?

በዲ/ን እሸቱ

ሚያዝያ 26፣2003ዓ.ም

ሰው ማነው?ሰው ማነው? ብሎ ለጠየቀ “ሰው ንግግሩን ይመስላል” እንዳትለኝ ንግግሩ እምነቱን የሚያመለክት ዕውቀት አይሆነውምና ነው፡፡ ለሰው ባሕርያዊ ተፈጥሮና ዕውቀት ምስክሩ ውስጣዊ የአዕምሮ አቋምና የሕሊና ሕግ ነው ብለንም አንደመድምም፡፡ ሰው እንዲያውቅ የተመደበለት የሕግ ተፈጥሮ ዕውቀት መጀመሪያ ክፍል መልካምን ማወቅ፡፡ ሁለተኛ ክፋትን ንቆ መልካምን ገንዘብ ማድረግ፡፡ ሦስተኛ መልካምን በግብር መግለጽ ናቸው፡፡ የቤተ ክርስቱያን ሊቃውንት ይሁዳን ሲገልጹ “በአፍ አምኖ በልቡ የካደ” ይሉታል፡፡ ባህላችን “አፈ ቅቤ፤ ሆደ ጩቤ” እንዲል፡፡

 

የክርስቲያናዊ ሥነ ምግባር መሠረት ያለ ትምህረት በተፈጥሮ የሚሰጥ ሲሆን ይህም ሕገ ልቦና፤ ሕገ ህሊና፤ ሕገ ተፈጥሮ ወይንም ሕገ ጠብዓያዊ በመባል ይታወቃል፡፡ ሕገ ኦሪትና ሕገ ወንጌል፤ ሕገ ሕሊናን ይተረጉማሉ፡፡ ለአብነት ብንጠቅስ አዳምና ሔዋን ቅዱስ ዳዊትና ይሁዳን፤ ከመጸጸት ክፉዎችን ከማዘን የምታደርሳቸው የሕሊና ኮሽታ ነች፡፡ በኑሮ ሂደት ሀዘን፣ ጸጸት ርትዕ በምናደርግበት ጊዜ ልዩ መንፈሳዊ ጥበብ አልያም ዕውቀት በመታደል ሳይሆን ሰው በመሆናችን በሕሊና ውስጥ የተቀረጸ በህሊና ሚዛን የሚሰጥ ፍርድ በመኖሩ ነው፡፡ ከዚህም በተጨማሪ ሕገ ሕሊና በጽሑፍ ከተሰጡን ሕግጋት /ሕገ ኦሪት፣ ሕገ ወንጌል፣ ማሕበራዊ ሕግ/ በላይ ሰማያዊና ምስጢርን ለመጠበቅ ሲያገለግል እናገኘዋለን፡፡ የቤተ ክርስቲያን የሀገር የግል ምስጢር ይጠበቅ ዘንድ መንፈሳዊ ሕግና ማህበረሰባዊ ሕግ ይደነግጋል፡፡ የአምላክ እናት ድንግል ማርያም ያለ ምድራዊ ሕግ አስገዳጅነት በሕገ ልቦና ዳኝነት ለሰማያዊ ምስጢር የታመነች ነበረች “እናቱ ማርያም በልቧ ትጠብቀው ነበር” እንዲል፡፡ /ሉቃ.2÷19/፡፡

 

 

ሰው ራሱ መጽሐፍ ነው” የሚለው የአነጋገር ስልት የሚያስተላልፈው ሰው ይነበባል፤ ይጠናል፤ ይተነተናል ይጸድቃል፤ ይሻራል ለማለት ነው፡፡ እነዚህን ተግባራት ለሌሎችም ሆነ ለራሳችን ለድርጊታችን ብያኔ ፍርድ ለመስጠት ረቂቅ የሕሊና ልጓም እንደ መሠረት ሆኖ ያገለግላል፡፡ ሰው በውስጡ የሚያረጋግጣት እውነት በክበበ አዕምሮ በሚጨበጥ ሕገ ባሕርይ ከመገለፅ እምቢ አትልም፡፡ እግዚአብሔርን ደስ ለማሰኘት እምነት በቅድሚያ እንዲገኝ ግድ ቢሆንም በተግባር ወይንም በድርጊት ካልተዋሃደ ክርስቲያናዊ ሕይወታችን ፍሬ ቢስ፤ ረብ የሌለው ከንቱ ድካም ይሆናል፡፡ ለመሆኑ እምነታችን ከድርጊታችን ለምን ተዛነፈ? በጽናት የምናምነውን እምነት አጥቦ የመውሰድ ብቃት ያለው ሃይል ይኖር ይሆን? በዕለት ተዕለት ማኅበራዊ መስተጋብር የምንወስናቸው መጠነ ሰፊ ጥቃቅን ውሳኔዎች ውህደ ሃይማኖት ምግባር የታሹ ወይስ የስሜት ውጤቶች ናቸው? እርግጥ ነው ስሜት አልባ ሰብአዊ ፍጡር ሊሆን አይችልም፡፡ ነገር ግን ነፍስን ደስ የሚያሰኝ ሰማያዊ እውነት ከስሜት በላይ ነው፡፡ በገሃዱ ዓለም በብዙዎቻችን ሕይወት የሚታየው ውሳኔዎቻችን በድካም ባካበትነው ዕውቀት፤ መንፈሳዊ አስተምህሮ፤ ዓለማዊ ጥበብ፤ የቅዱሳን ሕይወት ሳይሆን ለስሜት ያጋደለ ሆኖ እናገኘዋለን፡፡ ለሁለት ጌታ መገዛት አይቻልም የሚለውን ኃይለ ቃል ከጌታችን ከመድኃኒታችን ከኢየሱስ ክርስቶስ የተማረው ይሁዳ ለ30 ብር ሸጦታል ለምን ትለኝ እንደሆን ሰው ክፉን ነገር እስኪሰራ ሰው ልበ ሙሉ ይሆናልና ነው፡፡ ሁለተኛው የህሊና ዓይን ከነፍስ ባይለይም በኃጢአት ምክንያት ይጨልማል ይደክማልና ነው፡፡ በአጭር አገላለጽ ድርጊታችንን የሚቆጣጠረው በዕለቱ ስሜታችንን ያቀጣጠለው ኃይል እንጂ በጥረት ያካበትነው ትምህርት ወይም ዕውቀት ሆኖ አይታይም፡፡ ሰው ሆይ ለምን ይሆን

meskel 4

እናከብረው ዘንድ የምንመካበት ይህ መስቀል ነው፤

በዲ/ን ኅሩይ ባየ
ቀን ፡ መስከረም 17/2004 ዓ.ም.
meskel 4

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ከምታከብራቸው ዐበይት እና ንዑሳን በዓላት መካከል አንዱ በዓለ መስቀል ነው፡፡ ኦርቶዶክሳዊት ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን በወርኃ መስከረም ብቻ በዓለ መስቀልን አራት ጊዜ ታከብራለች፡፡
የመጀመሪያው ምክንያተ ክብረ በዓል፣ በኢትዮጵያ ነግሦ የነበረው ዓፄ ዳዊት ከግብፅ ንጉሥና ሊቃነጳጳሳት የተላከለትን በቅዱስ ሉቃስ እጅ የተሳለችውን ስዕለ ማርያምን፣ በወንጌላዊው ቅዱስ ዮሐንስ የተሳለውን ኩርዓተ ርእሱን ፣ ሌሎች ንዋያተ ቅድሳትን እና የጌታችን የመድኀኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስን ግማደ መስቀል የግብፅ እና ኢትዮጵያ ድንበር ከነበረችው አስዋን ከተባለችው ቦታ ተረክቧል፡፡
meskel 1ንጉሡ የያዘውን በረከት ወደኢትዮጵያ ሳያደርስ ስናር በተባለው ቦታ ዐረፈ፡፡ ከጊዜ በኋላ የዐፄ ዳዊት ልጅ ዳግማዊ ቆስጠንጢኖስ የተባለው ዐፄ ዘርዓ ያዕቆብ  ተቀብሎ በደብረ ብርሃን፣ በየረር፣ በመናገሻ እና በልዩ ልዩ ተራራማ ቦታዎች ሲዘዋወር ቆይቶ “ መስቀሌን በመስቀለኛ ቦታ አኑር ”  የሚል ራእይ ተገልጦለት ቅዱስ መስቀሉን በወሎ ክፍለ ሀገር በአምባሰል አውራጃ በግሸን ደብረ ከርቤ አስቀምጦታል ፡፡ መጋቢት ዐሥር ቀን ደብረ ብርሃን ሲገባ ብርሃን ስለወረደና ዐፄ ዳዊት ከግብፃውያን ጳጳሳት እና ንጉሥ እጅ መስቀሉን የተረከቡበትን ቀን በማዘከር የአድባራት እና የገዳማት ሊቃውንት ልብሰ ተክህኖአቸውን ለብሰው የብር መቋሚያ እና ጸናጽል  ይዘው ወደ ነገሥታቱ ሔደው ተቀጸል ጽጌ እያሉ  እያሸበሸቡ ጸሎተ ወንጌል  ያደርሱ ስለነበር መስከረም ዐሥር ቀን የዓፄ መስቀል በዓል ተብሎ ይከበራል፡፡
ሁለተኛው  መስቀሉን በቁፋሮ ያገኘችው ንግሥት እሌኒ ደመራ ያስደመረችበት እና የእጣኑ ጢስ መስቀሉ ወደተቀበረበት ድልብ አከልmeskel 2 ተራራ ያመለከተበት ዕለት መስከረም ዐሥራ ስድስት ቀን በመሆኑ የመስቀል ደመራ በዓል በዚሁ ዕለት ይከበራል፡፡
መስከረም ዐሥራ ሰባት ቀን ደግሞ ቁፋሮ ያስጀመረችበት ዕለት ሲሆን መጋቢት ዐሥር ቀን መስቀሉን አግኝታለች፡፡ ቤተ ክርስቲያን አሠርታ፣ መስቀሉን አስገብታ ቅዳሴ ቤቱን ያከበረችበት ዕለት ግን መስከረም ዐሥራ ሰባት ቀን ነው፡፡ የመስቀሉ መገኘት ጥንተ በዓሉ መጋቢት ዐሥር ቀን ቢሆንም አባቶቻችን በታወቀና በተረዳ ነገር ዋናው የመስቀል በዓል የሚከበርበት ዕለት መስከረም ዐሥራ ሰባት ቀን እንዲሆን አድርገዋል፡፡ በመጨረሻም መስከረም ሃያ አንድ ቀን በዓፄ ዘርዓ ያዕቆብ ዘመነ መንግሥት በግሸን ደብረ ከርቤ መስቀሉ ያረፈበት ዕለት ስለሆነ
“ በልደቱ ፍስሐ ፤
በጥምቀቱ ንስሐ ፤
በመስቀሉ አብርሃ፤ ” እያልን  በማኅሌት፣ በዝማሬና  በቅዳሴ ለዘለዓለም ስናከብረው እንኖራለን ፡፡
የመስቀሉ ቃል ለሚጠፉት ሞኝነት ለእኛ ለምንድን ግን የእግዚአብሔር ኃይል ነው ተብሎ እንደተጻፈ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ያለመስቀል የሚከናወን ሥርዓት የለም፡፡ ከካህናት አክሊል ከመነኮሳት አስኬማ ከእናቶች ቀሚስ እስከ አባቶች እጀጠባብ ድረስ የመስቀል ምልክት እያደረግን በሰውነታችን እየተነቀስን በአንገታችን እያሰርን ለእግዚአብሔር ያለንን ፍቅር እንገልጣለን፡፡
meskel 10እግዚአብሔር ለሰው ልጆች ያለውን እውነተኛ ፍቅር በተለያየ መንገድ አሳይቷል፡፡ ሰማይና ምድር የእርሱ የሆነ አምላክ በከብቶች ግርግም ተወለደ፡፡  የተነገረው ትንቢት የተቆጠረው ሱባዔ ሲያልቅ  በመስቀሉ ተፈጸመ ብሎ ሕይወትን በመስጠት ሞታችንን በመውሰድ ፍቅሩን ገለጠ መስቀል ፍቅረ እግዚአብሔርን የሚያሳስበን የስብከታችን ርእስ የኑሮአችን መርሕ ስለሆነ በዓመት አንድ ጊዜ ወይም ሁለት ጊዜ ብቻ ሳይሆን ዘወትር እናስበዋለን፡፡
ከዐሥራ አራተኛው መቶ ክፍለዘመን ጀምሮ በደጋግ ነገሥታቶቻችን አማካይነት ቅዱሱ መስቀል ወደ ሀገራችን እንዲገባ የዘወትር ጥረት አድርገዋል፡፡ የለመኑትን የማይረሳ የፈለጉትን የማይነሣ አምላክ መስቀሉ በሀገራችን እንዲቀመጥ ፈቃዱ ሆኖአል፡፡
በየዘመኑ እንደሚደረገው የዘንድሮው የመስቀል ደመራ በዓል በመናገሻ ከተማዋ አዲስ አበባ በመስቀል አደባባይ በታላቅ ሥርዓት  ተከብሮ ውሏል፡፡ ማክሰኞ መስከረም ዐሥራ ስድስት ቀን 2004 ዓ.ም ከቀኑ ሰባት ሰዓት ጀምሮ የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ገዳማት እና አድባራት አስተዳዳሪዎች፣ ልብሰ ተክህኖ የለበሱ ካህናት ፣ ጥንግ ድርብ የለበሱ ሊቃውንተ ቤተክርስቲያን የዚህ ዓመት ተረኞች የማኅደረ ስብሐት ቅድስት ልደታ ለማርያም እና ደብረ መድኀኒት መድኃኔዓለም አብያተክርስቲያናት ካህናት እና ሊቃውንተ ቤተክርስቲያን እንዲሁም የሰንበት ትምህርት ቤት ወጣቶች ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ጳወሎስ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ፣ ብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳት፣ ክቡር አቶ ኩማ ደመቅሳ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ፣ አምባሳደሮች እና ጥሪ  የተረደገላቸው የክብር እንግዶች በመስቀል አደባባይ ተገኝተው በዓሉን አክብረዋል ፡፡
meskel 8በኅብረ አልባሳት ደምቀው ከአዲስ አበባ ከተማ የተለያዩ አካባቢዎች የተሰባሰቡ ምእመናን መስቀል አደባባይን እንደ አሸዋ ሞለተውት ነበር፡፡ የአድባራትና የገዳማት የሰንበት ትምህርት ቤት ወጣቶች የክብር ልብሳቸውን ለብሰው የተለያዩ መንፈሳዊ ትርኢቶችን በመሥራት  ከቅዱሳት መጻሕፍት መሪ ጥቅሶችን አንግበው በዕለቱ ለተገኙ ምእመናን፣ ለብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ጳውሎስ ፣ ለብፁዓን ሊቃነጳጳሳት፣ ለክቡር ከንቲባው፣ አምባሳደሮችና እንግዶች አሳይተዋል፡፡ በዚህ ዓመት ከቀረቡት መንፈሳዊ ትርኢቶች ጎልተው የወጡት የሰንበት ትምህርት ቤት ወጣቶች የጽሁፍ መልእክት እና የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን የአብነት ትምህርት ቤቶች እንዳይነጥፉ ክብካቤ እንደሚያሻቸው የቀረበው ትእይንት ነው፡፡ ከቀረቡት ጽሑፍ መልእክቶች መካከል ጥቂቶቹ
“  የአባቶቼን ርስት አልሰጥህም፤  ” 1ኛ ነገሥት 20 ፣4
“ ኢትዮጵያ እጆቿን ወደ እግዚአብሔር ትዘረጋለች  ”  መዝ 67 ፣31
“ ነዋ ወንጌለ መንግሥት ” ማቴ 3 ፣ 6
We are assigned by GOD to make the earth ever green
የሚሉ ይገኙባቸዋል፡፡ በተጨማሪም የኢትዮጵያ ፌዴራል ፖሊስ የማርሽ ባንድ፣ የኢትዮጵያ ጀግኖች አርበኞች ማኅበር አባላት፣ የጋሞ ብሔረሰብ አባላት በአፍ መፍቻ ቋንቋቸው፣ መስማት የተሳናቸው የምሥካዬ ኅዙናን መድኀኔዓለም ገዳም ሰንበት ተማሪዎችም በምልክትmeskel 7 ቋንቋ ዝማሬና ትርዒት አሳይተዋል፡፡ የደብረ ጽጌ ቅዱስ ዑራኤል ቤተክርስቲያን ሰንበት ተማሪዎች ቅድስት እሌኒን በገጸ ባሕርይ ወክለው የመስቀሉን መገኘት አብሥረዋል፡፡ ከዚያም በብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ጳውሎስና በብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳት ቡራኬ ደመራው ተባርኮ ተቀጣጥሏል፡፡ ምእመናን ከመስቀሉ በረከት ለመሳተፍ የደመራውን ዓመድ እንደ እምነት አድርገው በግምባራቸው እየተቀቡ ወደ ቤታቸው ተመልሰዋል፡፡
የመስቀል በዓል በብሔራዊ ደረጃ የዐደባባይ በዓል ሆኖ ሲከበር ከተለያዩ የሀገራችን ክፍሎች የተውጣጡ ምእመናን፣ የውጭ ሀገር ጎብኝዎች  እና በቴሌቪዥን መስኮት በቀጥታ የሚከታተሉ ሕዝብና አሕዛብ በቤተክርስቲያናችን ሥርዓት በመደነቅ አክብሮታቸውን በተለያዩ መንገድ ገልጠዋል፡፡
“መስቀል መልዕልተ ኩሉ ነገር ያድኅነነ እም ፀር –  መስቀል ከሁሉ ነገር በላይ ነው፤ ከጠላት ዲያብሎስ ያድነናል፡፡” ብሎ ቅዱስ ያሬድ እንደ ዘመረው ሀገራችን ኢትዮጵያ  ከመስከረም ዐሥራ ስድስት  ቀን እስከ መስከረም ሃያ አራት ቀን ያለውን አንድ ሱባኤ የመስቀል መታሰቢያ በዓል አድርጋ በማኅሌት በኪዳንና በቅዳሴ ታከብራለች፡፡መጋቢት ዐሥር ቀን መስቀሉ በቅድስት እሌኒ ከተቀበረበት የወጣበት ዕለት ሥለሆነ ታቦት አውጥተን ዑደት አድርገን በታላቅ ሥርዓት እናከብራለን፡፡ ከዘጠኙ ንኡሳን የጌታ በዓላት አንዱ የሆነው የመስቀል በዓል በየዓመቱ  በተወሰኑ ጊዜዎች አስበነው የምናለፈው ሳይሆን ሁልጊዜ የምናከብረው ቅዱስ ቄርሎስ ዘእስክንድርያ እንዳለው ከመስቀሉ በቀር በሌላ ሳንመካ በመስቀሉ ፍቅር የምንኖረው ሕይወት ነው፡፡
meskel 9“ውእቱ ዝንቱ መስቀል ወቦቱ ንትመካህ ከመ ንሰብሖ … እንሰግድለት ዘንድ የምናከብረው፣ እናከብረው ዘንድ የምንመካበት ይህ መስቀል ነው፡፡” /ጸሎተ ኪዳን/ እንደተባለው ሕይወትና ድኅነትን ያገኘንበት የሲኦልን እሳት ተሻግረን ወደ ገነት የገባንበት የአምልካችን ፍቅር የተገለጠበት ዐውድ በመሆኑ መስቀሉን እያሰብን በዓሉን እናከብራለን፡፡
በሐፁረ መስቀሉ የጠበቀን በደመ መስቀሉ የዋጀን አምላክ ይክበር ይመስገን፡፡
ልሳነ ጥበብ

ልሳነ ጥበብ

ልሳነ ጥበብ

tinatna mirimir

3ኛው ዓመታዊ የጥናት ጉባኤ ቅዳሜ ይጀመራል።

ዲ/ን ተስፋየ አእምሮ

tinatna mirimirየማኅበረ ቅዱሳን ጥናትና ምርምር ማዕከል ያዘጋጀው 3ኛው ዓመታዊ የጥናትና ምርምር ጉባኤ ከነሐሴ 28 እስከ 29 ቀን 2003 ዓ.ም በብሔራዊ ሙዚየም አዳራሽ ይከናወናል።

የጥናትና ምርምር ማዕከሉ ዳይሬክተር ዲ/ን መንግስቱ ጎበዜ እንደገለጹት ዓመታዊ ዓውደ ጥናቱ  “ጥናትና ምርምር ለቤተ ክርስቲያን አስተዳደር መጠናከር” በሚል መሪ ቃል ይከናወናል።

የዓውደ ጥናቱ ዋና ዓላማም መሠረታዊ ችግሮችን በመለየትና የመፍትሔ አቅጣጫዎችን በመጠቆም የቤተ ክርስቲያንን አስተዳደር ለማጠናከር ይረዳ ዘንድ ነው ብለዋል።

በሁለቱም ቀናት አምስት ጥናቶች የሚቀርብ ሲሆን፥ የመንፈሳዊ ፍርድ ቤት አስፈላጊነት በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን፣ የሰው ኃይልና የገንዘብ አስተዳደር ሥርዐት በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን፣ የውጭ ሀገር ሰዎች ተደራሽነት በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን፣ ነገረ ማርያም በድርሳነ ጽዮን፣ እንዲሁም ይምርሃነ ክርስቶስ ዘመን ተሻጋሪው ሥልጣኔ የሚሉት ርዕሶች ተመርጠው እንደቀረቡ ዳይሬክተሩ ተናግረዋል።

ጥናቶቹ በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በሚያስተምሩ ምሁራንና ሌሎች ተመራማሪዎች የተዘጋጁ ሲሆን የውይይት መሪዎችም ከጉዳዩ ጋር ዝምድና ያላቸው ታዋቂ ምሁራን መሆናቸው ተገልጿል። በዓውደ ጥናቱ ላይ መሳተፍ ለሚፈልጉ ሁሉ እንዲገኙ ዳይሬክተሩ ጥሪያቸውን አስተላልፈዋል።

«የአሮጊቷ ሣራ» ወለደች ዐዋጅ ተሐድሶ ዘመቻ የጥፋት ፈትል እንደማጠንጠኛ

በመጽሐፍ ቅዱስ ትምህርት በብሉያትና በሐዲሳቱም የምትነሣው ሣራ አበ ብዙኃን ሥርወ ሃይማኖት የምንለው የአብርሃም ሚስት ነች፡፡ እግዚአብሔር ለአብርሃም የብዙዎች አባት እንዲሆን ቃል ኪዳን ሳይገባለት በፊት፣ በመካንነት ታዝን፣ ተስፋም አጥታ ትተክዝ በነበረችበት ጊዜ ሦራ ትባል ነበር፡፡

ሦራ ሙቀት ልምላሜ ከተለያት በኋላ ልጅ እንደምትወልድ ከአብርሃም በኩል እግዚአብሔር ቃል ኪዳን ከገባላት፣ ተስፋም ከተሰጣት በኋላ ሣራ ተብላለች፡፡ እግዚአብሔርም ስለእርሷ ለአብርሃም «የሚስትህን የሦራን ስም ሦራ ብለህ አትጥራ፤ ስምዋ ሣራ ይሆናል እንጂ፤ እባርካታለሁ፤ ደግሞም ከእርሷ ልጅ እሰጥሃለሁ፤ እባርካትማለሁ፤ የአሕዛብ እናት ትሆናለች፤ የአሕዛብ ነገሥታት ከእርሷ ይወጣሉ» በማለት ተናገረው /ዘፍ. 17፥15/፡፡

ሣራ ሦራ ተብላ ትጠራ በነበረበት፣ ያለተስፋ በኖረችበት የቀደመው ዘመኗ ለአብርሃም ልጅ አልወለደችለትም ነበር፡፡ ሦራ ዘር ማጣት ታላቅ ሐዘን በሆነበት በዚያ ዘመን፣ መካንነት ያስንቅ በነበረበት በዚያን ጊዜ አብራም ከሌላ ይወልድ ዘንድ አዘነችለት፡፡ አብራም አጋር ወደ ተባለችው ግብጻዊት ባሪያዋ ይደርስ ዘንድ «እነሆ እንዳልወልድ እግዚአብሔር ዘጋኝ ምናልባት ከእርሷ በልጅ እታነጽ እንደ ሆነ ወደ እርሷ ግባ» አለችው፡፡ /ዘፍ.16፥2/ በትሑቷ ሦራ ምክር አጋር ከአብርሃም በፀነሰችበት ወራት ሦራን አሳዘነቻት፤ አጋርም ተመካች፤ እመቤት የነበረችውን ሦራ ስለመካንነቷ በዓይኗ አቃለለቻት፡፡ ይህ ለሦራ በእግዚአብሔር እና በባሏ በአብራም ፊት ያዘነችበት ሰቆቃዋ ነው፡፡ ሦራም ከሐዘኗ ጽናት የተነሣ አብራምን እንዲህ አለችው «መገፋቴ በአንተ ላይ ይሁን እኔ ባሪያዬን በብብትህ ሰጠሁህ፤ እንዳረገዘችም ባየች ጊዜ እኔን በዓይኗ አቃለለችኝ፤ እግዚአብሔር በእኔና በአንተ መካከል ይፍረድ» አለችው፡፡ በአብራም ፍርድም ሦራ ባሪያዋን አጋርን በመቅጣቷ አጋር ኮበለለች፡፡

እንግዲህ ከላይ አስቀድመን የጠቀስነው ለአብርሃም የተገባው ቃል ኪዳን የተሰጠው ሦራና አብራም በዚህ ሐዘን ውስጥ በነበሩበት ጊዜ ነው፡፡ ያዘነችው ሦራ ከቃል ኪዳኑ በኋላ የብዙኃን እናት ልትሆን ሣራ ተብላ እርሱም የብዙዎች አባት ሊሆን አብርሃም ተብሎ የተስፋው ቃል ተነገረው «በእውነት ሚስትህ ሣራ ወንድ ልጅን ትወልድልሃለች ስሙንም ይስሐቅ ብለህ ትጠራዋለህ ከእርሱ በኋላ ለዘሩ የዘላለም ቃልኪዳን እንዲሆን ቃል ኪዳኔን ከእርሱ ጋር አቆማለሁ» /ዘፍ.17፥19/፡፡

እግዚአብሔር ለአብርሃም ሣራ እንደምትወልድ የነገርውን የተስፋ ቃል በቤቱ በእንግድነት ተገኝቶ አጸና፡፡ «የዛሬ ዓመት እንደ ዛሬው ጊዜ ወደ አንተ በእውነት እመለሳለሁ ሚስትህ ሣራም ልጅን ታገኛለች፡፡»/ዘፍ.18፥10/ አለው፡፡ ሁል ጊዜም ቃሉ የሚታመን እግዚአብሔር ይመስገንና እንደተባለው ሆነ «እግዚአብሔርም እንደተናገረው ሣራን አሰበ እግዚአብሔርም እንደተናገረው ለሣራ አደረገላት ሣራም ፀነሰች እግዚአብሔርም በተናገረው ወራት ለአብርሃም በእርጅናው ወንድ ልጅን ወለደችለት አብርሃም ሣራ የወለደችለትን የልጁን ስም ይስሐቅ ብሎ ጠራው» /ዘፍ.21፥1/ «ሣራም እግዚአብሔር ሳቅ /ደስታ አድርጎልኛል ይህንንም የሚሰማ ሁሉ በእኔ ምክንያት ይስቃል አለች ደግሞም ሣራ ልጆችን እንድታጠባ ለአብርሃም ማን በነገረው በእርጅናው ልጅን ወልጄለታለሁና /ዘፍ. 21፥7/፡፡

እንግዲህ መካኒቱ ሣራ ሙቀት ልምላሜ ከተለያት በኋላ በጨዋነት ወልዳ ለአብርሃም ለዘላለም የገባው ቃል ኪዳን የሚፈጸምበትን ዘር ይስሐቅን አሳድጋለች፡፡ በቃል ኪዳን፣ በተስፋ የተወለደው ይስሐቅ ታላቅ ነውና «የዚህች ባሪያ /የአጋር/ ልጅ ከልጄ ከይስሐቅ ጋር አይወርስም» አለች፡፡ እግዚአብሔርም ቃሏን ተቀብሎ ለአብርሃም «ሣራም የምትነግርህን ቃል ሁሉ ስማ በይስሐቅ ዘር ይጠራልሃልና…» አለው /ዘፍ.21፥1-12/፡፡

እንዲህ በእግዚአብሔር የተስፋ ቃል የከበረችው ሣራ በብሉያት ብቻ ሳይሆን በሐዲሳትም ለተለያዩ ጉዳዮች እንደ አርአያና ምሳሌ ስትጠቀስ እናነባለን፡፡ ሊቀ ሐዋርያት ቅዱስ ጴጥሮስ ሚስቶችን ሲመክር በመልካም ትሑት ሰብእናዋ አርአያ የምትሆን አድርጎ የጠቀሳት ሣራን ነው «ጠጉርን በመሸረብ፣ ወርቅን በማንጠልጠል፣ ወይም ልብስን በመጎናጸፍ በውጪ በሆነ ሽልማት» ሳይሆን «በእግዚአብሔር ፊት ዋጋው እጅግ የከበረ የዋህና ዝግተኛ መንፈስ ያለውን የማይጠፋውን ልብስ» ተጎናጽፋ ውስጧን ያስጌጠች ብፅዕት ሚስት መሆኗን መስክሯል፡፡ «ሣራ ለአብርሃም ጌታዬ ብላ እየጠራችው ታዘዘችለት፤ እናንተም ከሚያስደነግጥ ነገር አንዳች እንኳ ሳትፈሩ መልካም ብታደርጉ ልጆችዋ ናችሁ፡፡» /1ጴጥ. 3፥3-6/ ብሏል፡፡

ቅዱስ ጳውሎስ ደግሞ የክርስቶስ የማዳኑ የምስራች ከታወጀላቸው በኋላ ሕገ ኦሪትን ካልጠበቅን አንድንም የሚሉ ቢጽሐሳውያንን ቃል ሰምተው ያመኑ የገላትያን ሰዎች በገሰጸበት መልእክቱ ሣራን የሕገ ወንጌል ምሳሌ አድርጎ አቅርቧታል፡፡ በአንጻሩ ባሪያዋን አጋርን የሕገ ኦሪት ምሳሌ አድርጎ አቅርቧል /ገላ.4፥21/፡፡

የሣራን ሕይወት በዚህ ጽሑፍ ያነሣንበትንም መሠረታዊ ምክንያትም ይህንን የቅዱስ ጳውሎስን ምሳሌያዊ መልእክት ተንተርሰው ያለአገባቡ እየጠቀሱ የቤተ ክርስቲያናን ልጆች ምእመናንን ግራ ስለሚያጋቡ የተሐድሶ መናፍቃንና ተሐድሶአዊ ትምህርት ስለሚያስተምሩ ሰዎች ሐሳብ ለማንሣት ነው፡፡ በቅድሚያ የቅዱስ ጳውሎስ የመልእክቱን ሐሳብ በአጭሩ እናብራራና፤ ተሐድሶ የዘመቻ ማወራረጃ አድርጎ ስለሚጠቀምበት ጥራዝ ነጠቅ ቃልና አስተሳሰብ ደግሞ ቀጥሎ እናመጣለን፡፡ ሐዋርያው ስለዚህ ነገር ሲናገር የሚከተለውን ብሏል፡፡

«እናንተ ከሕግ በታች ልትኖሩ የምትወዱ ሕጉን አትሰሙምን ? እስኪ ንገሩኝ፤ አንዱ ከባሪያዪቱ አንዱ       ከጨዋዪቱ የሆኑ ሁለት ልጆች ለአብርሃም እንደነበሩት ተጽፏልና፤ ነገር ግን የባሪያዪቱ ልጅ እንደ ሥጋ ተወልዷል፤ የጨዋዪቱ ግን በተስፋው ቃል ተወልዷል፤ ይህም ነገር ምሳሌ ነው እነዚህ ሴቶች እንደ ሁለቱ ኪዳናት ናቸውና፤ ከደብረ ሲና የሆነችው አንዲቱ ለባርነት ልጆችን ትወልዳለች፤ እርሷም አጋር ናት፤ ይህቺም አጋር በዓረብ ምድር ያለችው ደብረ ሲና ናት፤ አሁንም ያለችውን ኢየሩሳሌምን ትመስላለች፤ ከልጆቿ ጋር በባርነት ናትና፤ ላይኛዪቱ ኢየሩሳሌም ግን በነጻነት የምትኖር ናት፤ እርሷም እናታችን ናት… ስለዚህ ወንድሞች ሆይ የጨዋዪቱ ልጆች ነን እንጂ የባሪያዪቱ አይደለንም» /ገላ.4፥21-31/፡፡
በገላትያ መልእክቱ ቅዱስ ጳውሎስ ትኩረት የሰጠው ጉዳይ «የክርስቶስን ሐዋርያት እንዲመስሉ ራሳቸውን እየለወጡ ውሸተኞች ሐዋርያትና ተንኮለኞች ሠራተኞች» ስለነበሩት ከአይሁድ ወገን የሆኑ ካልተገረዛችሁ፣ ሕገ ኦሪትንም ካልፈጸማችሁ አትድኑም እያሉ የሚያስተምሩ ሰዎች ጉዳይ ነው፡፡ እነዚህ ኦሪታዊ ሁኑ የሚሉ ሰዎችን ትምህርት እየሰሙ የወንጌልን ቃል ቸል ያሉት የገላትያን ሰዎች በግልጽ «እግዚአብሔርን ስታውቁ፣ ይልቅስ በእግዚአብሔር ስትታወቁ እንደገና ወደ ደካማ ወደሚናቅም ወደ መጀመሪያ ትምህርት እንዴት ትመለሳላችሁ? እንደገና ባሪያዎች ሆናችሁ ዳግመኛ ለዚያ ልትገዙ ትወዳላችሁን ? ቀንና ወርን ዘመንንም ዓመትንም በጥንቃቄ ትጠብቃላችሁ…» ይላቸዋል፡፡ /ገላ.4፥9-11/
የሐዋርያው ዋነኛ ጉዳይ ሕገ ኦሪት ይጠበቅ አይጠበቅ በመሆኑም ነው «እናንተ ከሕግ በታች ልትኖሩ የምትወዱ ሕጉን አትሰሙምን ?» ያላቸው /ገላ. 1፥21/፡፡ ምክንያቱም ያመኑትን ሁሉ በደሙ የዋጀ የኢየሱስ ክርስቶስ የምስራች ወንጌል ከተነገረች በኋላ ዳግመኛ ወደ ኋላ ተመልሶ ቀንና ወርን ዘመንንም እየቆጠሩ መሥዋዕተ ኦሪትን ለማቅረብ፣ ግዝረትን አበክሮ ለመጠበቅ፣ ያንንም ካልፈጸማችሁ አትድኑም ወደሚል ትምህርት መመለስ ያሳፍራልና፡፡
ስለዚህ እናንተ በኦሪት እንኑር የምትሉ ሆይ! በኦሪት የተነገረውን ምሳሌ አንብቡ ብሎ የሣራን እና የአጋርን ምሳሌነት ያነሣል፡፡ በኦሪት አብርሃም አስቀድመን እንዳየነው ጨዋይቱ ከተባለችው ከእመቤቲቱ ሣራ ይስሐቅን፣ ከባሪያይቱ ከአጋር ደግሞ እስማኤልን ወልዷል፡፡ የሁለቱ ልደት ግን ለየቅል መሆኑን ይነግራቸዋል፡፡ ከባሪያዪቱ የተወለደው አጋር ሙቀት ልምላሜ እያላት ተወልዷልና፤ ከእመቤቲቱ የተወለደው ግን ሙቀት ልምላሜ ከተለያት በዘጠና ዓመቷ/ ከእግዚአብሔር ብቻ በተሰጠው ተስፋ ተአምራትም ተወልዷልና፡፡ እነዚህ ሁለቱ ሴቶች የሕገ ኦሪትና የሕገ ወንጌል ምሳሌ ናቸው፡፡ ቅዱስ ጳውሎስም በቃሉ «ይህም ነገር ምሳሌ ነው» እንዳለ /ገላ. 4፥24/፡፡ አጋር ኦሪትን ደብረ ሲናን አንድ ወገን ያደርጋል፤ ሣራን፣ ወንጌልን ሰማያዊቱ ኢየሩሳሌምን ደግሞ አንድ ወገን እያደረገ እያነጻጸረ ተናግሯል፡፡
አንዲቱ /ኦሪት/ አምሳል መርገፍ ሆና በደብረ ሲና ተሠርታለችና፤ ደብረ ሲናም ከኢየሩሳሌም ስትነጻጸር በምዕራብ ያለች ተራራ ናትና፤ ስለዚህ ይህች ምድራዊት የምትሆን አምሳል መርገፍ አማናዊት ከምትሆን ሰማያዊት ኢየሩሳሌም ጋር ስትነጻጸር ዝቅ ያለች ናትና «ወትትቀነይ ምስለ ደቂቃ» አምሳል መርገፍ በመሆን ከልጆቿ ጋር ትገዛለች፡፡ ላዕላዊት የምትሆን ኢየሩሳሌም ግን ከመገዛት ነጻ ናት ብሎ «ወይእቲ እምነ፤ እርስዋም እናታችን ናት» ይላል፡፡ ይቺም እናታችን ሣራ ምሳሌዋ የምትሆን ወንጌል ናት፡፡
ስለዚህ ከሣራ የተወለደው ተስፋውን ወራሽ እንደሆነ ሁሉ እኛም ከወንጌል የተወለድን ክርስቶሳውያን በይስሐቅ አምሳል እንደይስሐቅ ተስፋውን መውረስ የሚገባን የነጻነት ልጆች ነን ማለቱ እንደሆነ ሊቃውንቱ ያስተምራሉ፡፡ የባሪያዪቱ ልጅ ከእመቤት ልጅ ጋር ተካክሎ ርስት አይወርስምና በበግና በፍየሎች ደም ምሳሌያዊ ወይም ጥላ   አገልግሎት በምትሰጥ ገረድ /ሞግዚት/ የተባለች የኦሪት ልጆች አይደለንም፡፡ ክርስቲያኖች በእግዚአብሔር ልጅ ሥጋና ደም ነጻ በምታወጣ አዲስ ኪዳን የወንጌል ልጆች ነንና፡፡
ሐዋርያው ይህንን ሁሉ ያለው ካልተገረዛችሁ አትድኑም የሚለውን የቢጽ ሐሳውያንን ትምህርት በመኮነን ሲሆን ይህንንም በግልጽ «በክርስቶስ ኢየሱስ ሆኖ በፍቅር የሚሠራ እምነት እንጂ መገረዝ ቢሆን ወይም አለመገረዝ አይጠቅምምና /ገላ. 5፥6/ ይላል፡፡ በክርስቶስ ኢየሱስ ሆኖ በፍቅር የሚሠራ ያለው ሕይወትም ፍትወተ ሥጋን አሸንፎ በመንፈሳዊ ተጋድሎ የበቁ ሆኖ በመንፈስ መራመድን ነው፡፡ ይህ ሣራ በተመሰለችባት ሕገ ወንገል ውስጥ የተጠራንበት የመታዘዝ ሕይወት ነው፡፡ ሐዋርያውም ለገላትያ ሰዎች ይህንኑ ተርጉሞ ሲናገር «የክርስቶስ ኢየሱስም የሆኑት ሥጋን ከክፉ መሻቱና ከምኞቱ ጋር ሰቀሉ» /ገላ. 5፥24/ አለን፡፡ ስለዚህ የቤተክርስቲያን ወገኖች ሁሉ ሥጋን ከክፉ መሻቱና ከምኞት ጋር የሰቀሉ መንፈሳውያን፣ በፍቅር የእግዚብሔርን ትዕዛዝ የሚፈጽመው የጨዋይቱ /የእመቤቲቱ/ የሣራ ልጆች ናቸው፤ እንጂ ሥጋዊ ሥርዓት፣ መርገፍ፣ ጥላ በሆነው ብሉይ ኪዳን ውስጥ የመገረዝ አለመገረዝ ጣጣን የሚሰብኩ፣ የሚሰበኩ በሥጋ ልማድ የወለደችው የባሪያዪቱ የአጋር ልጆች አይደሉም፡፡
እንግዲህ በነጻነት የምትመራውን ላይኛይቱን ኢየሩሳሌምን የመረጡ ክርስቶሳውያን ለ2ሺሕ ዘመናት ያህል ክርስቶስን በመስበክ በስሙም ክርስቲያን ተብለን ስንጠራ ኖረናል፡፡ ኢትዮጵያውያን ክርስቲያኖች ገና አስቀድሞ በ34 ዓ.ም «ኢየሱስ ክርስቶስ የእግዚአብሔር ልጅ እንደሆነ አምናለሁ፡፡ ካለው ጃንደረባው ጀምረው ሠልጥና ከነበረችው ባሪያይቱ አጋር ይልቅ በተስፋው ሥርዓት የወለደችውን እመቤቲቱን ሣራ መርጠው እስከዚህ ዘመን ድረስ ኖረዋል፡፡
ከየካቲት ወር 1990 ዓ.ም ጀምሮ ግን «ተሐድሶ» በኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን ላይ በይፋ በጀመረው ዘመቻ ውስጥ የዘመቻው አዋጅ ማጠንጠኛ «አሮጊቷ ሣራ እኔ /እኛን/ ወለደች» የሚለው ቃል ነው፡፡ «የተሐድሶ መነኮሳት ኅብረት» የተባለው ቡድን በቤተ ክርስቲያናችን ውስጥ ሆኖ ከቤተ ክርስቲያን ማዕድ እየተቋደሰ ነገር ግን በመሠሪነት ለመናፍቃን ተላላኪ ሆኖ የቆየ ሲሆን በየካቲት ወር 1990 ግን በአዲስ አበባ ከተማ በኢግዚብሽን ማዕከል በፕሮቴስታንቶች ተደራጅቶ በተዘጋጀው «ጉባኤ» በይፋ ራሱን ለይቶ የ«ተሐድሶ» ጥሪ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን ላይ እንዲደረግ ሲያውጅ ተገኝቷል፡፡ /ይህንን ለማጋለጥ የወጣወን ቪዲዮ ፊልም ወይም ቪሲዲ ይመልከቱ/ በዚህ አዋጅ በጉልህ የሚስማው ድምፅ ከላይ የተጠቀሰው «አሮጊቷ ሣራ እኔን ወለደች» የሚለው ንግግር ነበር፡፡ ይህንን ቃል ደጋግሞ ሲያስተጋባ የነበረው አባ ዮናስ /በለጠ/ የተባለው «መነኩሴ» «ወንጌልን ለመስበክ ተሾምኩ፤… አሮጊቷ ሣራ ወለደች፤ አሮጊቷ ሣራ እኔን ወለደች፣ ዘውዱን ወለደች፣ ፍስሐን ወለደች፣ ገብረ ክርስቶስን ወለደች… ይህ ትውልድ የኢያሪኮን ግንብ ያፈርሳል…» ወዘተ እያለ አብረውት ለጥፋት የተሰለፉ ከሃዲ መነኮሳትን እየጠቀሰ ፎክሯል፡፡
በእነ አባ ዮናስ አዋጅ ውስጥ ያለው ግልጽ መልእክት ግን በሁለት መልኩ የሚታይ ወይም ሊተረጎም የሚችል ነው፡፡
1.    ቤተክርስቲያንን በእርጅና ዘመኗ ከወለደችው ከቅድስት ሣራ ጋር በማነጻጸር ራሳቸውን የዚህችው ኦርቶዶክሳዊት ቤተክርስቲያን አድርገው በማቅረብ ከዚህች ቤተክርስቲያንም አካል የተገኙ መሆናቸውን በመግለጥ የቤተክርስቲያን አስተምህሮ እነርሱ የሚሉት እንደሆነ አድርገው ለማደናበር ነው፡፡
2.    ሌላው የድፍረት መልእክት ደግሞ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያንን በባሪያይቱ በአጋር ምሳሌ ልትጠቀስ የምትችል ኦሪታዊት፤ የጨዋይቱ የተባለች የሣራ የተስፋው ዘር ቅሪት የሌለባት፣ የወንጌል ብርሃን ያልበራባት፤ ክርስቶስን የማታውቅ፣ ጌትነቱንም የማታምን አድርገው አቅርበዋታል፡፡ ራሳቸውንም ለኢትዮጵያ ሕዝብ ወንጌልን ለማድረስ የተሾሙ በኩራት አድርገው አቅርበዋል፡፡
የመጀመሪያውን ትርጉም ወይም መልእክት በማጉላትም የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስም የዚህን የ«ተሐድሶ» መሠሪ አካሔድ በውል በመረዳት አውግዞ በመለየትና ውግዘት በማስተላለፍ ለ2ሺሕ ዘመናት ወንጌልን ስትሰብክ የነበረች ቤተ ክርስቲያንን ልዕልናና ክብር አጉድፎ በወንጌል ሰባኪነት ስም በማጭበርበር ፕሮቴስታንታዊ ኑፋቄ ለመዝራት ተሐድሶ እያደባ መሆኑን አጋልጧል፡፡ ጠቅላይ ቤተክህነት ከሰጠው ሰፊ መግለጫ ውስጥ ይህን የተመለከተውን በአጭሩ እንደሚከተለው እናስታውስ፡፡

 

«አሮጊቷ ሣራ ወለደች» የሚል ኃይለ ቃል መናገራቸው ተዘግቧል፤ መናፍቃኑ ይህን የተናገሩት የእነሱን ከጥንታዊቷ ቤተ ክርስቲያናችን አፈንግጦ መውጣት የዘጠና ዓመት እድሜ ከነበራት እና ከቅድስት ሣራ ከተወለደው ከይስሐቅ ልደት ጋር ለማነጻጸር በመፈለግ መሆኑ ግልጽ ነው፡፡


የይስሐቅ እናት ቅድስት ሣራ በመሠረቱ እናትና አባቱን የሚያከብርና የሚያስከብር እንጂ የሚያዋርድ፣ እናትና አባቱን የሚያስመሰግን እንጂ ሰድቦ የሚያሰድብ፣ በእናትና አባቱ እግር የሚተካ እንጂ እናትና አባቱን የሚክድ፣ በወላጆቹ የተመረቀ እንጂ የተረገመ ልጅ እናት አይደለችም፡፡


በቅድስት ሣራ አምሳል የተጠቀሰችው ጥንታዊቷ ቅድስት ቤተ ክርስቲያናችንም እንዲሁ እናቱን ለመሸጥና ለመለወጥ የሚያስማማ፣ እናቱን ሲሰድብና ሲነቅፍ ሐፍረት የማይሰማው ርጉም ልጅ እናት አይደለችም፤ ቤተ ክርስቲያናችን እንዲህ ያለ ልጅ አልወለደችም፣ አትወልድምም፡፡


ጠላትና አረም ሳይዘሩት ይበቅላል እንደሚባለው፣ በአንድ የስንዴ ማሳ ላይ የበቀለ አረም ቢኖር ያ አረም ሳይዘራ የበቀለ መሆኑን ማረጋገጥ አስቸጋሪ እንደማይሆን ሁሉ እነዚህ መናፍቃንም በቤተ ክርስቲያናችን የስንዴ ማሳ ላይ ሳይዘሩ የበቀሉ ጠላቶች እንደሆኑ መገንዘብ አስቸጋሪ አይሆንም፡፡ በምሳሌ ዘር እንደተጠቀሰው /ማቴ.13፥24-30/ በንጹሕ ስንዴ ማሳ ላይ ጠላት የዘራው ክርዳድ ሊበቅል እንደሚችልም ታውቋል፡፡ እነዚህ መናፍቃንም የጠላት እንጂ የቤተ ክርስቲያናችን አበው ተክል ባለመሆናቸው ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን እንደ ተወለዱ አድርገው ራሳቸውን ከማስተዋወቅ ይልቅ የማን ልጆች እንደሆኑ ቢጠይቁ ዕውነቱን ለማወቅ በቻሉ ነበር፡፡


አሁንም ቢሆን ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ ለጢሞቴዎስ በጻፈው ሁለተኛ መልእክቱ «በኋላ ዘመን አንዳንድ ሰዎች ገንዘብን የሚወድዱ፣ ራሳቸውን የማይገዙ፣ ሐሜተኞች፣ መልካም የሆነውን ነገር ሁሉ የማይወዱ ከዳተኞች ይሆናሉ፤ የአምልኮት መልክ አላቸው፤ ኃይሉን ግን ይክዱታል፤ ከእነዚህ ደግሞ ራቅ ወደ ቤቶች ሾልከው እየገቡ ኃጢአታቸው የተከመረባቸውን በልዩ ልዩ ምኞትም የሚወሰዱትን፣ ሁልጊዜም እየተማሩ እውነትን ወደ ማወቅ ከቶ ሊደርሱ የማይችሉትን… የሚማርኩ ከእነዚህ ዘንድ ናቸውና» /1ጢሞ. 3.1-7/ ሲል እንደተናገረው እነዚህ መናፍቃን ከዚህ የትንቢት ዘመን የተወለዱ እንጂ የቤተ ክርስቲያናችን ልጆች አለመሆናቸውን በግልጽ መንገር ግዴታ ይሆናል፡፡ /መጋቢት 26 ቀን 1990 ዓ.ም/

ጠቅላይ ቤተክህነት የተነተነበት መንገድ እንዳለ ሆኖ የ«ተሐድሶ» ቡድን «አሮጊቷ» የሚለውን ቃል የመረጠበትን መሠረታዊ ምክንያት በውል ማጤን ይገባል፡፡ ቅዱስ ጳውሎስ ወንጌልን የምትሰብክን ቤተ ክርስቲያን ከቅድስት ሣራ ጋር አነጻጽሮ ባቀረበበት መንገድ አስበው ተናግረውት ቢሆንማ ከኦርቶዶክሳዊት ቤተ ክርስቲያን አፈንግጠው የፕሮቴስታንት ፓስተሮች ባዘጋጁት በዚያ የስድብ ጉባኤ ላይ የቤተ ክርስቲያኒቱን የሃይማኖት ትምህርትና ሥርዓት የምእመ ናንን ሕይወት ባላዋረዱ ባላናናቁ ነበር፡፡ ነገር ግን «አሮጊት /አሮጌ» የሚለውን ቃል የመረጡት ቤተ ክርስቲያን አርጅታለችና ማደስ አለብን ለሚለው አስተሳሰብ መንደርደሪያ ነው፡፡ እነዚህ የተሐድሶ መናፍቃን ተወግዘው ቢለዩም በውጪም በውስጥም ሆነው ቤተ ክርስቲያንን ለመገዝገዝና አስተምህሮአቸውን አንዳንድ የቤተ ክርስቲያኒቱ «መምህራን» አውቀውም ሳያውቁም በየዓውደ ምህረቱ እንዲያስተጋቡ ተፅዕኖ መፍጠራቸውን ቀጥለዋል፡፡

እነ አባ ዮናስ የ«አሮጊቷ ሣራ ወለደች» ቃላቸውን ከአዋጁ ከ12 ዓመታት በኋላ አሁን በይፋ ደግሞ «ቤተ ክርስቲያንን አሪታዊት፣ ጨለማ ውስጥ ናት ሲሉ አሮጊቷ ሣራ ዛሬ እኔን ወለደች፣ እገሌን ወለደች፣ እገሌን ወለደች…» የሚል ከእነ አባ ዮናስ ጋር የቃልና የስሜት ዝምድና ያለው የአዋጅ ቃል በአንዳንድ ሰባኪያን ነን ባዮች ተሰምቷል፡፡ በአባ ዮናስና በእነዚህ ሰባኪያን መካከል ያለው የአቀራረብ ልዩነት የአባ ዮናስ በኤግዚቢሽን ማዕከል፣ እነዚህ ደግሞ በራሷ በቤተ ክርስቲያኒቱ ዓውደ ምህረት ላይ ማወጃቸው ነው፡፡

ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ ያስተማረው ትምህርት ቃሉም ትርጓሜውም የታወቀ ሆኖ ሳለ ቤተ ክርስቲያናችንም ከጨዋይቱ የተወለድን ክርስቲያኖች አንድነት መሆኗ ለ2ሺሕ ዘመን የተመሰከረ ሆኖ ሳለ የአሁኖቹ «ሰባክያን» ራሳቸውንና ጓደኞቻቸውን ነጥለው «የተስፋው ወራሾች የአሮጊቷ የሣራ ልጆች» እያሉ የሚያቀርቡበት ገለጻ ትርጓሜ ይፋ መሆን አለበት፡፡

በመሠረቱ በሐዋርያው በቅዱስ ጳውሎስ የተሰበከውን ምሳሌያዊ ትምህርት ይዞ ተንትኖ ማስተማር ተገቢ ነው፡፡ ነገር ግን ከአርባ ሚሊዮን በላይ ምእመናን ባሉበት ጥንታዊት እና ሐዋርያዊት ቤተ ክርስቲያን ውስጥ ራሳቸውንና እነርሱ የመረጧቸውን የቡድን አባላት አባ ዮናስ ባቀረቡበት መንገድ «የአሮጊቷ ሣራ» ብሎ የጠሩበት ቤተ ክርስቲያን እነርሱን ከመውለዷ በፊት ምን ጎድሎባት፣ ምንስ አጥታ ነበር ? ቅዱስ ጳውሎስ መካኒቱ፣ ጨዋይቱ፣ እመቤቲቱ እያለ የጠራበት ቅጽል እያለ «አሮጊቷ» የሚለውን በማስጮኽ ማቅረብስ ለምን ተፈለገ ? ቀጥተኛ ምንጩስ ማነው ? ምንድነው ? እነዚህ ሁሉ ጥያቄዎች መመለስ ያለባቸው ናቸው፡፡ እነ አባ ዮናስ «አሮጊቷ ሣራ» ያሏትን ቤተ ክርስቲያንን ድንግል ማርያምን፣ ተክለሃይማኖትን፣ ጊዮርጊስን በልብሽ አኑረሻልና አውጪ እያሉ በአደባባይ ድፍረት ተናግረዋል፡፡ በእነዚህ «ሰባክያን» የ«አሮጊቱ ሣራ» አስተምህሮ ውስጥ ያለው አንድምታስ ምንድነው ? እነ አባ ዮናስ በ«አሮጊቷ ሣራ» አስተምህሮአቸው «ቤተክርስቲያኒቱ በ4ኛው ክፍለ ዘመን አባ ሰላማ ከሳቴ ብርሃን ከሰበኩበት ጊዜ በኋላ ወንጌል አልተሰበከችም የወላድ መካን ሆና የኖረች ናት» በማለት አሁን እነርሱ ያንን ለመፈጸም የተወለዱ አድርገው አቅርበዋል፡፡ የእነዚህ ሰባክያን የ«አሮጊቷ ሣራ» አስተምህሮስ ከዚህ አንጻር ምን ይላል ?

ይህ ብቻ ሳይሆን አባ ዮናስ «ይህ ትውልድ የኢያሪኮን ግንብ ያፈርሳል» ያለው ቤተ ክርስቲያኒቱን ዒላማ ያደረገ ፉከራው በእነዚህ ሰባክያን የመዝሙር መንደርደሪያዎች ውስጥ ከሚነገረውና «መዶሻ ያልያዘ ሠራዊት ኢያሪኮን ያፈርሳል…» ከሚሉት አዝማች ቃል ጋር ያለውንም የትርጉም ዝምድና መጤን እንዳለበት         እንድናስብ ያስገድዳል፡፡ በተመሳሳይ ይህንኑ መንገድ ተከትሎ በየደረጃው ምእመናን እነ አባ ዮናስ በግልጽ ያወጁት የ«ተሐድሶ» ፕሮቴስታንታዊ አስተምህሮ ዓውደ ምህረቶቻችን ላይ አሁንም ወደቆሙ «መምህራን» መሻገር አለመሻገሩን ቃሎቻቸውን እያጠኑ ለመመርመር ተገደዋል፡፡ የቤተ ክርስቲያናችን የሚመለከታቸው አካላትም የእነዚህን «ሰባኪያን» ትምህርት መርምረው ካለማወቅ በስሕተት የቀረበ ትምህርት መሆኑን ወይም በድፍረት የቀረበ ለ«ተሐድሶ» ዘመቻ የጥፋት ፈትል ማጠንጠኛ መሆን አለመሆኑን ለይተው እንደሚያቀርቡ ተስፋ እናደርጋለን፡፡

ምንጭ፦ ሐመር 19ኛ ዓመት ቁጥር 2

ወስብሐት ለእግዚአብሔር

የተሐድሶ መናፍቃን እንቅስቃሴን አስመልክቶ ቅዱስ ፓትርያሪኩ ከማኅበረ ቅዱሳን አመራር ጋር ውይይት አደረጉ

 

ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ጳውሎስ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት የዓለም አብያተ ክርስቲያናት ምክር ቤት ፕሬዚዳንት የዓለም ሃይማኖቶች ለሰላም የክብር ፕሬዚዳንት ከማኅበረ ቅድሳን ሥራ አመራርና አስፈጻሚ ጉባኤያት ተወካዮች ጋር ነሐሴ 15 ቀን 2003 ዓ.ም ስለ ማኅበሩ አገልግሎትና በተለይም የተሐድሶ መናፍቃንን እንቅስቃሴ አስመልክቶ ውይይት ማድረጋቸውን የማኅበሩ ጽ/ቤት አስታወቀ፡፡

በቅዱስ ፓትርያሪኩ ጽ/ቤት በተካሔደው ውይይት፤ የማኅበሩ አመራር ስለተሐድሶ መናፍቃን እንቅቃሴ አራማጆችና ተቋማት የተዘጋጁ ልዩ ልዩ መጻሕፍት እንዲሁም በምስል ወድምጽ /VCD/ የታገዘ ገለጻና ማብራሪያ ቀርቧል፡፡

ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ጳውሎስም በቤተ ክርስቲያኒቱ ላይ እየተፈጸመ ያለውን ድርጊት ከተመለከቱ በኋላ “ይህ ሁሉ የንብ ሠራዊት እያለ ወረራው ሲካሔድ የት ነበራችሁ?” የሚል የአባትነት ጥያቄያቸውን አቅርበዋል፡፡

ቅዱስነታቸው፤ ቤተ ክርስቲያንን እና ምእመናንን ከእንዲህ ዓይነቱ ተግባር መጠበቅ የሁሉም ሓላፊነት እንደሆነ ጠቅሰው፤ ከዚህም በላይ መብታችንን በሕግ ሳይቀር ማስከበር እንደሚኖርብን ገልጸዋል፡፡ ማኅበረ ቅዱሳን በልጅነት ድረሻው እያከናወነ ያለው አገልግሎት እንደተጠበቀ ሆኖ፤ የግለሰቦችን ስም እየጠቀሰ “ተሐድሶ ናቸው” ማለት ግን አግባብ እንዳልሆነና ይህም የቤተ ክርስቲያናችንን አሠራር ጠብቆ መፈጸም እንዳለበት አሳስበዋል፡፡

የማኅበሩ አመራር አባላትም፤ በአሁኑ ወቅት እየተከናወነ ያለው ሥራ የተሐድሶ መናፍቃን እንቅስቃሴ ምንነት፣ በእንዴት ዓይነት ሁኔታና ደረጃ ላይ እንደሚገኝ ምእመናን ግንዛቤ አግኝተው ራሳቸውን እንዲጠብቁ፤ እንዲሁም ፕሮቴስታንታዊ የተሐድሶ መናፍቃን እንቅስቃሴን የሚመሩና የሚደግፉ ተቋማትን፣ ስልትና አሠራራቸውን የማሳወቅ ሥራ እንደሆነ ገልጸዋል፡፡

ማኅበረ ቅዱሳን በ1990 ዓ.ም የተሐድሶ መናፍቃንን እንቅስቃሴ የማጋለጥ ሰፊ ሥራ ባከናወነበት ወቅት፤ በቤተ ክርስቲያን ውስጥ ሆነው ነገር ግን ፕሮቴስታንታዊ የተሐድሶ ኑፋቄ በምእመኑ ውስጥ በመዝራት ጉልህ ድርሻ የነበራቸው “መነኮሳት” ተወግዘው እንዲለዩ ሲደረግ፤ በቤተ ክርስቲያን ሥርዐትና አሠራር መሠረት ማኅበሩ አስፈላጊውን መረጃና ማስረጃ ለሊቃውንት ጉባኤ አቅርቦ ከዚያም በኋላ በቅዱስ ሲኖዶስ የመጨረሻ ውሳኔ እንዲሰጥ ያደረገበት ሁኔታ እንደነበረ፤ የማኅበሩ አመራር አባላት በውይይቱ ላይ አስታውሰው፤ ማኅበሩ የቅድስት ቤተ ክርስቲያንን ሥርዐትና አሠራር ጠንቅቆ እንደሚያውቅና ይህንኑ ለማስጠበቅ ጠንክሮ እንደሚሠራ ገልጸዋል፡፡ አሁንም ማኅበረ ቅዱሳን እየሠራ ያለው የግለሰቦችን ስም በመጥቀስ “ተሐድሶ” የማለት ሳይሆን፤ ስለ ተሐድሶ መናፍቃን እንቅስቃሴ ምንነትና ስልት ግንዛቤ እንዲኖር በማድረግ ምእመናን ራሳቸውን እንዲጠብቁ የማሳወቅ ሥራ እየተከናወነ እንደሆነ ማብራሪያ ተሰጥቷል፡፡
ወደፊትም በዚህ የተሐድሶ መናፍቃን እንቅስቃሴና ሥራ ላይ የተጠመዱ ነገር ግን በቤተ ክርስቲያኒቷ ውስጥ የሚገኙ አካላትንና ደጋፊዎችን፤ የቅድስት ቤተ ክርስቲያንን ሥርዐትና አሠራር በመጠበቅ ማኅበረ ቅዱሳን ለሚመለከታቸው የቤተ ክርስቲያን አካላትና አባቶች እንደሚያቀርብ በማኅበሩ አመራር አባላት ለቅዱስነታቸው ተገልጿል፡፡

ብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያሪኩም፤ በበቂ መረጃ በማስደገፍ ለሚመለከተው የቤተ ክርስቲያን አካል በማቅረብ ሁሉም ነገር በሕግና በሥርዐት መከናወን እንዳለበት አባታዊ መመሪያ ሰጥተዋል፡፡

ብፁዕ አቡነ ሚካኤል አረፉ፡፡

የሰሜን ምዕራብ ትግራይ ሽሬ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስና የቅዱስ ሲኖዶስ አባል ብፁዕ አቡነ ሚካኤል ነሐሴ 8 ቀን 2003 ዓ.ም አርፈዋል። በአንብሮተ እድ ከተሾሙበት ከነሐሴ 22 ቀን 1997 ዓ.ም ጀምሮ በአሁኑ ሀገረ ስብከታቸው የተሾሙ ሲሆን በመካከል ለተወሰኑ ወራት የወላይታ፣ ዳውሮና ኮንታ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ሆነው አገልግለዋል።

የሐሞት ጠጠር ሕመም የነበረባቸው ብፁዕነታቸው የቀዶ ጥገና ህክምናቸውን በቅዱስ ገብርኤል ሆስፒታል በመከታተል ላይ የነበሩ ሲሆን በመካከል ከሰመመናቸው መንቃት ሳይችሉ እንደቀሩ ምንጮቻችን ገልጸዋል። ቀጣይ የአስከሬን ምርመራ ከተደረገ በኋላ ምክንያቱ ሊገለጽ እንደሚችልም ይገመታል።

በቅዱስ ሲኖዶስ ምርጫ በትግራይ ክልል ሰሜናዊ ምዕራብ ዞን የተሾሙት የቀድሞው ሊቀ ሥልጣናት አባ ተክለሚካኤል ዓባይ አሁን ብፁዕ አቡነ ሚካኤል በቀድሞው አድዋ አውራጃ በአምባ ሰነይቲ ወረዳ በላውሳ ቅዱስ ገብርኤል አካባቢ ከአለቃ ዓባይ ወ/ገብርኤልና ከወ/ሮ ታደለች ንጉሤ በ1942 ዓ.ም ተወለዱ፡፡

በታላቁ በደብረ ዓባይ ገዳም ከመምህር አበራና ከመምህር ገብረ እግዚአብሔር ከመሠረተ ትምህርት እስከ ጸዋትወ ዜማ፣ ከመምህር የኔታ የኋላእሸት መዝገበ ቅዳሴ ጠንቅቀው ከተማሩ በኋላ በመምህርነት ተመርቀዋል፡፡

በዋልድባ ገዳም መዓርገ ምንኩስና ተቀብለዋል፡፡ ጎንደር ክፍለ ሀገር በወገራ አውራጃ በጉንተር አቦ ከመሪጌታ ሐረገወይን፣ ጎንደር ከተማ ከመምህር እፁብ ቅኔ ተምረው ተቀኝተዋል፡፡

በሐረርጌ ክፍለ ሀገር ቁልቢ ቅዱስ ገብርኤል ገዳም እያገለገሉ የአንደኛና መለስተኛ ሁለተኛ ደረጃ ዘመናዊ ትምህርታቸውን ተከታትለዋል፡፡ በሰዋስወ ብርሃን ቅዱስ ጳውሎስ ት/ቤት በአዳሪነት ገብተው የሁለተኛ ደረጃ ትምህርታቸውን አጠናቀዋል፡፡

በውጪ አገር እንግሊዝ ለንደን ሴንት ኤድዋርድስ ኮሌጅ የመጽሐፍ ቅዱስ ኮርስና የእንግሊዝኛ ቋንቋ ለአንድ ዓመት፣ ግሪክ አገር በአቴንስ ዩኒቨርስቲ ለስድስት ዓመታት ከፍተኛ መንፈሳዊ ትምህርት በመማር በቲኦሎጂ ማስትሬት ዲግሪ፣ በአሜሪካ ሆሊ ክሮስ በተባለው የግሪክ ሴሚናሪ ከሲስተማቲክ ቲኦሎጂ ዲፕሎማ፣ በቦስተን ዩኒቨርስቲ የኤስ.ቲኤም ወይም በፓስተራል ካውንስሊንግ /ሳይኮሎጂ/ በማስተርስ ዲግሪ ተመርቀዋል፡፡

በተለያዩ ጊዜያት በጠቅላይ ቤተ ክህነት የእስኮላር ሽፕ ዋና ክፍል ኃላፊ፣ የኢትዮጵያ ገዳማት መምሪያ ኃላፊ፣ የቅዱስ ጳውሎስ ከፍተኛ መንፈሳዊ ት/ቤት ዲን፣ በወቅቱ የኤርትራ ሀገረ ስብከት ዋና ሥራ አስኪያጅ፣ የዕቅድና ጥናት መምሪያ ኃላፊ፣ የትንሣኤ ዘጉባኤ ማተሚያ ቤት የበላይ ኃላፊ፣ የቅድስት ሥላሴ ካቴድራል አስተዳዳሪ፣ በጠቅላይ ቤተ ክህነት የካህናት አስተዳደር መምሪያ ኃላፊ፣ የትምህርትና ሥልጠና መምሪያ ሐላፊ በመሆን አገልግለዋል፡፡

የብፁዕነታቸው የቀብር ሥነሥርዓት ዛሬ ነሐሴ 10 ቀን 2003 ዓ.ም ከዘጠኝ ሰዓት ጀምሮ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ጳውሎስ ፓትርያርክ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ፣ ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳትና እንግዶች እንዲሁም ምእመናን በተገኙበት በቅድስት ሥላሴ ካቴድራል ይፈጸማል።

ምንጭ፦ ስምዐ ጽድቅ ጋዜጣ 19ኛ ዓመት ቁጥር 12

የ6 ወር የሥራ አመራር ስብሰባ ውሳኔዎችን አስመልክቶ ከማኅበሩ የሕዝብ ግንኙነት አገልግሎት የተሰጠ መግለጫ

በማኅበራችን ማኅበረ ቅዱሳን ወቅታዊ ጉዳዮች ዙሪያ ውይይት ያደረገው የ6ወሩ የሥራ አመራር ስብሰባ ወሳኔዎችን አስመልቶ ከማኅበሩ ሕዝብ ግንኙነት አገልግሎት የተሰጠ መግለጫ።

በማኅበረ ቅዱሳን ላይ የተሠሩ የሐሰት ሰነዶችን አስመልክቶ ከማኅበሩ ሕዝብ ግንኙነት አገልግሎት የተሰጠ መግለጫ፡፡

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!

በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን በሰንበት ት/ቤቶች ማ/መምሪያ ሥር ተዋቅሮ በርካታ መንፈሳዊና ማኅበራዊ አገልግሎቶችን ለቤተ ክርስቲያን በማበርከት ላይ የሚገኘው ማኅበረ ቅዱሳን በቅዱስ ሲኖዶስ በተሰጠው መተዳደሪያ ደንብ መሠረት በመመራት ሕጋዊ በሆነ መንገድ አገልግሎቱን በመስጠት ላይ የሚገኝ ማኅበር ነው፡፡

ይሁን እንጂ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያንን ዕድገትና ልማት የማይፈልጉ አፅራረ ቤተ ክርስቲያን የማኅበሩን መልካም ስም በማጥፋት አገልግሎቱን ለማሰናከል በየጊዜው ይጥራሉ፡፡ በተለይም ከቅርብ ጊዜ ወዲህ የማኅበሩን ስም ለማጥፋት አመች ነው ብለው ያሰቡትን የሐሰት ሰነድ የማዘጋጀት ተግባራቸውን አጠናክረው ቀጥለዋል፡፡ ከዚህ በፊት በስምዐ ጽድቅ ጋዜጣ የግንቦት ወር ልዩ ዕትም “የማኅበረ ቅዱሳን የ25 ዓመት ዕቅድ” ብለው ያዘጋጁትን የሐሰት ሰነድ አስመልክተን እንደገለጽነው ሁሉ አሁንም ሁለት የሐሰት ደብዳቤዎች በማኅበሩ የመቀሌ ማዕከል ስም ተዘጋጅተው በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን በሰንበት ት/ቤቶች ማ/መምሪያ መካነ ድር ተለቅቀዋል፡፡

እጅግ በጣም የሚያሳዝነው የሐሰት ሰነዶቹ መዘጋጀት ሳይሆን እነዚህ በከባድ ወንጀል ሊያስጠይቁ የሚችሉ የተጭበረበሩ ሰነዶች የቤተ ክርስቲያኒቱ መምሪያ ነኝ በሚል ተቋም መካነ ድር ላይ መለቀቃቸው ነው፡፡

ከሐሰት ሰነዶቹ መካከል አንዱ የተሐድሶ መናፍቃንን ዝርዝር የሚገልጽ ሲሆን ሁለተኛው ደግሞ የመቀሌ ማዕከል የሒሳብ ሪፖርት አስቸጋሪ መሆኑን ይገልጻል፡፡

ማኅበረ ቅዱሳን ይህንን የሐሰት ሰነድ አስመልክቶ ድርጊቱ እንዲጣራና ሕጋዊ እርምጃ እንዲወሰድ ለቅዱስ ሲኖዶስ፣ ለመንበረ ፓትርያርክና ለሚመለከታቸው ሁሉ የሚያቀርብ ሲሆን በሐሰት ሰነዶቹ ስማቸው የተነሱ አካላትም ድርጊቱ የማኅበሩ አለመሆኑን እንዲያውቁና ምዕመናንንም እውነቱን እንዲረዱ ይህ መግለጫ ተሰጥቷል፡፡

በሰንበት ትምህርት ቤቶች ማደራጃ መምሪያ መካነ ድር የተለቀቁት ሁለቱም የሐሰት ሰነዶች በቁጥር መቀጽቤ 99/2003 ዓ.ም እና መቀጽቤ 100/2003 ዓ.ም “ለማኅበረ ቅዱሳን የሕዝብ ግንኙነት አገልግሎት ክፍል” በሚል አድራሻ የተላኩ ናቸው፡፡

ነገር ግን ከመቀሌ ማዕከል መዝገብ ቤት ቀሪ ሆነው የተገኙት እውነተኞቹ ደብዳቤዎች በማኅበረ ቅዱሳን የመቀሌ ማዕከል በቁጥር መቀጽቤ 99/2003 ዓ.ም እና በቁጥር መቀጽቤ 100/2003 ዓ.ም በቀን 05/09/2003 ዓ.ም በማዕከሉ የሰባኬ ወንጌልነት ተቀጥረው ሲያገለግሉ ለነበሩ /አሁን የIT ምሩቅ ናቸው/ ግለሰብ የሥራ ስንብትና የሥራ ልምድ መስጠትን የሚመለከቱ ናቸው፡፡ መመልከት እንደሚቻለው የሐሰት ሰነዶቹም ሆነ  እውነተኞቹ ደብዳቤዎች ቁጥራቸው ተመሳሳይ ነው።

በቀጣይነትም በሰነዶቹ ላይ ማጭበርበሩ የተደረገው በማዕከሉ መዝገብ ቤት ከተገኙት ደብዳቤዎች ሳይሆን ምን አልባትም ከባለጉዳዩ እጅ ከወጡት ደብዳቤዎች ሊሆን እንደሚችልም አንባቢ ያስተውል፡፡ ምክንያቱም የማኅተሞቹና የፊርማዎቹ አቀማመጥ ተመሳሳይነት የላቸውምና አልተጭበረበሩም ብለን እንዳናስብ ያደርገናልና፡፡

ወደ ዝርዝር ጉዳዮቹ ስንገባ ደግሞ፣

1. በአድራሻው ላይ የተጠቀሰው የማኅበረ ቅዱሳን የሕዝብ ግንኙነት አገልግሎት እንደ ክፍል ያልተዋቀረ እንደሆነ ይታወቃል። በአድራሻው የሚመጡለት ደንዳቤዎችም “ለማኅበረ ቅዱሳን የሕዝብ አገልግሎት” ተብለው ይደርሱታል እንጅ “ለማኅበረ ቅዱሳን የሕዝብ ግንኙነት አገልግሎት ክፍል” ተብሎ በአድራሻ አይጠራም። ከዚህ በፊት በመካነ ድራችን የተለቀቁትንና በአገልግሎቱ እየወጡ የሚታተሙትን የመጽሔተ ተልዕኮ መጽሔቶችንም መመልከት ይቻላል።

2. በቁጥር መቀጽቤ 99/2003 ዓ.ም የተጻፈው የሐሰት ሰነድ “በቀን 17/07/2003 ዓ.ም በቁጥር አአ/ልዩ/05/2003 ዓ.ም 11 ገጽ አባሪ አድርጋችሁ በጻፋችሁልን ደብዳቤ ተንተርሰን የሰራነው ሥራ…” ብሎ ከማኅበረ ቅዱሳን ዋናው ማዕከል ጽ/ቤት ለመቀሌ ማዕከል የተላከ ለማስመሰል ይሞክራል፡፡ ነገር ግን በማኅበረ ቅዱሳን ስም የሚወጡት ማናቸውም ደብዳቤዎች ቁጥራቸው ማቅ በማለት የሚጀመሩ ናቸው። በተጨማሪም የማኅበሩ ዋናው ማዕከል ጽ/ቤት ለመቀሌ ማዕከል ልኮታል ተብሎ የተጠቀሰው ደብዳቤ የተጻፈበትን ቀን ስንመለከት፤ 17/07/2003 ዓ.ም የዋለው ቅዳሜ ዕለት ሲሆን በዚህ ቀን የማኅበረ ቅዱሳን መደበኛ አገልግሎት የማይኖርበት ዕለት መሆኑ ይታወቃል፡፡ ምን አልባት ካላንደር ሳይዙ ጽፈውት ይሆን? የሰንበት ት/ቤቶች ማደራጃ መምሪያው በየጊዜው ከማኅበሩ ደብዳቤዎች ይደርሱታል። አአ/ልዩ/05/2003 ዓ.ም የሚለው ቁጥር አስተውሎት ውስጥ ሳይገባ በመካነ ድሩ በችኮላ መለቀቁ ማኅበሩን ለመክሰስ ካለው የግለሰቦች ጉጉት የተነሣ ይሆን?

3. በቁጥር መቀጽቤ 99/2003 ዓ.ም በተጻፈው የሐሰት ሰነድ ሒሳብ ክፍልንና ትምህርትና ሐዋርያዊ አገልግሎት ክፍልን የሚመለከት ምንም ጉዳይ ሳይኖረው ወደ ሒሳብ ክፍልና የትምህርትና ሐዋርያዊ አገልግሎት ክፍል ግልባጭ መደረጉ ለምን ይሆን? ለዚያውም በማደራጃ መምሪያው መካነ-ድር እንደተገለጠው የተደበቀ የስለላ ሥራ ከሆነ እንዴት ለእነዚህ ክፍሎች ግልባጭ ሊደረግ ይችላል? ሒሳብ ክፍልስ ከሕዝብ ግንኘነት አገልግሎቱ ጋር ምን ግንኙነት ይኖረው ይሆን? እነዚህ ጥያቄዎች በጥብቅ ሊመለሱ የሚገባቸው ናቸው።

ምን አልባት ለማጭበርበር በሚደረገው ሙከራ የአንዱ ደብዳቤ ሐሳብ ከሌላው ደብዳቤ ላይ ተቀያይሮባቸው ይሆን? የየትኛው ደብዳቤ ሃሳብ ለየትኛው ክፍል ግልባጭ መደረግ እንዳለበት ፊደል የቆጠረ የሚያስተውለው ነው።

4. በማኅበሩ የአገልግሎት ክፍሎች የሚመደቡት አባላት በሰበካ ጉባኤ ወይም በሰንበት ትምህርት ቤት የታቀፉ መሆን እንዳለባቸው በመተዳደሪያ ደንቡ አንቀጽ 6/ለ ተጠቅሶ ሳለ “የሰ/ት/ቤቶችን በተመለከተ፣ የማኅበሩ አባላት በሙሉ በየሰንበት ትምህርት ቤቱ በአባልነት እንዲያገለግሉ ተደርጓል፤ እየተሰራበት ይገኛል።” የሚለው ዓረፍተ ነገር የማኅበሩ አባላት የሰ/ት/ቤትና የሰበካ ጉባኤ አባላት አይደሉም የሚለውን የአባ ሠረቀን የሐሰት የክስ ሐሳብ ለማጽናት ይሆን?

ማኅበረ ቅዱሳን በሰ/ት/ቤቶች ማደራጃ መምሪያ ስር የሆነው በራሱ ጥያቄ አቅራቢነት ነው፡፡ ይኸውም አባላቱ በሰ/ት/ቤቶች ታቅፈው እንዲያገለግሉለት ካለው ጽኑ ፍላጎት የተነሣ እንደሆነ ግንዛቤ ውስጥ ሊገባ ያስፈልጋል፡፡

የሐሰት ሰነዶቹን አጠቃላይ ሐሳብ ለመረዳት ለሚሞክር ሰው፥ አጭበርብሮ ማኅበረ ቅዱሳንን ለመክሰስ እንዲሁም የፀረ ተሐድሶ መናፍቃንን ዘመቻ ለማጨናገፍ የሚደረግ ሴራ መሆኑን ማኅበሩ አያጣውም፡፡

ማኅበረ ቅዱሳንና ሌሎች ማኅበራትም በሚያደርጉት የፀረ ተሐድሶ መናፍቃን እንቅስቃሴ በቅዱስ ሲኖዶስ ተወግዘው ከተለዩት ግለሰቦች ውጭ የማንም ስም በግልጽ ተጠቅሶ አያውቅም፡፡ የተሐድሶ መናፍቃንን ምልክቶች ግን ይጠቁማል፡፡ ከተሰጡት መረጃዎች እንዲሁም ከምልክቶቹ ምእመኑ እየተረዳው እንደመጣ ይታመናል፡፡

የተሐድሶ መናፍቃኑ እንቅስቃሴ ዘርፈ ብዙ የሆነ፣ በብዙ ሚሊዮኖች በጀት ተመድቦለት፣ በዓላማ የቤተ ክርስቲያንን ትምህርት ለመበርዝና ለማጥፋት እጅግ ተምረዋል ተብለው በሚገመቱ ሰዎችና በግዙፍ ድርጀቶች የሚመራና የሚታገዝ ቤተ ክርስትያኗን የሚያናጋ ነው።

ነገር ግን ትግሉ ከተጀመረ ጀምሮ አንዳንድ ግለሰቦች እንቅስቃሴውን ከግለሰቦች ጋር እያያዙት ይገኛሉ፤ የተሐድሶ ኑፋቄ ዘመቻንም እያፋጠኑት ይገኛሉ።

ይህንን ለመከላከል የሚደረገውን ጥረት ለማስተጓጐል ብሎም የምእመኑን ትክክለኛ ትኩረት ለማሳጣት የሚደረግ እንቅስቃሴ እንደሆነ እናምናለን፡፡

ምን አልባት ማኅበረ ቅዱሳን ስም አጥፊ ነው፣ የአባቶችና የሊቃውንት ከሳሽ ነው የሚለውን የአንዳንዶችን ክስ ለማጠናከር ይሆን? አንባቢ ይመርምር።

እግዚአብሔር ሀገራችን ኢትዮጵያን እና ቅድስት ኦርቶዶክሳዊት ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያንን ይጠብቅልን፡፡

ወስብሐት ለእግዚአብሔር

የክብረ ገዳማት የቀጥታ ዘገባ

በስመአብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን።

እንደምን ዋላችሁ ውድ ምእመናን አሁን የክብረ ገዳማትን የቀጥታ ዘገባ ለማቅረብ እንሞክራለን።

9:23 በዝናብ ምክንያት ዘግየት ብሎ የጀመረው ይህ መርሐ ግብር በጠቅላይ ቤተ ክህነት እየተደረገ ይገኛል።

አዳራሹ ሞልቶ ምእመኑ ቆሞ በሚታይበት ሁኔታ በዚህ አመት ሙሉ ፕሮፌሰርነት ያገኙት ፕርፕፌሰር ሽፈራው በቀለ የጥናት ጽሁፋቸውን እያቀረቡ ይገኛሉ።

“የገዳማት ደጀሠላሞች ዋጋ እንደሌላቸው ታስቦ መፍረስ የለባቸውም። የገዳማት የትኛውም ቤት ከመፍረሱ በፊት በአርኪኦሎጂስቶች መታየት አለባቸው”

ፕሮፌሰር እንዳሉት በሀገራችን አንድ ባህል አለን በክፉ ቀን የከበረን ነገር መሬት ውንጥ መቅበር፣ ስለዚህ እንደተቀበረ ሊቀር ይችልሉና ገዳማትና አድባራት በጥ ንቃቄ ሊያዙ ይገባቸዋል።

በመካከለኛው ዘመን ገዳማከ የትምህርትና የባህል ማእከላት ነበሩ። በአክሱም ዘመነ መንግስት የጀመረው የገዳም ሥር ዓት በዛግዌ ጊዜ ወደ በጌምድር፣ ሸዋ፣ ወሎ አንዲሁም ወደ ደቡብ ክልሎች ተስፋፍትዋል።

9:40 ም እመናን  በተለያዩ ምክንያቶች መቆራረጡን ታግሳችሁ አሁንም ከእኛ ጋር እንደምትሆኑ እናስባለን

አሁንም ፕሮፌሰር ሽፈራው የጥናት ጽሁፋቸውን እያቀረቡ ይገኛሉ።

ገዳማት በተለያዩ ዘመናት ከሚገጥማቸው ችግሮችን ለምሳሌ መውደማቸውን ግንዛቤ ውስጥ አስገብተን ጥልቅ የአርኪኦሎጅ ጥናት ያስፈልጋል።

ገዳማት የቅርስ የጥበብ ምንጮች ናቸው። መስቀል በተለያዩ መልኮች የሚሰራበት ቤተ ክርስቲያን በየትም የለም፤ በምሥራቅ አብያተ ክርስቲያንት ዘንድ ቢሆን።

9:55 አሁን ማኅበረ ቅዱሳን በገዳማት በኩል ያደረገውን የ10 ዓመት የልማት እንቅስቃሴ አስመልክቶ ሪፖርት በወ/ሮ አለም ጸሐይ መሠረት እየቀረበ ነው።

“የግራኝ ዜና መዋ ዕል ጸሐፊ ከየረር እስከ አዋሽ ወንዝ ድረስ ብዙ ገዳማት መቃጠላቸውን ገልጽዋል።” ፕሮፌሰር ሽፈራው በቀለ

“በቀደምት የኢትዮጵያ ታሪክ የመንግስታት መጠናከር ለገዳማትና አድባራት መጠናከር አስተዋጾ ነበርው” ፕሮፌሰር ሽፈራው በቀለ

“ከአፄ ቴዎድሮስ ጀምሮ እየተጠናከረ የመጣው የገዳማት ሁኔታ በደርግ ዘመነ መንግስት ተዳፈነ።” ፕሮፌሰር ሽፈራው በቀለ

9:57 “በቆላ ተምቤን ከሚገኙት ወደ 28 የሚጠጉ ገዳማት አንዱ አብራ አንሳ ነው፤ አፄ ግ/መስቀል የመነኮሳቱን ብዛት አይተው እንደ አሳ ይበዛሉ ለማለት ስሙን እንደሰጡት ይነገራል። ዛሬ ግን 5 መነኮሳት ብቻ ቀርተዋል።” ወ/ሮ ዓለምፀሐይ

“እኛ ወደ ቦታው በሄድንበት ወቅት የሚበላ ስላልነበራቸው ከሳምንት በፊት የመጣ ጠላ ብቻ ሊሰጡን ችለዋል።”

“ሌላ ጊዜ አባ ሳሙኤል ወደ ሚባል ገዳም ሄድን፤ መቅደሱ ፈርስዋል፣ የመነኮሳትም መኖሪያ ፈርሶ ደግር ሆንዋል። አሁን በካህን ይለገላል”

“የአባ ሰላማ ከሳቴ ብርሃንን ገዳምን 4 ብቻ መነኮሳት የሚመግበው የ16 ዓመት ልጅ ነበር” ምእመናን ከላይ የቀረቡት ከወ/ሮ ዓለም ፀ ሐይ የግል የውሎ ዘገባ የቀረቡትን እጅግ ጥቂት ችግሮችን ነው። ከዚህ የከፋ ችግር ያለባቸው እንዳሉ ለመግለጽ እንወዳለን።

ለእነዚህ ገዳማት የቤተ ክርስቲያናችን የልማት ኮሚሽን የሚሰራው ሥራ ቢኖርም ማኅበረ ቅዱሳን ከቅዱስ ሲኖዶስ በተሰጠው መመሪያ መሠረት መሥራቱ የግድ ሆኖበታል። ብለዋል ወ/ሮ ዓለምፀሐይ

ስለሆነም ማኅበሩ ገዳማቱ ያላቸውን ሃብት በመጠቀም ዘላቂ ፕሮጀክክት ይሠራል። በዚህም ገዳማቱ ከቁሪትነት እንዲወጡ እንዲሁም እንዳይፈቱ ያደርጋል።

10:19 አቶ አጥናፍ ከ1992-2002 ዓም በማኅበሩ የተሰሩ ሥራዎችን ዳሰሳ አቅርበዋል።

ፕሮጀክቶቹ ከአነስተኛ ጊዜአዊ ድጋፍ እያደጉ የሄኡ ናቸው። ከ2000 ብር ሥራ የጀመረው የፕሮጀክት ሥራ አሁን እስከ 5 ሚሊዮን ብር የሚደርሱ የፕሮጀክት ሥራዎች እየተከናወኑ ነው።

እስከ አሁን በ6.9 ሚሊዮን ወደ 73 የሚጠጉ ፕሮጀክቶች ተተግብረዋል።

10:30 ክብረ ገዳማት ዘጋቢ ፊልም እየቀረበ ነው።

እስከ አሁን በተሰሩት ሥራዎች ገዳማቱ በራሳቸው ሰርተው መለወጥ እንደሚችሉ የተረዱበት ነው።

የዘጋቢ ፊልሙ ርዕስ “ሥርዓተ ገዳም በኢትዮጵያ”  ይሰኛል።

10:55 በቀጣይ ዓመታት እንደ እግዚአብሔር ፈቃድ እንደ አብረንታንት ዋልድባ፣ ደብረ በንኮል ባሉ ገዳማት ለመሥራት አቅደናል።

“የኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን መጻሕፍት ተቀምጠውበታል ወደ የሚባለው ጉንዳጉንዲ ስንሄድ የተቀበሉን አንድ መነኮስ ብቻ ነበሩ።” ዲ/ን ደረጀ ግርማ

ለ2004 ዓ.ም ወደ 18 የሚጠጉ ፕሮጀክቶች ለገዳማት አቅደናል። እነዚህ ፕሮጀክቶች ከላይ የተጠቀሱትን ጨምሮ ችግር እጅግ የጸናባቸው ናቸው። ዲ/ን ደረጀ የቃል መግቢያ ሰነዱን እያአስተዋወቁ ይገኛሉ።

“አብረን እንሥራ ለውጥ እናመጣለን” በማለት ዲ/ን ደረጀ መልእክት አስተላልፈዋል።

ለገዳማት እርዳታ ለማድረግ የምትፈልጉ gedamat_mk@yahoo.com ወይም 0173036604664000 የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ አራት ኪሎ ቅርንጫፍ

11:10 አሁን የምእመናን አስተያየት እየተደመጠ ነው።

“ታሪክ እየጠፋ ኢትዮጵያዊነት የለም። ገዳማት ደግሞ የታሪክ ምንጮች ናቸውና የቻልነውን ልናደርግ ይገባል።”

“ይህን መርሐ ግብር በሌሎች አድባራትም ብታደርጉት የተሻለ ገንዘብ በመሰብሰብ ገዳማትን መርዳት ይቻላል።”

“እናንተ እንደተለመደው አስታውሱን እንጅ ከአሰብነው በላይ እንሰጣለን።”

“ሌሎች የጠፉ ገዳማትንም ብታስታውሱን”

“ሦስት አራት ሆነን መርዳት እንችላለን?” “ይችላል፣ ለደረሰኝ እንዲመች ግን በአንድ ስም ብትከፍሉ ይሻላል።”

ወስብሐት ለእግዚአብሔር።

አባታችን ሆይ