብ ወደ ሰሎሞን መሔድና የቀዳማዊ ምኒልክ ከሰሎሞን መወለድ ለሥርዓተ ጽዮን አገባብና ለሕገ ኦሪት አመጣጥ ምክንያት ሆነ፡፡ እንዲሁም ደግሞ በሕንደኬ ንግሥት ጊዜ የበጅሮንዷ ወደ ኢሩሳሌም መሔድና ከሐዋርያው ፊልጶስ ጋራ ተገናኝቶ የወንጌልን ዜና ጽድቅ ለማምጣት መሪ ሆነ፡፡ ቅዱስ ፍሬምናጦስ በኢትዮጵያ ቤተ ክህነትና ቤተ መንግሥት አማካኝነት ተመርጦ ወደ እስክንድርያ ሔዶ ጵጵስና ተሹሞ መጠቶ እስካሁን ሲያያዝ የመጣውን የወንጌል መክሊት በብዙ ሚሊዮን ለሚቆጠሩ ምእመናን አተረፈ፡፡ ይኼ ደግሞ ሌላኛው ቤተ ክርስቲያናችን የተገነባችበት የታሪክ ገጽታችን ነው፡፡
የዚህ ዓይነቱ ታሪካዊ ትስስር በወቅቱ ከነበረው ዓለም አቀፋዊ ነባራዊ ሁኔታ አንጻር ቤተ ክርስቲያኒቱ የነበረችበትን ታሪክዊ ቦታ ዶክተር ሥርግው ሐብለ ሥላሴ “The Establishment of the Ethiopian church”  በሚለው ጥናታቸው ሲተነትኑ “የክርስትና ሃይማኖት እንደ መንግሥት ሃይማኖት በኢትዮጵያ መግባቱ በተደራጀ በሌላ ሀገር የስብከት ውጤት ሳይሆን የነገሠታቱ /አማኝነት/ ነው” ካሉ በኋላ “ክርስትና በኢትዮጵያ የተዛመተው እንደ ግሪክ ሮማውያን ዓለም ዓይነት የክርስትና ተዛምቶ መንገድ አይደለም፡፡ ክርስትና በእነዚህ ሀገሮች ለሦስት ምእት ዓመታት በታችኛው የኅብረተሰብ ክፍል ቢታቀብም ወዲያው የገዢው መደብ ተቃውሞታል፡፡ በእርግጥ በአራተኛው መቶ ክፍለ ዘመን መጀመሪያዎች በጣም ጥቂት የሚሆኑ የነገሥታት ቤተሰቦች የክርስትና ሃይማኖትን መቀበል ቢጀምሩም በኢትዮጵያ ግን መቀበሉ ከምር ነበር፡፡ ክርስትናው በመጀመሪያ በቤተ መንግሥቱ ገባ፣ ከዚያ ቀስ በቀስ ወደመላው ሕዝብ ተዛመተ፡፡ በሮማ ግዛት ዐፄ ሕዝቡን በክርስትና ሃይማኖት ለማሳመን ሐዋርያትና የኋላ ዘመን አባቶች ሲሳተፉ፣ በኢትዮጵያ ክርስትና በፈቃደኝነት ገባ” ይላሉ፡፡ ይህ ማለት ሐዋርያዊ፣ አገልግሎት አልነበረም ለማለት እንዳልሆነ ልብ ይሏል፡፡
ዶክተር ሥርግው ሐብለ ሥላሴ ትንታኔያቸውን በመቀጠል፤ የኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን እንደ መንግሥት ሃይማኖት ከርስትናን ስትቀበል ስለነበረው ወቅታዊ ዓለም አቀፍ ሁኔታም ሲያብራሩ የኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን ሥርዓቷ እየተጠናከረ በምትቋቋምበት ወቅት የአርዮስ ክህደት ጫፍ ላይ ደርሶ ነበር፡፡ ቅዱስ ፍሬምናጦስ በቅዱስ አትናቴዎስ በሚመራው የእስክንድርያ መንበር ሥር ሆኖ በኒቅያ ጉባኤ አርዮስን ከሚቃወሙ የኦርቶዶክሳውያኑ ወገን ነበር፡፡ ይህም የሆነው የኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን በብሔራዊነት ከመመሥረቷ በፊት ነው፡፡ ነገር ግን የጉባኤው ውሳኔ አስገዳጅ ባይሆንም ኢትዮጵያ ከአትናቴዎስ እና ከኒቅያ እምነት ነች ካሉ በኋላ በወቅቱ የኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን ከአርዮሳውያን የገጠማትንም ፈተና ሲገልጹም፤ “የታላቁ ቆስጠንጢኖስ ልጅ ቆንስጣ ወደ አርዮስ ምንፍቅና ለማምጣት ጥረት አድርጎ ነበር፡፡ በዚህ ምክንያትም ለኢዛና እና ሳይዛና ቅዱስ ፍሬምናጦስን ወደ እስክንድርያ እንዲልከውና የእርሱም ሃይማኖት እንዲፈተሽ ደብዳቤ በመላክ ጠይቆ ነበር፡፡ ዓላማውም የኦርቶዶክሳዊነትን ዓለም ተቀፋዊ ተቀባይነት ማረጋገጥ ነበር፡፡ በዚህ አንጻር በኢትዮጵያ ላይ ያደረጉት ተልእኮ ሳይሳካ ቀረ፡፡ ቅዱስ ፍሬምናጣስም ከአትናቴዎስ የተማረውን ትምህርት እያስተማረ በአክሱም ቀረ፡፡” በማለት ነው፡፡ ይኼ እንግዲህ አንዱ የታሪኳ አካል ነው፡፡

ዘመነ ተሰዓቱ ቅዱሳን

ዶክተር ሥርግው ሐብለ ሥላሴ “The Expansion and consolidation of Christianity” በሚል ርእስ በአሰፈሩት መጣጥፋቸው ደግሞ የኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን የሐዋርያነት አገልግሎት ምን እንደሚመስል ያስቃኙናልና፡፡ “እንደ ኢትዮጵያ ጳጳሳት ታሪካዊ ቅደም ተከተል ዝርዝር ከሆነ ቅዲስ ፍሬምናጦስ የተተካው በአቡነ ሚናስ ነው፡፡ መካነ ልደቱም ከግብጽ ነው፡፡ ከዚህ ጊዜ ጀምሮ ለአንድ ሺሕ ስድስት መቶ ዓመታት የግብጻውያን ልዩ የሆነው አገዛዝ በኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን ላይ ተጫነ፡፡ በዚህ ዘመን በግብጻውያን ዘንድ ሁሉ ኢትዮጵያውያን ለሢመተ ጵጵስና ብቁዎች ተደርገው አይወሰዱም፡፡ ሚናስ ስለራሱ ሐዋርያዊ አገልግሎት ጥቂት የሥነ ጽሑፍ መረጃ ቢተውም በሐዋርያዊ አገልግሎት በከፍተኛ አስተዋጽኦነቱ የሚጠቀሰው የዘጠኙ ቅዱሳን አገልግሎት ነው” ይላሉ ዶክተር ሥርግው ሐብለ ሥላሴ ከላይ በጠቀስነው ጽሑፋቸው፡፡
እኚህ የታሪክ ምሁር “The Religious Life in Ethiopia” በተባለው የጥናት ወረቀታቸው ደግሞ እነዚህ ቅዱሳን ሐዋርያነትን መሠረት በአደረገው አስተዳደራዊና ማኅበራዊ አገልግሎት ቤተ ክርስቲያኒቱን በየትኛው የታሪክ ምዕራፍ ላይ እንደአስቀመጡ ሲገልጹ “በዘጠኙ ቅዱሳን ቤተ ጣዖትንና የቆዩ ማእከለ ሁሉን አምላኪዎች /Pagan centers/ ወደ ክርስትና ማእከልነት ለወጡ፡፡ በዚህ ሒደት ከሕዝቡ ምንም ተቃውሞ አልገጠማቸውም፤ አንድም ቅዱስ አልተሰዋም” ይላሉ፡፡
ይህ ሒደት በሀገሪቱ የክርስትና ታሪክ ውስጥ አንዱ አስደሳች ክስተት ነው፡፡ በዘጠኙ ቅዱሳን መምጣት ምክንያት የተስፋፋው የክርስትናው ሃይማኖት ብቻ ሳይሆን የአገሪቱም ባህል ክርስቲያናዊ እንዲሆን ተደርጓል፡፡ ይህም የጥንቱ የክርስትና አገባብ ጠባይ ነው፡፡ የሚሉት ዶክተር ሥግግው ሐብለ ሥላሴ “ይኼ ሃይማኖታዊ ክስተት ብቻ ሳይሆን የማኅበራዊ አገልግሎት፣ የኅብረተሰቡ የማኅበራዊ ኑሮ አካል ነው፡፡ ቤተ ክርስቲያን የእግዚአብሔር ማምለኪያ ሥፍራ ብቻ ሳትሆን የተለያዩ ማኅበራዊ ችግሮች መፍቻ ቦታ መሆኗም በእነዚህ ቅዱሳን ተግባር ተረጋግጧል፡፡” ይላሉ፡፡ ከዚያም በመቀጠል “በጥቅሉ እነዚህ ቅዱሳን ቤተ ክርስቲያኒቱ ወይም ክርስትና እንደ ሃይማኖት ክስተት ሃይማኖታዊ ተቋም እና በማኅበረሰቡ ውስጥ ደግሞ ማኅበራዊ አገልግሎት ሰጪ እንድትሆን አድርገዋታል” ይላሉ፡፡
ብፁዕ አበኑ ጎርጎርዮስ “የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርሰቲያን ታሪክ” በተባለው መጽሐፋቸው እነዚህ ቅዱሳን ኦርቶዶክሳዊት ሃይማኖታችንን እንዴት እንደ አጸኑም ሲገልጹ “… በእነዚህ ዘጠኙ ቅዱሳን የጸናችልን ሃይማኖታችን ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ትባላለች፡፡” በማለት ነው፡፡ እነዚህ ቅዱሳን ቤተ ክርስቲያኒቱን ያጸኑበትን የአገልግሎት ትሩፋታቸውን “የኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን ትናንትናና ዛሬ” በሚል ርእስ የተዘጋጀው መጽሐፍ ሲዘረዝር “ሥርዓተ ምንኩስናን፣ ገዳማዊ ሕይወትንና ምናኔን ማስተማር፣ ገዳማትን በየቦታው ማቋቋም፣ በቅዱስ ፍሬምናጦስ ጊዜ ያልተተረጎሙ መጻሕፍትን መተርጎም፤ በከሣቴ ብርሃን ሰላማ ጊዜ የተቋቋመችውን ቤተ ክርስቲያን ማጠናከር” በማለት ነው፡፡
ዲያቆን ዳንኤል ክብረት “የሐዋርያት ሥራ በኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን አጭር መግቢያ” በሚል ርእስ በጻፈው መጣጥፉ እንደገለጸው፣ ዘጠኙ ቅዱሳን በትግራይና አካባቢዋ ወንጌልን በማስፋፋት ቅዱስት መጻሕፍትን በመተርጎምና ገዳማትን በማስፋፋት ለሐዋርያነት ተልእኮ ታላቅ አስተዋጽኦ አድርገዋል፡፡ በዚህም የመጀመሪያው ዘመን በኤርትራ፣ ትግራይ፣ ወሎ፣ ጎንደር ጎጃምና ሸዋ ሀገረ ስብከት ወንጌልን ማስፋፋት ተችሏል፡፡ በትግራይ የተሰዐቱ ቅዱሳን ገዳማት፣ በወሎ የተድባበ ማርያም ደብር፣ በሸዋ በጥንቱ ዞረሬ በዛሬው ደረሳ ብርቴ ጥረት የተደረገው በዚህ ዘመን ነው፡፡
ከተግባራቸው ተንሥተው የዘጠኙ ቅዱሳን ወደ ኢትዮጵያ መምጣት በኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን ያለውን አንድምታ ዶክተር ሥርግው “The Expansion and consolidation of Christianity” በተባለው የጥናት መጣጥፋቸው ሲጠቅሱ “…. የዘጠኙ ቅዱሳን ወደ ኢትዮጵያ መምጣት በኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን ሃይማኖታዊ ሕይወት እና በሀገሪቱ የባህል ዕድገት ውስጥ አዲስ ምዕራፍ የከፈተ ነው” በማለት ነው፡፡ “የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ታሪክ ከልደተ ክርስቶስ እስከ 2000 ዓ.ም” የተባለውም መድበል ከላይ የጠቀስነው የዶክተር ሥርግውን ሐሳብ በማጠናከር እንዲህ ይላል፡፡
“ከዘጠኙ ቅዱሳን መምጣት በኋላ የአክሱም ቤተ መንግሥትና መላው የኢትዮጵያ ግዛት በክርስትና ሃይማኖት ትምህርትና ስብከት ተደርሶ ነበር፡፡ ተሰዐቱ ቅዱሳን ለኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ እምነት ጥንካሬ ከፍተኛ ተልእኮን ፈጽመው ስለዐረፉ ቤተ ክርስቲያናችን ቅዱሳን ብላ ታከብራቸዋለች”
በዚሁ መጽሐፍ ብፁዕ አቡነ ገሪማ “የኢትዮጵያ ኦርቶዶክሪስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን አስተዳደርና መንግሥት በየዘመናቱ” በሚል ርእስ ባቀረቡት ጽሑፍ ተሰዓቱ ቅዱሳን በአመራራቸው በሕዝበ ክርስቲያኑ እንደሚወደዱ ገልጸዋል፡፡
እንግዲህ ከነዚህ የመጀመሪያዎቹ የክርስትና ዘመናት ክንዋኔዎች ተነሥተን ቤተ ክርስቲያኒቱ በወቅቱ ተልእኮዋን ለመወጣት የሚያስችላት የወቅቱ አደረጃጀት እንደነበራት መደምደም ይቻላል፡፡ ይኼንም አደረጃጀት ዶክተር ሥርግው ከላይ በጠቀስነው የጥናት ጽሑፋቸው ላይ የጠቀሱት “ከክርስትና መስፋፋት በኋላ በኢትዮጵያ ውስጥ ቢያንስ አራት አህጉረ ስብከት ነበር፡፡ እያንዳንዱ የሚመራው በጳጳስ ነበር፡፡ የእነዚህም ርእስ የአክሱም ሊቀ ጳጳስ እንደሆነ ግልጽ ነው፡፡ አስቀድመን እንደገለነጽነው ሁሉም ጳጳሳት መካነ ልደታቸው ግብጽ ወይም ግብጻውያን ናቸው፡፡ በዶግማም ሆነ በአስተዳደር ከግብጹ ፓትርያርክ ጋራ የጠበቀ ግንኙነት አላቸው፡፡ በኢትዮጵያ ላይ የሚያስፈጽሙት የግብጽን ፍላጎት ነበር፡፡ ይህም በቤተ ክርስቲያን ታሪክ ውስጥ ልዩ ክስተት ነው” በማለት ነው፡፡
ከዚህም በተጨማሪ በአራተኛው መቶ ክፍለ ዘመን የቤተ ክርስቲያኒቱ አስተዳደር የነበረበት ሁኔታ ብፁዕ አቡነ ገሪማ ከላይ በጠቀስነው መጽሐፍና ርእሰ ጉዳይ ላይ “አራተኛው መቶ ዓመት በቅዱሳን ነገሥተ ኢትዮጵያ አብርሃ ወአጽብሐ ዘመን መንግሥት፤ በቅዱስ ፍሬምናጦስ ዘመን ክህነት ስብከተ ወንጌል የተስፋፋበት የቤተ ክርስቲያኒቱ አስተዳደር አምሮ፣ ሰምሮ፣ የታየበት የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክረስቲያን ብሔራዊት የሆነችበት ጊዜ ነበር” ይላሉ፡፡
ከዚህም ጋር አያይዘው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ከአራተኛው መቶ ዓመት እስከ ዐሥራ አምስተኛው መቶ ዓመት እስከ ዐሥራ አምስተኛው መቶ ዓመት በነበሩት በዘመናት በመካከሉ በየጊዜው ችግር ቢያጋጥምም ሁለንተናዊ የሆነ አርኪ የቤተ ክርስቲያን ታሪካዊ አስተዳደር የተፈጸመበት ዘመን መሆኑን አበክረው ይገልጻሉ፡፡
እንግዲህ ቤተ ክርስቲያን በፊት በኢትዮጵያው ጃንደረባ የተሰበከችልን በቅዱስ ፍሬምናጦስ እና በዘጠኙ ቅዱሳን የጸናችልን ነች፡፡ ከዚያም በኋላ የእስልምና መነሳት፣ የዮዲት ጉዲት ጥፋትና የግራኝ አህመድ ውድመት በቤተ ክርስቲያኒቱ በየዘመኑ ቢፈራረቁም በርካታ ወርቃማ ሥራዎች ተሠርተዋል፡፡ ከአለው ነባራዊ ሁኔታ ከዚህ በላይ መሔድ አንችልም፡፡ የት ነበርን የሚለውን ለማሳየት የክርስትና የመጀመሪያዎቹን ዘመናት አይተናል፡፡ ቦታ ኖሮን እያንዳንዱን ዘመን ብናይ አሁን ከአለንበት ጋራ ስናነጻድር እጅግ ያስቆጭ ነበር፡፡ ይሁንና አሁን ያለውን ነባራዊ ሁኔታ ለማየት ያነሳናቸው ማሳያዎች በቂ ናቸው፡፡

ቤተ ክርስቲያኒቱ አሁን ያለችበት ሁኔታ
እንግዲህ ቤተ ክርስቲያኒቱ በየዘመናቱ የተለያዩ ፈተናዎች ቢገጥሟትም አስቀድመን እንደተመለከትነው ተልእኮዋን በአግባቡና ሥርዓታዊ በሆነ መልኩ ትወጣ ነበር፡፡ በዚህ መልኩም ከእኛ ዘመን ደርሳለች፡፡ ይሁንና አሁን ያለችበት ነባራዊ ሁኔታ ከጊዜ ወደጊዜ እየተወሳሰበ ከመምጣቱ የተነሣ ተልእኮዋ ላይ አደጋዎች ተጋርጠዋል፡፡ እነዚህን በሦስት ከፍለን እናቀርባለን፡፡
ሀ. አስተምህሯዊ ቅሰጣ
ቤተ ክርስቲያን የተመሠረተችው ወልድ ዋሕድ በሚለው መሠረተ እምነት እና ነቢያት፣ ሐዋርያት ስለ ወልድ ዋሕድ መሠረተ እምነት በአስተማሩት ትምህርት ላይ ነው፡፡ እነዚህን የመሠረተ እምነት ትምህርቶች ከምእመናን ልቡና የማራቅና ከቤተ ክርስቲያኒቱ ዐውደ ምሕረት የማስወገድ ሥራ በከፍተኛ ሁኔታ የእርሷ ነን በሚሉ በተግባራቸው ግን ባልሆኑት እየተሠራ ነው፡፡ ይኼም ሥራ እየተሠራ ያለው በተሐድሶ ኑፋቄ አንቀንቃኞች፣ ሰባክያንና የስሕተት ትምህርት ባዘሉ መጻሕፍት ጸሐፊያን ነው፡፡ የቤተ ክርስቲያኒቱን ሥርዓተ አምልኮ፣ ትውፊትና ታሪክ የመከለሱና የመበረዙ ሥራ በነዚሁ አካላት ተጧጡፏል፡፡ በአንጻሩ ደግሞ ቤተ ክርስቲያኒቱ ይህን አደጋ በአግባቡ የተረዳና ተገቢውን የመፈትሔ አቅጣጫ የሚያስቀምጥ የስብከተ ወንጌል ዕቅድና ግብ የላትም፡፡ ለዚሁ ተግባር ማስፈጸሚያ ተገቢ አደረጃጀት፣ የሰው ኃይልና በጀት አትመድብም፡፡ ይኼ ደግሞ ችግሩ እጅግ አሳሳቢና የቅድስት ቤተ ክርስቲያንን ሐዋርያዊ ተልእኮ በማሳካት ረገድ መጪውን ዘመን ጨለማ ያደርገዋል፡፡ ለዚህ እንደማሳያ የሚጠቀሰው በ1999-2000 ዓ.ም በተካሔደው የሕዝብና ቤቶች ቆጠራ ውጤት በግልጽ የታየው እውነታ ነው፡፡ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ምእመናንን ቁጥር ከ50.6 በመቶ ወደ 43.5 በመቶ ወርዷል፡፡  በከተማ ቤተ ክርስቲያናችን ያላት የምእመናን ድርሻ እየቀነሰ መጥቶ ወደ 59.1 በመቶ ሲሆን በገጠር ደግሞ 40.5 በመቶ ነው፡፡ በአጠቃላይ ቤተ ክርስቲያኒቱ በሀገር አቀፍ ደረጃ ያለው ድርሻ ቁልቁል እየወረደ መሆኑን ያሳያል፡፡ በሀገር አቀፍ ደረጃ የ7.1 በመቶ መቀነስ አሳይቷል፡፡ ይኼ ሁኔታ በዚህ መልኩ ከቀጠለ የቤተ ክርስቲያን ህልውና አደጋ ላይ መሆኑን ለመጠቆም ነቢይ መሆን አያስፈልግም፡፡ በዚህ ሒደት ውስጥ ደግሞ የእርሷን እንጀራ እየበሉ በሌላው ደጅ የሚጠኑ ሰዎቿ ድርሻውን ይወስዳሉ፡፡
ለ. አስተዳደራዊ ችግር
የቤተ ክርስቲያኒቱ ዋነኛ ተልእኮዎች የሆኑት ማጥመቅ፣ ማጽናትና መከታተል መሆኑ እየታወቀ ይህን ተልእኮ ማሳካት የሚያስችል የተጠናከረ አስተዳደራዊ አደረጃጀትና የሰው ኃይል የለም፡፡ የቤተ ክርስቲያኒቱ አስተዳደራዊ አደርጃጀትና አወቃቀር ወቅቱ ከሚጠይቀው፣ አሁን ካሉት ሥራዎች ስፋትና ከልማትና ማኅበራዊ እንቅስቅሴዎች ጋር አብሮ የሚጓዝ አይደለም፡፡ ቤተ ክርስቲያናችን ወቅቱን በመዋጀት ከጊዜው ጋራ እንዳትራመድ አድርጓታል፡፡
ቅዱስ ሲኖዶስ የቤተ ክርስቲያኒቱን ፖሊሲ በማውጣትና ስትራቴጀ በመንደፍ የመምራት ሓላፊነቱንና አደራውን በብቃት ለመወጣት በሚያስችል ሁኔታ አልተደራጀም፡፡ የሚወስናቸውን ውሳኔዎች አፈጻጸም የሚከታተልበትና የሚገመግምበት መከታተያና መገምገማያ እንዲሁም የአሠራር ሥርዓት የለውም፡፡
እንደሚታወቀው የአሠራር መዋቅር ተቋማዊ ግብን የማስፈጸም ሥርዓት እና ብቃት እንዲኖረው ተደርጎ ይዘጋጃል፡፡ በቤተ ክርስቲያኒቱ መዋቅራዊ የአሠራር ሥርዓትን ጠብቆ ጉዳይን በወቅቱ ማስፈጸምም ሆነ መፈጸም አስቸጋሪ ነው፡፡ በየደረጃው የሚገኙ የቤተ ክህነቱ አሠራር መዋቅሮች የቅዱስ ሲኖዶስን ውሳኔዎች የማስፈጸምም ሆነ የመፈጸም ግዴታ ቢኖርባቸውም መዋቅራዊ የአሠራር ሥርዓቱ ልል ከመሆኑ የተነሣ ይህ ሲሆን አይታይም፡፡ የቅዱስ ሲኖዶስ ውሳኔን ከአስፈለገ አንድ የአጥቢያ አስተዳዳሪ የሚጥስበት፣ የጠቅላይ ሥራ አስኪያጅን የሥራ መመሪያ አንድ የመምሪያ ሓላፊ ተገቢና ምክንያታዊ ባልሆነ መንገድ የማይቀበልበት እና የማያስፈጽምበት ሁኔታ አለ፡፡
በቤተ ክርስቲያኒቱ ውስጥ የሚታየው የአስተዳደራዊ አሠራር ክፍተት እንዲህ መሆኑ የራሳቸውን አጀንዳ ለማስፈጸም በቤተ ክርስቲያኒቱ ውስጥ ለሚንቀሳቀሱ አካላት ምቹ መስፈንጠሪያ ሆኖላቸዋል፡፡ በየትኛውም አግባብ በየትኛውም የአሠራር መዋቅር የሚፈልጉትን ያስወስናሉ፤ ያልፈለጉትን ውሳኔ ያሽራሉ፡፡
ገዳማቱና የአብነት ትምህርት ቤቶቹም የሚገኙበት አስከፊ ገጽታም የአስተዳደራዊ ችግሩ ነጸብራቅ ነው፡፡ በቤተ ክርስቲያኒቱ በሚፈጠሩ የተለያዩ አስተዳደራዊ ችግሮች የተነሣ ገዳማቱ ያላቸውን ጥቂት ገቢ፣ መሬት፣ የሰው ኃይልና ሌሎች ሀብቶችን እንዳይጠቀሙ አድርጓቸዋል፡፡ ይህም ገዳማቱን ወደ ቁሪት ገዳምነት እንዲቀየሩ ምክንያት ሆኗል፡፡ በገዳማት ሊኖር ይችል የነበረውንም የልማት ተሳትፎ በእጅጉ ጎድቶታል፡፡ የአብነት ትምህርት ቤቶች ለደቀ መዛሙርቱ እና ለመምህራኑ ምግብና መጠለያ ማግኘት ተስኗቸው ትምህርት ቤቶቹ እንዲዘጉና እንዳይስፋፉ የሆነውም የአስተዳደራዊው ችግር ውጤት ነው፡፡ በዚህ መልኩ በየገዳማቱና የአብነት ትምህርት ቤቶቹ የሚታየው ችግር በዚህ ሁኔታ ከቀጠለ የነገይቱን ቅድስት ቤተ ክርስቲያን አገልግሎት የሚተካ ትውልድ ማግኘትን ከባድ ያደርገዋል፡፡
የአስተዳደሪዊው ችግር ውጤት /Effect/ ያረፈው በገዳማቱና በአብነት ትምህርት ቤቶቹ ብቻ ሳይሆን በካህናቱም ኑሮ ላይ ነው፡፡ ካህናት የሚያገኙት ደመወዝ አሁን ካለው የገበያ ሁኔታ አንጻር ቤተሰቦቻቸውን ለማስተዳደር በቂ አይደለም፡፡ ተምረው ነገ ሀገርንና ቤተ ክርስቲያንን ያገለግላሉ፣ ኑሯችንን ያሻሽላሉ፤ ጧሪ ቀባሪያችን ይሆኑናል የሚሏቸውን ልጆቻቸውን ዘመናዊ ትምህርት ማስተማር እንዳይችሉ ተፅዕኖ አድርጎባቸዋል፡፡ ከዚህ ሲብስም “እኔ በየአብነት ት/ ቤቱ ብዙ ደክሜ የቤተ ክርስቲያኒቱን ትምህርት ተምሬ ምን አገኘሁ” በሚል ልጆቻቸውን ከቤተ ክርስቲያኒቱ ትምህርት እንዲያርቁ አድርጓቸዋል፡፡
የቤተ ክርስቲያኒቱን መንፈሳዊና ቁሳዊ ሀብት /የሰው ኃይል፣ ገንዘብ፣ ንብረት/ አመራር ሠራተኞችን፣ ገንዘብንና ንብረትን በአግባቡና ዘመኑ በሚጠይቀው የአሠራር ዘይቤ በማቀናጀት የቤተ ክረስቲያኒቱ ዋነኛ ተልእኮ ማስፈጸሚያ የሆነውን ሐዋርያዊ አገልግሎት ለማስፋፋትና ማኅበራዊና ምጣኔ ሀብታዊ አስተዋጽኦ ለማድረግ የሚያስችል ዕውቀትና ልምድ ያለው የሰው ኃይል እና አስተዳደር ሥርዓት የላትም፡፡ ይህ ደግሞ የመጪው ዘመን ቀጣይ አገልግሎቷን በሚፈለገውና ወቅቱ በሚጠይቀው መጠን ውጤታማ አያደርገውም፡፡
በመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ጽ/    ቤትና በየአህጉረ ስብከት የሓላፊዎች ምደባ የትምህርት ዝግጅትን ሙያና ችሎታን ወይም ብቃትን መሠረት ያደረገ አይደለም፡፡ ይኼ ደግሞ በቤተ ክርስቲያኒቱ ከፍተኛ የሆነ የአመራር እና አስተዳደር ችግር የሀብት ብክነትና ዝርፊያ፣ ውዝግብና የመልካም አስተዳደር ዕጦትን አንሰራፍቷል፡፡ ይህ ሁኔታ በዚህ መልኩ የሚቀጥል ከሆነ ቤተ ክርስቲያኒቱ ለቤተ ክረስቲያኒቱ ተልእኮ ግድ የሌላቸው ሰዎች መጠራቀሚያ ትሆናለች፡፡ ምእመኑም ባለው አመራር ላይ እምነቱን እያጣ ሲሔድ ለቤተ ክርስቲያኒቱ ማበርከት የሚገባውን በጎ አስተዋጽኦ ከማበርከት ሊታቀብ ይችላል፡፡
ሐ. ዘመናዊ የፋይናንስ አስተዳደር አለመኖር
ቤተ ክርስቲያኒቱ  ተልእኮዋን መፈጸም የሚያስችላት በማእከላዊነት የሚተዳደር ዘመናዊ የፋይናንስ አያያዝና አጠቃቀም ሥርዓት የላትም፡፡ አብያተ ክርስቲያናት ከምፅዋት ከሚያገኙት ገንዘብ ባሻገር የተለያዩ የገቢ ማስገኛ ሕንፃዎች እየገነቡ የተለያዩ የልማት ሥራዎችን ለመሥራት ጥረት ቢያደርጉም የፋይናንስ አያያዛቸውና አጠቃቀማቸው ለብክነትና ምዝበራ የተጋለጠ ነው፡፡ በቤተ ክርስሪቲያኒቱ ውስጥ ጠንካራ የፋይናንስና የኦዲት ሥርዓት እንዲሁም ሓላፊነትና ተጠያቂነት ያለበት በዕቅድና ሪፖርት የታገዘ የአሠራር ሥርዓት የለም፡፡ በዚህ ምክንያት ለልማት ሊውል የሚችለው የቤተ ክርስቲያኒቱ አንጡራ ሀብት ሊባክን ከመቻሉም በላይ ጠንካራ ልማት ሊመጣ አልቻለም፡፡
እንዲህ ዓይነቱ የፋይናንስ አያያዟና አጠቃቀሟ የቤተ ክርስቲያኒቱን መሠረታዊ ተልእኮ ከማደናቀፉም በላይ የራሷን አገልጋዮች በአመዛኙ ከችግር ማሳቀቅ ያልቻለበት ደረጃ ላይ ይገኛል፡፡ ይህም ቤተ ክርስቲያኒቱ በሐዋርያዊ ተልእኮዋ አፈጻጸሟ እንድትደክም ከማድረጉም ባሻገር የሙስናው ጽንፍ ቤተ ክርስቲያኒቱን በምእመናን ዘንድ ያላትን አመኔታና ከበሬታ እያሳጣት ነው፡፡
በአጠቃላይ በቤተ ክርስቲያኒቱ ማእከላዊ የሆነ የፋይናንስ አስተዳደር ባለመኖሩ አገልጋዮቿ ገጠሩን እየተው ገቢ ይገኝባቸዋል ወደሚሏቸው ከተሞች እንዲጎርፉ አድርጓቸዋል፡፡ ይህ ደግሞ በገጠር የሚገኙትን ብዙ አብያተ ክርስቲያናትን ያለ አገልጋይ በማስቀረቱ እንዲዘጉ ሆነዋል፡፡ እዚህ ላይ ሆነን የነገይቱን የገጠሪቱን ቤተ ክርስቲያን ስናስብ ስጋት ላይ ይጥለናል፡፡
ቤተ ክርስቲያኒቱ በስብከተ ወንጌልና ሐዋርያዊ ተልእኮ እንዲሁም በማኅበራዊ አገልግሎትና ልማታዊ ሥራዎች ሊደግፏት የሚችሉት የአገልግሎት ሰጪ ተቋማት በምዝበራና ብኩንነት እየተዳከሙና የሚጠበቅባቸውን ያህል ፍሬያማ ሊሆኑ አልቻሉም፡፡ እንዲህ ዓይነቱ ችግር ሥር እየሰደደና እየጸና ከሔደ ቤተ ክርስቲያኒቱ ለማትወጣው አዘቅት ሊዳርጋት ይተላል፡፡ የጥቂት ግለሰቦች ፈላጭ ቆራጭነት እየጨመረ መዋቅራዊ ውሳኔዎችና አፈጻጸሞች እየከሰሙ ከሔዱ የቤተ ክርስቲያኒቱ የወደፊት ዕጣ ፋንታ በግለሰቦች እጅ እንዲሆን ሊያደርግ ይችላል፡፡ አሁን እየታየ ያለውም በአመዛኙ የዚሁ ተመሳሳይ ነው፡፡
የመፍትሔ አቅጣጫ ጥቁምታ
በአደጋ ቁልቁለት ላይ ያለውን የቤተ ክርስቲያኒቱን አስተምህሯዊ ቅሰጣ-አስተዳደራዊ ፋይናንሳዊ ችግሮች ለመቅረፍ ቤተ ክርስቲያኒቱ ውስጧን በአስቸኳይ የምትፈትሽበት መፍትሔና አፋጣኝ የአሠራር ሥርዓት መዘርጋት አለባት፡፡
ቅዱስ ሲኖዶስ፤ ቤተ ክርስቲያናችን ዋናና ተቀዳሚ ዓላማዋ የሆነውን ሐዋርያዊ አገልግሎት በማስፋፋት፣ የምእመናንን ክርስቲያናዊ ሕይወት የማጽናትና የማጠናከር እንዲሁም ያላመኑትን በማስተማርና በማሳመን ተልእኮዋን ማሳካት የሚያስችላትን ተገቢውን አደረጃጀት፣ የሰው ኃይልና በጀት ሥርዓትም እንዲኖር በማድረግ ረገድ ቀዳሚ ሓላፊነት እንዳለበት ይተወቃል፡፡
ከዚህም በተጨማሪ ከውስጥ ሆነው የቤተ ክርስቲያኒቱን ተልእኮ በማደናቀፍ ከሌሎች የተለየ ዓላማ ካላቸው ጋር ሽርክና መፍጠር ምእመናንን ከበረታቸው እያስኮበለሉ ባሉት ላይም በቀኖና ቤተ ክርስቲያን መሠረት እርምጃ የሚወስድበትን አቅጣጫ ቅዱስ ሲኖዶስ ማስቀመጥ አለበት፡፡
ቤተ ክርስቲያኒቱ በአስቸኳይ ውስጧን በመፈተሽ ጊዜ እና መስክ ወለድ ለሆኑ መሠረታዊ ፈተናዎችና ችግሮች ዘለቄታ ያለው፣ ተጨባጭና ችግር ፈቺ መፍትሔ ማስቀመጥ አለባት፡፡ ከዚህ አንጻር የቤተ ክርስቲያኒቱ መዋቅራዊ አደረጃጀት መሠረታዊ ተልእኮዋን ለማስፈጸም፣ ቀልጣፋ አሠራርን፣ ግልጽ፣ ሓላፊነትና ተጠቃቂነት ሊያሰፍን በሚያስችል መልኩ አስተዳደራዊ የመዋቅር ማሻሻያ ማድረግ ይኖርበታል፡፡
ሙሉ ሥልጣንና ሓላፊነት ያለው በብፁዓን አበው የሚመራ፣ በሥሩ የተለያዩ ባለሙያ ምሁራንን ያካተተ የአማካሪ ቡድን የሚዋቀርበት አጠቃላይ የቤተ ክርስቲያኒቱን መዋቅራዊ እና አስተዳደራዊ ችግሮችን አጥንቶ የመፍትሔ ሐሳቦችን የሚጠቁም አካል እንዲቋቋም ማድረግ ይኖርበታል፡፡
ቅዱስ ሲኖዶስ የገዳማቱ ሥሪት ገቢያቸውን በራሳቸው እንዲቆጣጠሩ የሚያስችል በመሆኑና ወደ ሀገረ ስብከቶች ወይም ጠቅላይ ቤተ ክህነት የገቢ ፈሰስ እንዲያስገቡ የሚጠይቁ ባለመሆናቸው፤ ያለማንም ጣልቃ ገብነት የልማት ፕሮጀክቶችን በየገዳማቱ በተናጠል የሚሠራበትን አቅጣጫ ማስቀመጥ ለዚህም ሥራ ተስማሚ የሰው ኃይልና በጀት መመደብ፤ የቤተ ክርስቲያኒቱን ልማት የሚመራው አካል መንፈሳዊውን አገልግሎት ከሚመራና ከሚያከናውነው አካል ተለይቶ የልማት አስተደደሩ በቂ ዕውቀትና ልምድ ባለው የሰው ኃይል የሚመራበትን አስተዳደራዊና መዋቀራዊ ሁኔታዎች ማመቻቸት እና ማጠናከር ይኖርበታል፡፡
የቤተ ክርስቲያኒቱ የፋይናንስ አያያዝና አጠቃቀም ሥርዓት ዘመናዊና ወቅታዊ ድርብ የሒሳብ አያያዝን የተከተለ እንዲሁም የበጀት ሥርዐቱም በመደበኛና የካፒታል በጀት ተለይቶ በየዘመኑና በየሥራ ዘርፉ የበጀት ሥርዓት ተግባራዊ የሚሆንበትን፤ በየወቅቱ ሪፖርት እየቀረበበት ግምግማና ክትትል የሚደረግበትን አቅጣጫ ቅዱስ ሲኖዶስ ማስቀመጥ ይኖርበታል፡፡ ከዚህም ጋር አያይዞ ቤተ ክርስቲያኒቱ በማእከላዊነት የሚተዳደር የፋይናንስ አያያዝና አጠቃቀም ሥርዓት እንዲኖራት ማድረግ ወቅቱ የሚጠይቀው አሠራር በመሆኑ በተገቢው ሙያዊ ጥናት መሠረት ተግባራዊ የሚሆንበትን ሁኔታ ማመቻቸት ያስፈልጋል፡፡
የቤተ ክርስቲያኒቱ ላእላይ መዋቅር የሆነው ቅዱስ ሲኖዶስ ከላይ መፍትሔ ይሆናሉ በማለት የተጠቆሙትን ሐሳቦች እንዳላቸው ተጨባጭነትና ተግባራዊነት እንዲጠቀምባቸው አበክረን እንገልጻለን፡፡ ምክንያቱም አደጋው በዚሁ ከቀጠለ ቤተ ክርስቲያኒቱ ዐይናችን እያየ በአጭር ጊዜ ውስጥ በቀሳጮች ተውጣ፣ ታሪካዊና ወቅታዊ ልዕልናዋን አጥታና ሊኖራት የሚገባው ተደማጭነት ተሸርሽሮ አነስተኛ ቁጥር ተከታይ ያላት እንዳትሆን ስለምንሰጋ ነው፡፡ አሁን ያለው ነባራዊ እውነታም የሚያሳየው ይህንኑ ነውና፡፡
እንግዲህ ከላይ ለማሳየት እንደተሞከረው የኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን አሁን ያለችበት ሁኔታ በመጀመሪያዎቹ የክርስትና ዘመናት ከነበረችበት ደረጃ ምን ያህል በችግር የተተበተበ እንደሆነ ብዙ የሚያከራክር አይመስለንም፡፡ ከዚህም በላይ ግን አሁን በምንንደረደርበት አቅጣጫ ከቀጠልን ከዚህም የከፋ ውስብስብና ዘመን ተሻጋሪ ችግሮችን ለመጪው ትውልድና ለነገይቷ ቤተ ክርስቲያን እንዳናስተላልፍ ያሰጋል፡፡ ይህም እንደትውልድ ከታሪክ፣ ከሕሊናና ከእግዚአብሔር ተጠያቂነት አያድነንም፡፡
ይህ ማለት ግን የተሻሉ ዕድሎች የሉም ማለት አይደለም፡፡ ከላይ ለመጠቆም እንደተሞከረው በቅዱስ ሲኖዶስ የመፍትሔ እርምጃዎች ቤተ ክርስቲያኒቱ ያላትን ሀብት በአግባቡ በመጠቀም ወደፊት ሊገጥሙን የሚችሉ አደጋዎችን በተሻለ ብቃት መሻገር እንችላለን፡፡ ይህ ሆኖ እንድናይ ደግሞ አሁን ያለንበትን አካላዊና ሥነ ልቡናዊ ድባብ በመሠረታዊነት ሊቀይሩ የሚያስችሉ ምሁራዊ እይታዎችንና ሒሶችን ማስፋትም ይጠበቅብናል፡፡
ውጤቱም የተጋረጡብንን መሠረታዊ ችግሮች መሻገር ብቻ ሳይሆን በቤተ ክርስቲያኒቱ ላእላይና ታህታይ የሥልጣን መዋቅር የሚቀመጡ የቤተ ክርስቲያኒቱ ልጆች በብቃታቸው፣ በሥነ ምግባራቸው፣ በመንፈሳዊ ተጋድሎ የታወቁ፣ ቤተ ክርሰቲያኒቱን ካለችበት አሰክፊ ችግር በዘላቂነት ለማውጣት ችሎታ፣ እልሁና ርእይ ያላቸው ይሆናሉ ብለን እናምናለን፡፡ አምላከ ቅዱሳን ይህንኑ ያድለን፡፡
ምንጭ፡- ስምዐ ጽድቅ፣ 19ኛ ዓመት ቁጥር 2

ስሞት እጸልይላችኋለሁ

በዲ/ን ሄኖክ ኃይሌ

“ከመውጣቴም በኋላ እነዚህን ነገሮች እንድታስቡ በየጊዜው ትችሉ ዘንድ እተጋለሁ!”2ኛ ጴጥ.1÷13-15

ለስም አጠራሩ ክብር ይግባውና ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ወደዚህ ዓለም በመጣበት ወቅት ቅድስት ቤተ ክርስቲያንን መሥርቶአል፡፡ ቅዱሳን ሐዋርያቱን “እኔን ማን ትሉኛላችሁ?” ብሎ በጠየቃቸው ጊዜ “አንተ ክርስቶስ የሕያው እግዚአብሔር ልጅ ነህ” ብሎ ቅዱስ ጴጥሮስ መልሶ ነበር፡፡ ከዚህም በኋላ “አንተ ዓለት ነህ በዚህችም ዓለት ላይ ቤተ ክርስቲያኔን እሠራታለሁ፤ የሲኦልም ደጆች ሊያናውጿት አይችሉም፡፡” በማለት ቤተ ክርስቲያንን በሐዋርያት መሠረት ላይ መሠረተ/ማቴ.16÷16-18/፡፡

ቅዱስ ጴጥሮስ በአምሳ አምስት ዓመቱ ወደ ሐዋርያት የተጠራ፣ በሁሉም ስፍራ በሐዋርያት ስም ዝርዝርም፣ መልስ በመስጠትም፣ በመካድም፣ ንስሓ በመግባትም ፈጣን እንደነበር ቅድመ ትንሣኤ ክርስቶስ የተጻፈው ታሪኩ ያስረዳል፡፡ ከትንሣኤ በኋላ ሦስት ጊዜ ክዶት መጸጸቱን የተመለከተለት ጌታ አንዳች የሚቆጠቁጥ የወቀሳ ቃል ሳይኖረው በጭቃ ላይ የወደቀ ዕንቁን ወልውለው ወደ ቦታው አንደሚያስቀምጡት ወደ ክብር ስፍራው መለሰው፡፡ አልፎ ተርፎም ለምሕረቱ ወሰን የሌለው አምላክ ይህን ሐዋርያ “ ግልገሎቼን አሰማራ፣ ጠቦቶቼን ጠብቅ፣ በጎቼን አሰማራ” ብሎ ምእመናንን ከሕፃናት እስከ አረጋውያን አደራ ሰጠው /ዮሐ.21÷15-17/፡፡ቅዱስ ጴጥሮስ ጸጋ መንፈስ ቅዱስን በተቀበለበት ዕለት በአንድ ቀን ሦስት ሺህ ነፍሳትን በትምህርቱ ማርኮ “ምን እናድርግ?” በማሰኘት ጠብቅ አሰማራ የተባለውን መንጋ ወደ በረቱ ማስገባት ጀመረ፡፡ /ሐዋ.2÷31/ በሐዋርያዊ አገልግሎቱ ምእመናንን በአፍም በመጽሐፍም ሲያስተምር ቆይቷል፡፡ በኋላም ጠብቃቸውና አሠማራቸው የተባለውን ግልገሎች፣ ጠቦቶችና በጎች ሲጠብቅና ሲያሠማራ ከተኩላ ታግሎ ነፍሱን ሰጠ፡፡ የእረኝነት ሥራውን ሊፈጽም ቁልቁል ተሰቅሎ “የእረኞች አለቃ” /1ኛጴጥ.5÷4/ ብሎ በመልእክቱ የጠራውን የጌታውን ፈቃድ ፈጸመ፡፡

ይህ ሐዋርያ በመልእክታቱ ምእመናንን ሲገሥጽና ሲመክር ሲያስተምር የኖረ ሲሆን በሁለተኛይቱ መልእክቱ ላይ ግን ለዚህ ጽሑፍ መነሻ የሆነ ኃይለ ቃልን ጽፏል፡፡ “ስለዚህ እነዚህን ነገሮች ምንም ብታውቁ በእናንተም ዘንድ ባለ እውነት ብትጸኑ ስለ እነዚህ ዘወትር እንዳሳስባችሁ ቸል አልልም፡፡ ሁል ጊዜም በዚህ ማደሪያ ሳለሁ በማሳሰቤ ላነቃችሁ የሚገባኝ ይመስለኛል፤ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ እንዳመለከተኝ ከዚህ ማደሪያዬ መለየቴ ፈጥኖ እንዲሆን አውቃለሁና፡፡ ከመውጣቴም በኋላ እነዚህን ነገሮች እንድታስቡ በየጊዜው ትችሉ ዘንድ እተጋለሁ” /2ኛጴጥ. 1÷13-15/

ብታውቁም፤ ብተጸኑም ማሳሰቤን ቸል አልልም!

ቅዱስ ጴጥሮስ በመልእክታቱ ስለ ክርስቶስ የባሕርይ አምላክነትና ስለ ሰው ልጅ ብሎ ስለተቀበለው መከራ፣ ክርስቲያኖች ሊኖራቸው ስለሚገባ መንፈሳዊ አኗኗር፣ አለባበስ፣ ስለ ጋብቻና ቤተሰባዊ ጉዳዮች፣ በምእመናን ላይ ስለሚመጡ መከራዎችና የዲያብሎስ ውጊያዎች፣ ድል ሲያደርጉም ስለሚያገኙት ጸጋና ዋጋ፣ ስለሚደርሱበት መዓርግ በአጠቃላይ በቀላሉ ተዘርዝሮ የማያልቅ ሰፊ ትምህርትን በመልእክቱ አስተምሯል፡፡ ይሁንና ሐዋርያው አውቀውታል፣ ጸንተዋል ብሎ ማሳሰቡን አላቆመም፡፡ ሰው ከመንገድ የሚስተው በእውቀት ጉድለት ብቻ አይደለም፡፡ እያወቁ መሳት፣ ጸናሁ ሲሉም መጥፋት አለ፡፡ ስለዚህም “አሳስባችሁ ዘንድ ቸል አልልም፡፡” አለ፡፡ ቅዱስ ጴጥሮስ መንጋውን ጠብቅና አሰማራ የተባውን አደራ የማይረሳ፣ በጥበቃ ተሰላችቶ ቸል የማይል፣ ትናንት የበሉት የጠጡት ይበቃቸዋል የማይል በመሆኑ ያውቁታል ብሎ ከመናገር ሳይቆጠብ “ዘወትር እንዳሳስባችሁ ቸል አልልም፡፡” አለ፡፡

በዚህ ማደሪያ ሳለሁ!

ሥጋ የነፍስ ማደሪያ ናት፤ አዳሪዋ ነፍስ ከማደሪያዋ ሥጋ ስተለይ ሰው ያን ጊዜ ሞተ ይባላል፡፡ “ከነፍስ የተለየ ሥጋ የሞተ ነው” እንዲል /ያዕ.2÷26/ ጻድቁ ኢዮብም “ይህ ቁርበቴም ከጠፋ በኋላ÷ በዚያን ጊዜ ከሥጋዬ ተለይቼ እግዚአብሔርን እንዳይ አውቃለሁ፡፡” ኢዮ.19÷26/ ያለው ሥጋ ጊዜያዊ ማደሪያ መሆኑን ሲያስረዳና ራሱን ከነፍስ አንጻር አድርጎ በሞት ሥጋውን ጥሎ እንደሚሄድ ሲናገር ነበር፡፡

ቅዱስ ጴጥሮስ “በዚህ ማደሪያዬ ሳለሁ በማሳሰቤ ላነቃችሁ ይገባኛል፡፡” ሲል በሥጋዬ ሳለሁ፣ ነፍሴ ሳትወሰድ ማለቱ ነበር፡፡ ቅዱስ ጴጥሮስን ቀሪ ዕድሜውን በችኮላ የሚጠቀመው ለሌላ ሥጋዊ ተርታ ጉዳዮች ሳይሆን ምእመናን ያስተማረውን ትምህርት እንዳይገድፍና አንዳይጠፉበት በማሳሰብ ማንቃት ነው፡፡

ጌታዬ እንዳመለከተኝ መለየቴ ፈጥኖ እንዲሆን አውቃለሁ!

“በእግዚአብሔር ፊት የቅዱሳኑ ሞት የከበረ” ስለሆነ ሞት ለቅዱሳን ድንገተኛና ያልተጠበቀ አይሆንባቸውም፡፡ እርግጥ ነው ሰው ሁሉ ሟች እንደ ሆኑና የሞትን አይቀሬነት በመጥቀስ ሁሉም ሰው እንደሚሞት ያውቃል ሊባል ይችላል፡፡ ቅዱሳን ግን የሚሞቱ መሆናቸውን የሚያውቁት ሞት አይቀርም ብለው ሳይሆን የሚሞቱበትን ጊዜና ሁኔታ ለመረጣቸው ለባሪያዎቹ የሚያደርገውን የማይሠውር እግዚአብሔር ገልጣላቸው ነው፡፡ የሚከተሉት የሊቀ ነቢያት ሙሴንና የቅዱስ ጳውሎስን ንግግሮች እንመልከት፡-

“እኔ ግን በዚህች ምድር እሞታለሁ ዮርዳኖስንም አልሻገርም” /ዘዳ.4÷22/

“በመሥዋዕት እንደሚደረግ የእኔ ሕይወት ይሠዋልና የምሄድበትም ጊዜ ደርሷል” /2ኛጢሞ.4÷6/

እነዚህ ታላላቅ ቅዱሳን የሚሞቱ መሆናቸቸውን ብቻ ሳይሆን የሚሞቱበትን ቦታ ጊዜ አስቀድመው መናገራቸው ከእግዚአብሔር ስለተነገራቸው ነው፡፡ የቅዱሳን አባቶቻችንን እና የቅዱሳት እናቶቻችንን ገድላት ስንመረምር ቅዱሳን ዕለተ እረፍታቸው ቀድሞ በእግዚአብሔር እንደሚነገራቸው እንረዳለን፡፡

ቅዱስ ጴጥሮስም ሰው እንደመሆኑ “መሬት ነህና ወደ መሬት ትመለሳለህ” ብሎ ጌታ ለሁሉ ካመለከተው ጥሪ በተጨማሪ ከቅዱሳን አንዱ እንደመሆኑ ከመሞቱ በፊት እንደሚሞት ያውቅ ነበር፡፡ ጌታችን ከዕርገቱ በፊትና ከዕርገቱ በኋላ ሁለት ጊዜ ተገልጦ ስለሞቱ ነግሮታል፡፡

ከዕርገቱ በፊት ከላይ የጠቀስነውን የእረኝነት አደራ ከሰጠው በኋላ “እውነት እውነት እልሃለሁ አንተ ጎልማሳ ሳለህ ወገብህን በገዛ ራስህ ታጥቀህ ወደምትወደው ትሄድ ነበር፤ ነገር ግን በሸመገልህ ጊዜ እጆችህን ትዘረጋለህ ሌላውም ያስታጥቅሃል ወደማትወደውም ይወስድሃል፡፡” ብሎታል፡፡ ወንጌልን ጽፎ በብዙ ቦታዎች የጻፈውን ሲተረጉምና ሲያትት የምናገኘው ቅዱስ ዮሐንስ ወንጌላዊ ትርጓሜን ሳንሻ ንባቡ ላይ “በምን ዓይነት ሞት  እግዚአብሔርን ያከብር ዘንድ እንዳለው ሲያመለክት ይህን አለ፡፡” ብሎ የጌታን ንግግር ትርጓሜ አስከትሎ ጽፎልናል፡፡

በእርግጥም ቅዱስ ጴጥሮስ በሸመገለ ጊዜ እጆቹን በተዘቀዘቀ መስቀል ላይ ዘርግቶ ቁልቁል መሰቀል ትንቢተ ክርስቶስን ፈጽሟል፡፡

ጌታችን ከዐረገ በኋላ ደግሞ ቅዱስ ጴጥሮስ በሮም ሲያስተምር “ልበ ንጹሖች ብጹዓን ናቸው፡፡” ብሎ ባስተማረው ትምህርት ሚስቶቻችንን አሸፈተብን ያሉ ሰዎች ተነሡበት፡፡ በዚህን ወቅት ሴቶቹ ተማክረው ቅዱስ ጴጥሮስ እንዲሸሽ ነገሩት ከከተማይቱ ወጥቶ ሊሄድ ሲል ጌታችን ተገልጦ ታየው “ጌታ ሆይ ወዴት ትሄደለህ” ቢለው “ዳግም በሮም ልሰቀል” በማለት ነገረው፡፡ ቅዱስ ጴጥሮስ በዚህ ልቡ ተነክቶ ወደ ሮም ተመለሰና የሰማዕትነትን አክሊል ተቀዳጀ፡፡ “ጌታችን እንዳመለከተኝ” ያለው ይህን ነበር፡፡

ከመውጣቴም በኋላ አንድታስቡ በየጊዜው ትችሉ ዘንድ እተጋለሁ!

ከላይ የተመለከትናቸው ሃሳቦች ቅዱስ ጴጥሮስ ጊዜ ሞቱ እንደቀረበ አውቆ መናገሩን እና ምእመናን የተማሩትን በማሳሰብ ሲያነቃቸው እንደነበር የሚያስረዱ ናቸው፡፡ እስካሁን የተመለከትናቸው የሚያወሱት ይህ ሐዋርያት በሕይወት ሳለ ስለሚያደርጋቸው ነገር ነበር፡፡ በመጨረሻው ዐረፍተ ነገር ግን “ከመውጣቴ በኋላ የሚል ሐረግ እናገኛለን፡፡ “ከመውጣቴ በኋላ” ሲል ምን ማለቱ ነው?

ቀደም ባሉት ዐረፍተ ነገሮች እንደሚሞትና ይህንንም ጌታችን እንዳመለከተው ተናግሮ ነበር፡፡ ስለዚህ መውጣቴ ያለው ሞቱን እንደ ሆነ እሙን ነው፡፡ በመጽሐፍ ቅዱስ ሞት መውጣት ተብሎ ሲነገር የቅዱስ ጴጥሮስ የመጀመሪያ አይደለም፡፡ በታቦር ተራራ ከሙሴና ኤልያስ ጋር ስለመነጋገሩ በተጻፈበት ስፍራ “በክብርም ታይተው በኢየሩሳሌም ሊፈጽም ስላለው ስለ መውጣቱ ይናገሩ ነበር” ይላል፡፡ በኢየሩሳሌም የተፈጸመው መውጣቱ ደግሞ ሞቱ ነው፡፡ /ሉቃ.9÷31/ ስለዚህ ቅዱስ ጴጥሮስ ባስተማርኳችሁ እንድትጸኑ “ከሞትኩም በኋላ እተጋለሁ!” እያለ ነው፡፡ “ከሞትኩ በኋላ” የሚለውን እናቆየውና “እተጋለሁ!” የሚለውን ቃል በጥቂቱ እናብራራው፡፡

ትጋት ምንድርን ነው? ትጋት አንድ ነገር ያለማቋረጥ፣ ደከመኝ ሰለቸኝ ሳይሉ፣ ያለመታከት ማድረግ ነው፡፡ ጠቢቡ ሰሎሞን “ታካች ሰው ምንም አደን አያድንም፤ የሰው የከበረ ሀብቱ ትጋት ነው” በማለት ትጋት የታካችነት ተቃራኒ መሆኑንና ጥቅሙን ተናግሯል /ምሳ.12÷27/፡፡ ጌታችን በምሴተ ሐሙስ ቅዱሳን ሐዋርያቱን “ከእኔ ጋር አንዲት ሰዓት እንኳን ልትተጉ አልቻላችሁምን? ወደ ፈተና እንዳትገቡ ትጉና ጸልዩ” ብሎ ገሥጿቸው ነበር /ማቴ.26÷30/፡፡ ጸጋ መንፈስ ቅዱስን ከተቀበሉ በኋላ ግን ሐዋርያት ትጉሐን ነበሩ፡፡ ቅዱስ ጳውሎስ እንደ መሰከረላቸው “ወደዚህም ወደ ተሰፋ ቃል አሥራ ሁለቱ ወገኖቻችን ሌሊትና ቀን በትጋት እያመለኩ ይደርሱ ዘንድ አለኝታ አላቸው” /ሐዋ.26÷7/ በዚህ ሁሉ ትጋት አለመታከት፣ አንድን ነገር ሌሊትና ቀን ማድረግ መሆኑን ተረዳን፡፡

ቅዱስ ጴጥሮስ “ከመውጣቴም በኋላ እነዚህን ነገሮች እንድታስቡ በየጊዜው ትችሉ ዘንድ እተጋለሁ” ሲል የሚተጋው በምንድርን ነው? እየዞረ በማስተማር ይሆን? ይህማ ቢሆን ከመሄዴ በፊት  ላሳስባችሁ ባላለን ነበር፡፡ ደግሞም ማስተማሩን በሚገባ ፈጽሞ በሰማዕትነት አርፏል፡፡ ታዲያ ከሞተ ወዲያ የሚተጋው ምን በማድረግ ነው? የትስ ነው የሚተጋው? መቼስ በመቃብር ያለሥጋው ሊተጋ አይችልም፡፡ “የሞቱትስ ተነሥተው ያመሰግኑሃልን? በመቃብርስ ውስጥ ቸርነትህን ይናገራሉን?” ብሏል ቅዱስ ዳዊት /መዝ.87÷15/ ራሱ ቅዱስ ጴጥሮስም “ከማደሪያዬ እለያለሁ፡፡ ብሎ ከሞተ ወዲያ እኔ የሚላት ነፍሱን እንደሆነ አስረድቶናል፡፡ ታዲያ በነፍሱ በሰማይ ምን እያደረገ ይሆን የሚተጋው? መቼስ በሰማይ እርሻ ቁፋሮ፣ ጽሕፈት፣ ድጒሰት የለም፡፡ ሐዋርያው በምን ይሆን የሚተጋው? በጸሎት ነዋ!

ስለዚህ ቅዱስ ጴጥሮስ “እንደተማራችሁት መኖርን እንዳትዘነጉ በየጊዜው /አንድ ጊዜ ብናስብ አንድ ጊዜ መዘንጋት አለና/ ትችሉ ዘንድ ከሞትኩም በኋላ ያለማቋረጥ ያለመሰልቸት ስለ እናንተ በመጸለይ እተጋለሁ! ማስተማርና መልእክትን ጽፎ መተው ብቻ ሳይሆን በተማራችሁት መገኘት እንድትችሉ በአጸደ ነፍስም ብሆን እለምናለሁ፣ እማልዳለሁ! እያለ ነው፡፡

በቅዱስ ጴጥሮስ ዓለትነት የተመሠረተችው ቅድስት ቤተ ክርስቲያን በአደባባይ ስለእርሷ የተጻፋላት፣ በደሙ የዋጃት አምላካችን ኢየሱስ ክርስቶስ ራሷ ነው፡፡ እርሱ በሁሉ የሞላ ሲሆን “ሁሉን በሁሉ ለሚሞላ ለእርሱ ሙላቱ የሆነች” አካሉ ቅድስት ቤተ ክርስቲያን ናት /ኤፌ.1÷22/፡፡ ቤተ ክርስቲያን የክርስቶስ አካሉ ስትሆን ክርስቶስ ደግሞ የቤተ ክርስቲያን ራሷ ነው፡፡ እኛ ደግሞ የሰውነት አካል ክፍሎች ነን፡፡ “እንግዲህ እናንተ የክርስቶስ አካሉ ናችሁ፤ እያንዳንዳችሁ የአካሉ ክፍሎች ናችሁ፡፡” ተብለናል /1ኛቆሮ.12÷27/፡፡ በቤተ ክርስቲያን ሕይወትን የሚሰጡ ጥምቀትን፣ ንስሐን፣ ቊርባንን የመሳሰሉ ምስጢራትን በመፈጸም ራሳችን ከሆነው ከመድኃኔዓለም ጋር አንድ እንሆናለን፡፡

ክርስቲያኖች ሲሞቱ ከዚህ ኅብረት ይነጠላሉ ማለት አይደለም፡፡ ራሷ ክርስቶስ በሰማይም በምድርም ስላለ ቤተ ክርስቲያንም በምድርም በሰማይም አለች፡፡ ስለዚህ አንድ ክርስቲያን ነፍሱ ከሥጋው ስትለይ ወደ ሰማያዊቱ አጥቢያ ቤተ ክርስቲያን ይሄዳል፡፡ የሰማይዋ ቤተ ክርስቲያን ደግሞ ድል በነሱ ቅዱሳን የተሞላች ፍጹም መንፈሳዊ የሆነ ሥርዓት ያለባት፣ ሥጋዊ ደማዊ አሳብ የማይሰለጥንባት ናት፡፡ ከእኛ ተለይተው ወደዚያ ኅብረት የተደመሩ ወገኖቻችን በላይ ያሉ የክርስቶስ አካላት ናቸው፡፡ ከእኛ በምድር ካለነው የክርስቶስ አካላት ጋር አንድነታቸው አይቋረጥም፡፡ የክርስቶስ አካል አይከፈልማ! ስለዚህ በሰማይ ካሉት ድል የነሡ ቅዱሳን ጋር እኛ ደካሞቹ በጸሎት እንገናኛለን፡፡

“ዐይን እጅን አልፈልግሽም ልትላት አትችልም፤ ደካሞች የሚመስሉህ የአካል ክፍሎች ይልቁንም የሚያስፈልጉህ ናቸው፡፡ ተብሎ እንደተነገረ እኛ ኃጢአተኞቹ የቤተ ክርስቲያን የአካል ክፍሎች ብንሆንም ቅዱሳኑ ስለ እኛ ይጸልያሉ /1ቆሮ.12÷21/፡፡ ምክንያቱም ደካማ ብንሆንም ለቅዱሳን እናስፈልጋቸዋለን፡፡ ቅዱሳን ኃጥአንን ካልወደዱ ቅድስናቸውን ያጣሉ፡፡ እኛን ካልወደዱ “እኔ ክርስቶስን እንደመሰልሁ እናንተም እኔን ምሰሉ” “አሁን እኔ ሕያው ሆኜ አልኖርም፤ ክርስቶስ ግን በእኔ ይኖራል፡፡” ብለው ለመናገር እንደምን ይችላሉ? /ገላ.2÷20/  

እኛ በሥጋ ድሆች የሆኑ ነዳያንን በመመጽወት እንደምንከብር ቅዱሳንም በነፍስ ድሆች የሆንን እኛን በአማላጅነት ጸሎታቸው እየመጸወቱ ይከብራሉ፡፡ መጽሐፍ ቅዱስ “ለድሀ ግን የሚራራ ምስጉን ነው፡፡” ይላልና በምግባር ድሆች ለሆንን ለእኛ መራራት የቅዱሳን ግብር ነው፡፡ “ጻድቅ ሰው ለእንስሳው ነፍስ ይራራል” ተብሎ እንደተነገረላቸው ቅዱሳን ክቡር ሆነን ሳለን ለማናውቅ እንደሚጠፉ እንስሶች ለመሰልን ለእኛ ለኃጢአተኞች ይራራሉ፤ ይማልዱማል /ምሳ.12÷10፣ 14÷21/፡፡

ቅዱሳን በሕይወተ ሥጋ እያሉ መከራን ታግሠው ስለ ሌሎች በደል ይለምናሉ፡፡ ሳይበድሉ ራሳቸውን በኃጢአትኛው ቦታ አርገው፣ ከደካሞች ጋር እንደ ደካማ ሆነው ይማልዳሉ፡፡ ታዲያ ነፍሳቸው ከሥጋቸው ተለይታ “ሲሄዱና ከክርስቶስ ጋር ሲኖሩ” /ፊል.1÷23/ ምንኛ ይለምኑ ይሆን?

በምድር ያለችው ቤተ ክርስቲያን በሕይወተ ሥጋ ለሌሉና ወደ ሰማዩ ኅብረት ለሄዱ ምእመናን ጸሎተ ፍትሐትን፣ መታሰቢያን በማድረግ፤ ለዚያ የሚያበቃ ቅድስና ያላቸውን ደግሞ በዓላቸውን በማክበር ታስባቸዋለች /2ጢሞ.1÷17-18/፡፡ በሰማይ ያሉት ቅዱሳን ደግሞ ቅዱስ ጴጥሮስ እንዳለው ስለ እኛ ይተጋሉ፡፡ የቤተ ክርስቲያንን መከራና የምእመናንን ስቃይም በዝምታ አይመለከቱም፡፡ በዙፋኑ ፊት ቆመው “ቅዱስና እውነተኛ ጌታ ሆይ እስከ መቼ ድረስ አትፈርድም? ስለ ደማችንስ በምድር በሚኖሩት ላይ እስከ መቼ አትበቀልም?” እያሉ ያማልዳሉ፡፡ /ራእ.6÷10/ የቅዱስ ጴጥሮስ በረከቱ አይለየን! አሜን፡፡

/ምንጭ፡ ሐመር  ሐምሌ 2002 ዓ.ም./

ክርስቶስን መስበክ እንዴት?

ሚያዚያ 25፣ 2003ዓ.ም

/ምንጭ፦ ሐመር መጽሔት ሚያዝያ 2003ዓ.ም/

ፕሮቴስታንቶችና ፕሮቴስታንታዊ መንገድ የሚከተሉ አንዳንዶች  የኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን ወንጌልን አልሰበከችም የሚል ክርክር ይዘው ይቀርባሉ፡፡ ዝግጅት ክፍላችን ጥያቄያቸውን ለመመለስ ሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያንና ምእመናንን በምላሹ እንዲሳተፉበት ጋብዘናል፡፡ ለዚህ እትም የያዝነውን እነሆ!

ሊቀ ጠበብት ሐረገወይን አገዘ“ቤተክርስቲያናችን ዘመናትን የተሻገረችበት ኃይሏ ወንጌል ነው”

ቤተክርስቲያን ወንጌልን ስትሰብክ ሁለት ሺሕ ዓመታት አልፏታል። ይህንንም ሊቃውንቱ ምእመናንም ያስረዱትና የተረዱት ነው። ወንጌል ካልተሰበከ ክርስቲያኖች እንዴት ለአሁን ዘመን ደረሱ? ወንጌል መሠረት፣ በጎ እርሾ ሳይሆነው፣ ወንጌል ብርታት ሳይሆነው ይህን ሁሉ ዘመናት አቆራርጦ፣ ድልድዩን አልፎ እንዴት እዚህ ደረሰ? ወንጌል ቤተ ክርስቲያናችን ዘመናትን የተሻገረችበት ኃይሏ ነው፡፡

 

በቤተክርስቲያን ሊቃውንቱ የሚያነቧቸው፣ የሚተረጉሟቸው፣ ምእምናን የሚሰሟቸው፣ የሚታነጹባቸው ድርሳናት፣ ተአምራት ወንጌል ናቸው። እነዚህ መጻሕፍት ወንጌልን የሚፈቱ፣ የሚተረጉሙ፣ የሚያመሰጥሩ ናቸው። ከዚህ ውጭ የሆኑ መጻሕፍት በቤተክርስቲያን አይነበብም፣ አይተረጎምም፣ አይሰማም። ቤተክርስቲያን ወንጌልን የምትሰብከው በቃል፣ በመጽሐፍ ብቻ ሳይሆን በድርጊትም ነው። ጥምቀት ወንጌል ነው። ቤተክርስቲያንም ጥምቀት የዘወትር ሥራዋ ነው። ወንጌል ስለ ጥምቀት ነው የሚነግረን። የክርስቶስ ቅዱስ ሥጋውን ክቡር ደሙም በየዕለቱ ይቀርባል፤ ይህ ወንጌል ነው። ወንድሞቻችን፣ እኅቶቻችን የተቀደሰውን ጋብቻቸውን በተቀደሰው ቦታ፣ በተቀደሰው ጸሎት በምስጢረ ተክሊል ይፈጽማሉ። ይህም ወንጌል ነው። እናቶቻችን፣ አባቶቻችን፣ ወንድሞቻችን፣ እኅቶቻችን ከዚህ ዓለም ሲሸኙ በሥርዐተ ፍትሐት፤ ብሉያትና ሐዲሳት እየተነበቡ፣ ያሬዳዊ ዜማ እየተዜመ ነው። ይህ ወንጌል ነው። አላዛርን ከመቃብር ተነሥ እንዳለው፤ የታሰረበትን ፍቱት እንደተባለ እንደተ ፈታ ሁሉ፤ ካህናትም ከኃጢአት እስራት እየፈቱ ሕዝባቸውን መሸኘት፤ “አቤቱ እግዚኦ ይቅር በለው ሲያውቅ፣ ሳያውቅ በሠራው ኃጢአት ይቅር በለው” እያሉ መሸኘት ወንጌል ነው።

ቤተክርስቲያን ራሷም፣ እግሯም፣ መሠረቷም፣ ጉልላቷም ወንጌል ነው። ይህን በቅንነት፣ በበጎ ነገር፣ በምስጢር፣ በትርጓሜ ለሚያዩት ነው። በጥላቻ ካዩት ነጩም ጥቁር ነው፤ ብርሃኑ ጨለማ ነው፤ በጥላቻ ማየትና በፍቅር ማየት፤ በሐሰት መናገርና በእውነት መናገር መካከል ሰፊ ልዩነት አለ። የቤተክርስቲያን ጥንተ ጠላቶች ለቤተክርስቲያን በጎ ይመሰክራሉ ብለን ከጠበቅን የተሳሳትን ይመስለኛል። መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ጸሐፍት ፈሪሳውያንን “እግዚአብሔር ከእናንተ  ምስክርነትን አይፈልግም” ነው ያላቸው። ጸሐፍት ፈሪሳውያን ስለ ክርስቶስ በጎ ስለማይመሰክሩ ስለማይናገሩ ነው። ምክንያቱም በጭፍን፣ በቅናት፣ ስለጠሉት ነው። ቤተክርስቲያንም ከጠላቶቿ የእውነት ምስክርነትን አትጠብቅም፤ በበጎ ለሚያዩአት ግን ምስክርነቱ በእጅ የሚጨበጥ (የሚዳሰስ) በዐይነ የሚታይ ነው።

ቤተክርስቲያን ወንጌል ያልሰበከችበት ዘመንም፣ ጊዜም የለም። ወንጌል አልተሰበከም ለሚሉ ሰዎች ትናንት አለነበሩም፣ ዛሬም የሉም። ለነገሩስ የት ሆነው ያዩታል? ቢኖሩም አይገባቸውም፤ ውስጣቸውም በብዙ ችግር የተተበተበ፤ በቅራኔ የተሞላ ነው። በቅራኔ የተሞላ ደግሞ ከውጭ የሚነገረውን በጎ ነገር ለመቀበል ዝግጁ አይደለም።

 

ሊቀ ትጉኀን ኃይለ ጊዮርጊስ ዳኜ“ቤተክርስቲያን ክርስቶስን የምትሰብከው በቃል ብቻ ሳይሆን በድርጊትም ነው”

ሰው በተሰጠው የፈቃድ ነጻነት መሠረት የፈለገውን የመናገር መብት አለው። ፍሬ ነገሩ እውነቱ የቱ ነው? ሐሰቱስ? የሚ ለው ነው። ዲያብሎስ ስለ ቅዱስ ሚካኤል የብርሃን መላክነት አይመስክርም፤ ሊመሰክርም አይችልም። «ሚካኤል ደካማ ነው» እያለ የፈለገውን መናገር ይችላል። የዲያብሎስን ምስክርነትም ሚካኤል አይፈልገውም፣ አይቀበለውምም። ዲያበሎስ የፈለገውን ቢናገር ሚካኤልን አይከፋውም፤ ከጠላቱ ቡራኬ ስለማይጠብቅ። እንደዚሁ ሁሉ የእኛም ቤተክርስቲያን የሌሎችን ቤተእምነቶች ምስክርነትም ሆነ ክስ አታደንቀውም፤ አትደነግጥበትምም የእኛ ቤተክርስቲያን ጨርቅ ሰጥታ ጉቦ ሰጥታ እንዳልተስፋፋች ሁሉም ያውቁታል፤ ታዲያ ወንጌልና ክርስቶስን ሳትሰብክ ቤተክርስቲያን ሆና ሁለት ሺሕ ዓመታትን እንዴት ተሻገረች? አሸናፊ ስለሆነች በእውነቷ ብቻ ቆማ የምትኖር ናት። ጉቦ አይከፈልባትም፣ ማባበያም አትጠይቅም።

 

ቤተክርስቲያን ክርስቶስን የምትሰብከው በቃል ብቻ ልብን አሻክሮ ምላስን አለዝቦ በማነብነብ አይደለም፤ በድርጊት በማሳየትም እንጂ። በአንድ ታላቅ ዓመታዊ ክብረ በዓል በአንድ ቤተክርስቲያን በአንድ ቀን ብቻ የምናደርገው ስብሐተ እግዚአብሔር፤ ስብከቱ፣ ቅዳሴው፣ ማኅሌቱ፣ ዋዜማው በተግባርም ታቦት ይዘን ቆመን ያስተላለፍነው ትምህርት በጠቅላላው መናፈቃኑ ለአንድ ዓመት ከጮኹበት፣ ብዙ ነገር ካወጡበት «አገልግሎት» እጅግ ብልጫ አለው። የዚህ አጠቃላይ አገልግሎታችን ዋነኛ ማእከልም ወንጌልና የጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ነገረ ድኅነት ነው፡፡ ንዋያተ ቅድሳቶቻችን በሙሉ ስብከቶች ናቸው። በቅዳሴ ላይ ቄሱ፣ ዲያቆኑ መስቀል ይዞ የሚዞረው ምን  ለማሳየት ነው? ቀሳውስት ዕጣን እያጠኑ “ስብሐት ወክብር ለሥሉስ ቅዱስ” እያሉ ሲያመሰግኑ ምስጢረ ሥላሴ እና ምስጢረ ሥጋዌን መስበከ፣ ማስተማራቸው ነው። ልብሰ ተክህኖዎቹ ከታቦተ ሕጉ ጀምሮ ንዋያተ ቅድሳቱ ሁሉ መስቀል የሚደረግበት ለጌጥ አይደለም። ይህ ስብከት አይደለም እንዴ? መቅደስ ውስጥ ስንቀድስ በአራቱ ማእዘን የምንቆመው ጽርሃ አርያምን እያሳየን ነው። እነርሱ የማያስተውሉትን ሰባቱ ሰማያትን አምጥተን መቅደሱ ላይ ቁጭ አድርገን የምናሳያቸው ለስብከት ነው። ኪሩቤል እንዴት አድርገው ጌታን እንደተሸከሙት ታቦቱን መንበሩ ላይ አስቀምጠን ስንቀደስ እናሳያለን። በተጨባጭ እያሳየን እያሰተማርን ነው።

 

ደስ ሊለን ይገባል፤ ለሁለት ሺሕ ዘመን ወንጌል ሳይነበብባት በተለያየም መንገድ ሳይሰበክባት የማትውል የማታድር እንደ ሀገር ኢትዮጵያ እንደ ቤተክርስቲያንም የኢትዮጵያ ቤተክርስቲያን ነች። ቢያንስ በቅዳሴ ላይ ሰባኪ ያልቆመባቸው፣ ወንጌል ያልተሰማባቸው፣ ሃይማኖት አበው የማይነበብባቸው ገዳማትና አብያተክርስቲያናት የሉም። ስለዚህ ስብከት መንዘፍዘፍና ዓላማ የሌለው ጩኸት አይደለም። በእርጋታ፣ በማስተዋል፣ በጥንቃቄ የሚፈጸም በብዙ ዓይነት መንገድ የሚከናወን፤ ያልነበሩትን የምናመጣበት የነበሩትን የምናጸናበት አገልግሎት መሆኑን ሁሉም ይረዳ።

?

በዲ/ን እሸቱ

ሚያዝያ 26፣2003ዓ.ም

ሰው ማነው?ሰው ማነው? ብሎ ለጠየቀ “ሰው ንግግሩን ይመስላል” እንዳትለኝ ንግግሩ እምነቱን የሚያመለክት ዕውቀት አይሆነውምና ነው፡፡ ለሰው ባሕርያዊ ተፈጥሮና ዕውቀት ምስክሩ ውስጣዊ የአዕምሮ አቋምና የሕሊና ሕግ ነው ብለንም አንደመድምም፡፡ ሰው እንዲያውቅ የተመደበለት የሕግ ተፈጥሮ ዕውቀት መጀመሪያ ክፍል መልካምን ማወቅ፡፡ ሁለተኛ ክፋትን ንቆ መልካምን ገንዘብ ማድረግ፡፡ ሦስተኛ መልካምን በግብር መግለጽ ናቸው፡፡ የቤተ ክርስቱያን ሊቃውንት ይሁዳን ሲገልጹ “በአፍ አምኖ በልቡ የካደ” ይሉታል፡፡ ባህላችን “አፈ ቅቤ፤ ሆደ ጩቤ” እንዲል፡፡

 

የክርስቲያናዊ ሥነ ምግባር መሠረት ያለ ትምህረት በተፈጥሮ የሚሰጥ ሲሆን ይህም ሕገ ልቦና፤ ሕገ ህሊና፤ ሕገ ተፈጥሮ ወይንም ሕገ ጠብዓያዊ በመባል ይታወቃል፡፡ ሕገ ኦሪትና ሕገ ወንጌል፤ ሕገ ሕሊናን ይተረጉማሉ፡፡ ለአብነት ብንጠቅስ አዳምና ሔዋን ቅዱስ ዳዊትና ይሁዳን፤ ከመጸጸት ክፉዎችን ከማዘን የምታደርሳቸው የሕሊና ኮሽታ ነች፡፡ በኑሮ ሂደት ሀዘን፣ ጸጸት ርትዕ በምናደርግበት ጊዜ ልዩ መንፈሳዊ ጥበብ አልያም ዕውቀት በመታደል ሳይሆን ሰው በመሆናችን በሕሊና ውስጥ የተቀረጸ በህሊና ሚዛን የሚሰጥ ፍርድ በመኖሩ ነው፡፡ ከዚህም በተጨማሪ ሕገ ሕሊና በጽሑፍ ከተሰጡን ሕግጋት /ሕገ ኦሪት፣ ሕገ ወንጌል፣ ማሕበራዊ ሕግ/ በላይ ሰማያዊና ምስጢርን ለመጠበቅ ሲያገለግል እናገኘዋለን፡፡ የቤተ ክርስቲያን የሀገር የግል ምስጢር ይጠበቅ ዘንድ መንፈሳዊ ሕግና ማህበረሰባዊ ሕግ ይደነግጋል፡፡ የአምላክ እናት ድንግል ማርያም ያለ ምድራዊ ሕግ አስገዳጅነት በሕገ ልቦና ዳኝነት ለሰማያዊ ምስጢር የታመነች ነበረች “እናቱ ማርያም በልቧ ትጠብቀው ነበር” እንዲል፡፡ /ሉቃ.2÷19/፡፡

 

 

ሰው ራሱ መጽሐፍ ነው” የሚለው የአነጋገር ስልት የሚያስተላልፈው ሰው ይነበባል፤ ይጠናል፤ ይተነተናል ይጸድቃል፤ ይሻራል ለማለት ነው፡፡ እነዚህን ተግባራት ለሌሎችም ሆነ ለራሳችን ለድርጊታችን ብያኔ ፍርድ ለመስጠት ረቂቅ የሕሊና ልጓም እንደ መሠረት ሆኖ ያገለግላል፡፡ ሰው በውስጡ የሚያረጋግጣት እውነት በክበበ አዕምሮ በሚጨበጥ ሕገ ባሕርይ ከመገለፅ እምቢ አትልም፡፡ እግዚአብሔርን ደስ ለማሰኘት እምነት በቅድሚያ እንዲገኝ ግድ ቢሆንም በተግባር ወይንም በድርጊት ካልተዋሃደ ክርስቲያናዊ ሕይወታችን ፍሬ ቢስ፤ ረብ የሌለው ከንቱ ድካም ይሆናል፡፡ ለመሆኑ እምነታችን ከድርጊታችን ለምን ተዛነፈ? በጽናት የምናምነውን እምነት አጥቦ የመውሰድ ብቃት ያለው ሃይል ይኖር ይሆን? በዕለት ተዕለት ማኅበራዊ መስተጋብር የምንወስናቸው መጠነ ሰፊ ጥቃቅን ውሳኔዎች ውህደ ሃይማኖት ምግባር የታሹ ወይስ የስሜት ውጤቶች ናቸው? እርግጥ ነው ስሜት አልባ ሰብአዊ ፍጡር ሊሆን አይችልም፡፡ ነገር ግን ነፍስን ደስ የሚያሰኝ ሰማያዊ እውነት ከስሜት በላይ ነው፡፡ በገሃዱ ዓለም በብዙዎቻችን ሕይወት የሚታየው ውሳኔዎቻችን በድካም ባካበትነው ዕውቀት፤ መንፈሳዊ አስተምህሮ፤ ዓለማዊ ጥበብ፤ የቅዱሳን ሕይወት ሳይሆን ለስሜት ያጋደለ ሆኖ እናገኘዋለን፡፡ ለሁለት ጌታ መገዛት አይቻልም የሚለውን ኃይለ ቃል ከጌታችን ከመድኃኒታችን ከኢየሱስ ክርስቶስ የተማረው ይሁዳ ለ30 ብር ሸጦታል ለምን ትለኝ እንደሆን ሰው ክፉን ነገር እስኪሰራ ሰው ልበ ሙሉ ይሆናልና ነው፡፡ ሁለተኛው የህሊና ዓይን ከነፍስ ባይለይም በኃጢአት ምክንያት ይጨልማል ይደክማልና ነው፡፡ በአጭር አገላለጽ ድርጊታችንን የሚቆጣጠረው በዕለቱ ስሜታችንን ያቀጣጠለው ኃይል እንጂ በጥረት ያካበትነው ትምህርት ወይም ዕውቀት ሆኖ አይታይም፡፡ ሰው ሆይ ለምን ይሆን

meskel 4

እናከብረው ዘንድ የምንመካበት ይህ መስቀል ነው፤

በዲ/ን ኅሩይ ባየ
ቀን ፡ መስከረም 17/2004 ዓ.ም.
meskel 4

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ከምታከብራቸው ዐበይት እና ንዑሳን በዓላት መካከል አንዱ በዓለ መስቀል ነው፡፡ ኦርቶዶክሳዊት ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን በወርኃ መስከረም ብቻ በዓለ መስቀልን አራት ጊዜ ታከብራለች፡፡
የመጀመሪያው ምክንያተ ክብረ በዓል፣ በኢትዮጵያ ነግሦ የነበረው ዓፄ ዳዊት ከግብፅ ንጉሥና ሊቃነጳጳሳት የተላከለትን በቅዱስ ሉቃስ እጅ የተሳለችውን ስዕለ ማርያምን፣ በወንጌላዊው ቅዱስ ዮሐንስ የተሳለውን ኩርዓተ ርእሱን ፣ ሌሎች ንዋያተ ቅድሳትን እና የጌታችን የመድኀኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስን ግማደ መስቀል የግብፅ እና ኢትዮጵያ ድንበር ከነበረችው አስዋን ከተባለችው ቦታ ተረክቧል፡፡
meskel 1ንጉሡ የያዘውን በረከት ወደኢትዮጵያ ሳያደርስ ስናር በተባለው ቦታ ዐረፈ፡፡ ከጊዜ በኋላ የዐፄ ዳዊት ልጅ ዳግማዊ ቆስጠንጢኖስ የተባለው ዐፄ ዘርዓ ያዕቆብ  ተቀብሎ በደብረ ብርሃን፣ በየረር፣ በመናገሻ እና በልዩ ልዩ ተራራማ ቦታዎች ሲዘዋወር ቆይቶ “ መስቀሌን በመስቀለኛ ቦታ አኑር ”  የሚል ራእይ ተገልጦለት ቅዱስ መስቀሉን በወሎ ክፍለ ሀገር በአምባሰል አውራጃ በግሸን ደብረ ከርቤ አስቀምጦታል ፡፡ መጋቢት ዐሥር ቀን ደብረ ብርሃን ሲገባ ብርሃን ስለወረደና ዐፄ ዳዊት ከግብፃውያን ጳጳሳት እና ንጉሥ እጅ መስቀሉን የተረከቡበትን ቀን በማዘከር የአድባራት እና የገዳማት ሊቃውንት ልብሰ ተክህኖአቸውን ለብሰው የብር መቋሚያ እና ጸናጽል  ይዘው ወደ ነገሥታቱ ሔደው ተቀጸል ጽጌ እያሉ  እያሸበሸቡ ጸሎተ ወንጌል  ያደርሱ ስለነበር መስከረም ዐሥር ቀን የዓፄ መስቀል በዓል ተብሎ ይከበራል፡፡
ሁለተኛው  መስቀሉን በቁፋሮ ያገኘችው ንግሥት እሌኒ ደመራ ያስደመረችበት እና የእጣኑ ጢስ መስቀሉ ወደተቀበረበት ድልብ አከልmeskel 2 ተራራ ያመለከተበት ዕለት መስከረም ዐሥራ ስድስት ቀን በመሆኑ የመስቀል ደመራ በዓል በዚሁ ዕለት ይከበራል፡፡
መስከረም ዐሥራ ሰባት ቀን ደግሞ ቁፋሮ ያስጀመረችበት ዕለት ሲሆን መጋቢት ዐሥር ቀን መስቀሉን አግኝታለች፡፡ ቤተ ክርስቲያን አሠርታ፣ መስቀሉን አስገብታ ቅዳሴ ቤቱን ያከበረችበት ዕለት ግን መስከረም ዐሥራ ሰባት ቀን ነው፡፡ የመስቀሉ መገኘት ጥንተ በዓሉ መጋቢት ዐሥር ቀን ቢሆንም አባቶቻችን በታወቀና በተረዳ ነገር ዋናው የመስቀል በዓል የሚከበርበት ዕለት መስከረም ዐሥራ ሰባት ቀን እንዲሆን አድርገዋል፡፡ በመጨረሻም መስከረም ሃያ አንድ ቀን በዓፄ ዘርዓ ያዕቆብ ዘመነ መንግሥት በግሸን ደብረ ከርቤ መስቀሉ ያረፈበት ዕለት ስለሆነ
“ በልደቱ ፍስሐ ፤
በጥምቀቱ ንስሐ ፤
በመስቀሉ አብርሃ፤ ” እያልን  በማኅሌት፣ በዝማሬና  በቅዳሴ ለዘለዓለም ስናከብረው እንኖራለን ፡፡
የመስቀሉ ቃል ለሚጠፉት ሞኝነት ለእኛ ለምንድን ግን የእግዚአብሔር ኃይል ነው ተብሎ እንደተጻፈ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ያለመስቀል የሚከናወን ሥርዓት የለም፡፡ ከካህናት አክሊል ከመነኮሳት አስኬማ ከእናቶች ቀሚስ እስከ አባቶች እጀጠባብ ድረስ የመስቀል ምልክት እያደረግን በሰውነታችን እየተነቀስን በአንገታችን እያሰርን ለእግዚአብሔር ያለንን ፍቅር እንገልጣለን፡፡
meskel 10እግዚአብሔር ለሰው ልጆች ያለውን እውነተኛ ፍቅር በተለያየ መንገድ አሳይቷል፡፡ ሰማይና ምድር የእርሱ የሆነ አምላክ በከብቶች ግርግም ተወለደ፡፡  የተነገረው ትንቢት የተቆጠረው ሱባዔ ሲያልቅ  በመስቀሉ ተፈጸመ ብሎ ሕይወትን በመስጠት ሞታችንን በመውሰድ ፍቅሩን ገለጠ መስቀል ፍቅረ እግዚአብሔርን የሚያሳስበን የስብከታችን ርእስ የኑሮአችን መርሕ ስለሆነ በዓመት አንድ ጊዜ ወይም ሁለት ጊዜ ብቻ ሳይሆን ዘወትር እናስበዋለን፡፡
ከዐሥራ አራተኛው መቶ ክፍለዘመን ጀምሮ በደጋግ ነገሥታቶቻችን አማካይነት ቅዱሱ መስቀል ወደ ሀገራችን እንዲገባ የዘወትር ጥረት አድርገዋል፡፡ የለመኑትን የማይረሳ የፈለጉትን የማይነሣ አምላክ መስቀሉ በሀገራችን እንዲቀመጥ ፈቃዱ ሆኖአል፡፡
በየዘመኑ እንደሚደረገው የዘንድሮው የመስቀል ደመራ በዓል በመናገሻ ከተማዋ አዲስ አበባ በመስቀል አደባባይ በታላቅ ሥርዓት  ተከብሮ ውሏል፡፡ ማክሰኞ መስከረም ዐሥራ ስድስት ቀን 2004 ዓ.ም ከቀኑ ሰባት ሰዓት ጀምሮ የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ገዳማት እና አድባራት አስተዳዳሪዎች፣ ልብሰ ተክህኖ የለበሱ ካህናት ፣ ጥንግ ድርብ የለበሱ ሊቃውንተ ቤተክርስቲያን የዚህ ዓመት ተረኞች የማኅደረ ስብሐት ቅድስት ልደታ ለማርያም እና ደብረ መድኀኒት መድኃኔዓለም አብያተክርስቲያናት ካህናት እና ሊቃውንተ ቤተክርስቲያን እንዲሁም የሰንበት ትምህርት ቤት ወጣቶች ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ጳወሎስ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ፣ ብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳት፣ ክቡር አቶ ኩማ ደመቅሳ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ፣ አምባሳደሮች እና ጥሪ  የተረደገላቸው የክብር እንግዶች በመስቀል አደባባይ ተገኝተው በዓሉን አክብረዋል ፡፡
meskel 8በኅብረ አልባሳት ደምቀው ከአዲስ አበባ ከተማ የተለያዩ አካባቢዎች የተሰባሰቡ ምእመናን መስቀል አደባባይን እንደ አሸዋ ሞለተውት ነበር፡፡ የአድባራትና የገዳማት የሰንበት ትምህርት ቤት ወጣቶች የክብር ልብሳቸውን ለብሰው የተለያዩ መንፈሳዊ ትርኢቶችን በመሥራት  ከቅዱሳት መጻሕፍት መሪ ጥቅሶችን አንግበው በዕለቱ ለተገኙ ምእመናን፣ ለብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ጳውሎስ ፣ ለብፁዓን ሊቃነጳጳሳት፣ ለክቡር ከንቲባው፣ አምባሳደሮችና እንግዶች አሳይተዋል፡፡ በዚህ ዓመት ከቀረቡት መንፈሳዊ ትርኢቶች ጎልተው የወጡት የሰንበት ትምህርት ቤት ወጣቶች የጽሁፍ መልእክት እና የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን የአብነት ትምህርት ቤቶች እንዳይነጥፉ ክብካቤ እንደሚያሻቸው የቀረበው ትእይንት ነው፡፡ ከቀረቡት ጽሑፍ መልእክቶች መካከል ጥቂቶቹ
“  የአባቶቼን ርስት አልሰጥህም፤  ” 1ኛ ነገሥት 20 ፣4
“ ኢትዮጵያ እጆቿን ወደ እግዚአብሔር ትዘረጋለች  ”  መዝ 67 ፣31
“ ነዋ ወንጌለ መንግሥት ” ማቴ 3 ፣ 6
We are assigned by GOD to make the earth ever green
የሚሉ ይገኙባቸዋል፡፡ በተጨማሪም የኢትዮጵያ ፌዴራል ፖሊስ የማርሽ ባንድ፣ የኢትዮጵያ ጀግኖች አርበኞች ማኅበር አባላት፣ የጋሞ ብሔረሰብ አባላት በአፍ መፍቻ ቋንቋቸው፣ መስማት የተሳናቸው የምሥካዬ ኅዙናን መድኀኔዓለም ገዳም ሰንበት ተማሪዎችም በምልክትmeskel 7 ቋንቋ ዝማሬና ትርዒት አሳይተዋል፡፡ የደብረ ጽጌ ቅዱስ ዑራኤል ቤተክርስቲያን ሰንበት ተማሪዎች ቅድስት እሌኒን በገጸ ባሕርይ ወክለው የመስቀሉን መገኘት አብሥረዋል፡፡ ከዚያም በብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ጳውሎስና በብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳት ቡራኬ ደመራው ተባርኮ ተቀጣጥሏል፡፡ ምእመናን ከመስቀሉ በረከት ለመሳተፍ የደመራውን ዓመድ እንደ እምነት አድርገው በግምባራቸው እየተቀቡ ወደ ቤታቸው ተመልሰዋል፡፡
የመስቀል በዓል በብሔራዊ ደረጃ የዐደባባይ በዓል ሆኖ ሲከበር ከተለያዩ የሀገራችን ክፍሎች የተውጣጡ ምእመናን፣ የውጭ ሀገር ጎብኝዎች  እና በቴሌቪዥን መስኮት በቀጥታ የሚከታተሉ ሕዝብና አሕዛብ በቤተክርስቲያናችን ሥርዓት በመደነቅ አክብሮታቸውን በተለያዩ መንገድ ገልጠዋል፡፡
“መስቀል መልዕልተ ኩሉ ነገር ያድኅነነ እም ፀር –  መስቀል ከሁሉ ነገር በላይ ነው፤ ከጠላት ዲያብሎስ ያድነናል፡፡” ብሎ ቅዱስ ያሬድ እንደ ዘመረው ሀገራችን ኢትዮጵያ  ከመስከረም ዐሥራ ስድስት  ቀን እስከ መስከረም ሃያ አራት ቀን ያለውን አንድ ሱባኤ የመስቀል መታሰቢያ በዓል አድርጋ በማኅሌት በኪዳንና በቅዳሴ ታከብራለች፡፡መጋቢት ዐሥር ቀን መስቀሉ በቅድስት እሌኒ ከተቀበረበት የወጣበት ዕለት ሥለሆነ ታቦት አውጥተን ዑደት አድርገን በታላቅ ሥርዓት እናከብራለን፡፡ ከዘጠኙ ንኡሳን የጌታ በዓላት አንዱ የሆነው የመስቀል በዓል በየዓመቱ  በተወሰኑ ጊዜዎች አስበነው የምናለፈው ሳይሆን ሁልጊዜ የምናከብረው ቅዱስ ቄርሎስ ዘእስክንድርያ እንዳለው ከመስቀሉ በቀር በሌላ ሳንመካ በመስቀሉ ፍቅር የምንኖረው ሕይወት ነው፡፡
meskel 9“ውእቱ ዝንቱ መስቀል ወቦቱ ንትመካህ ከመ ንሰብሖ … እንሰግድለት ዘንድ የምናከብረው፣ እናከብረው ዘንድ የምንመካበት ይህ መስቀል ነው፡፡” /ጸሎተ ኪዳን/ እንደተባለው ሕይወትና ድኅነትን ያገኘንበት የሲኦልን እሳት ተሻግረን ወደ ገነት የገባንበት የአምልካችን ፍቅር የተገለጠበት ዐውድ በመሆኑ መስቀሉን እያሰብን በዓሉን እናከብራለን፡፡
በሐፁረ መስቀሉ የጠበቀን በደመ መስቀሉ የዋጀን አምላክ ይክበር ይመስገን፡፡
ልሳነ ጥበብ

ልሳነ ጥበብ

ልሳነ ጥበብ