ለሁለንተናዊ የቤተ ክርስቲያን እድገት የገዳማት ድርሻለሁለንተናዊ የቤተ ክርስቲያን እድገት የገዳማት ድርሻ
ታኅሣሥ 8 ቀን 2005 ዓ.ም.
በእንዳለ ደምስስ
ሪፓርታዥ
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያንን ተልእኮ ለማሳካት የገማት ድርሻ በሚል መሪ ቃል ማኅበረ ቅዱሳን ባዘጋጀው ዐውደ ጥናት ላይ ለመገኘት ከ65 ገዳማት የመጡ አበምኔቶችና እመምኔቶች ቅዳሜ ታኅሣሥ 6 ቀን 2005 ዓ.ም. ጠዋት በማኅበሩ ሕንጻ ላይ ስለ ማኅበሩ ሰፋ ያለ ግንዛቤ እንዲኖራቸው ለማስቻል በተዘጋጀው መርሐ ግብር ውይይት ሲያደርጉ ቆይተዋል፡፡
ከስዓት በኋላ በዐውደ ጥናቱ ላይ ለመገኘት በተዘጋጀላቸው መኪና ከማኅበሩ ዋና ጽሕፈት ቤት ወደ ኢትዮጵያ ስብሰባ ማእከል አዳራሽ ያመሩ ሲሆን ኢትዮጵያ ስብሰባ ማእከል እንደደረሱ በማኅበረ ቅዱሳን መዘምራን በዝማሬ በመታጀብ ወደ አዳራሹ ገብተዋል፡፡ በአዳራሹ ውስጥ የተገኙ ምእመናን በእልልታና ዝማሬ አቀባበል በማድረግ ገዳማውያን አባቶችም እጅ እየነሱና ምእመናን እየባረኩ ወደ ተዘጋጀላቸው ቦታ በማምራት ቦታቸውን ያዙ፡፡
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ዐቃቤ መንበር ብፁዕ አቡነ ናትናኤል ከብፁዐን ሊቃነ ጳጳሳት ጋር በመሆን እንደተገኙም ዐውደ ጥናቱ ተከፍቷል፡፡
የማኅበረ ቅዱሳን ሰብሳቢ ቀሲስ ዶ/ር ሰሙ ምትኩ የእንኳን ደኅና መጣችሁ መልእክታቸውን ለማስተላለፍ መድረኩን የተረከቡ ሲሆን በመልእክታቸውም ማኅበረ ቅዱሳን በኢትዮጵያ ጥንታዊ ገዳማት ላይ እየደረሰ ያለውን ልዩ ልዩ ችግሮች ለመታደግና የበኩሉን ድርሻ ለመወጣት ጥረቶችን በማድረግ ላይ እንደሚገኝ የገለጹ ሲሆን ገዳማትና የአብነት ትምህርት ቤቶች ያሉባቸውን ሁኔታ ለማጥናትና አግባብ ያለው መፈትሔ ለመስጠት መርሐ ግብር ነድፎ ተግባራዊ ሲያደርግ መቆየቱን ተናግረዋል፡፡
እስካሁን ከ100 በላይ ፕሮጀክቶች የተተገበሩና በመተግበር ላይ እንደሚገኙ የገለጹት ስብሰቢው በ145 አብነት ትምህርት ቤቶች ለ136 መምህንና ለ988 የአብነት ተማሪዎች ቋሚ ወርኀዊ የገንዘብ ድጋፍ ያደርጋል ብለዋል፡፡ ለገዳማት አበምኔቶችና እመምኔቶች ጥሪ የተደረገበትንም ምክንያት ሲገልጹ “ገዳማት ራሳቸውን እንዲችሉ በሚደረገው ጥረት ንቁ ተሳታፊ እንዲሆኑ ማስቻል፤ ገዳማት ከገዳማት ጋር ያላቸውን ትሥሥር ለማጠናከርና ወሳኝ አቅጣጫዎችን ለማስያዝ ከገዳማት አባቶች ጋር መመካከርና መወያያት አስፈላጊ ሆኖ በመገኘቱ ማኅበሩ ጥሪ አድርጓል” ብለዋል፡፡
ገዳማውያን አባቶችም ጥሪውን ተቀብለው አስቸጋሪውን ጉዞ ሁሉ ተቋቁመው በመገኘታቸው ምስጋናቸውን አቅርበዋል፡፡
በቀጣይነት የቀረበው በቀሲስ ዶ/ር ሙሉጌታ ስዮም ለሁለንታናዊ የቤተ ክርስቲያን እድገት የገዳማት ድርሻ በሚል ርእሰ ጉዳይ ላይ በመመርኮዝ “የገዳማት መጠናከር ለቤተ ክርስቲያን እድገት ያለው ሚና ምንድን ነው?” በሚል ጥናታቸውን አቅርበዋል፡፡ በጥናታቸውም ከዳሰሷቸው መካከል
-
ገዳማት የቤተ ክርስቲያናችን ሥውር ጓዳዎችና የምስጢር መዝገቦች ናቸው፡፡
-
ገዳማት የመማጸኛ ከተሞች ናቸው፡፡
-
ታላላቅ የቤተ ክርስቲያን ሊቃውንት የተገኙባቸው ምንጮች ናቸው
-
የተግባራዊ ክርስትና ሞዴሎች ናቸው
-
ገዳማውያን ለእግዚአብሔር የሚቀርቡ አሥራት በኩራት ናቸው፡፡
-
ገዳማት የብዝሃ ሕይወት መገኛና መጠበቂያ ናቸው፡፡
-
ለሁለንተናዊ የቤተ ክርስቲያን አገልግሎት መሠረት ናቸው
-
የማኅበራዊ ደኅንነት አገልግሎት መሥጫ ሥፍራዎች ናቸው፡፡
በማለት ሰፊ ትንታኔ በመስጠት ገዳማት ለቤተ ክርስቲያን እድገት አስፈላጊ መሆናቸውውን አብራርተዋል፡፡
በተያዘው መርሐ ግብር መሠረት በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ መምህር የሆኑት ፕሮፌሰር ሺፈራው በቀለ በኢትዮጽያ ገዳማት ላይ ያደረጉትን ጥናት አቅርበዋል፡፡ በጥናታቸውም ለኢትዮጵያ ሥልጣኔ ገዳማት ያላቸው ሚናና እነዚህንም የሥልጣኔ ምንጮቻችንን ጥበቃ ማድረግ እንደሚገባ ትኩረት ሰጥተው አብራርተዋል፡፡
በኢትዮጵያ ጥንታዊ ገዳማት ውስጥ ከ1500 በላይ ዘመናት ያስቆጠሩ የብራና መጻሕፍት መኖራቸውና በምሳሌነትም በአባ ገሪማ ገዳም የሚገኘውን የብራና ወንጌልን ጠቅሰዋል፡፡ በተጨማሪም በቤተ ክርስቲያን ውስጥ የሚገኙ ጥንታዊ ሥዕላትና ረጅም ዘመናትን ያስቆጠሩ ቤተ ክርስቲያናትና የአብነት ትምህርት ቤቶች ሳይፈርሱ በቅርስነት መያዝ እንደሚገባቸው ገልጸዋል፡፡
በጥናታቸው ማጠቃለያም “እነዚህ ቅርሶች የእኛ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን፤ የሁላችንም የኢትዮጵያውን /ሃይማኖታችን ምንም ቢሆን/፤ የመላው ጥቁር ሕዝቦች እንዲሁም የሰው ልጆችና የዓለማችን ቅርሶች ናቸው፡፡ ጥቁር ሕዝቦች እጅግ የረዘመ የሥእልና የኪነ ጥበብ ቅርስ የላቸውም የሥእልና የኪነ ጥበብ ቅርስ ያለው ሕዝብ እኛ ኢትዮጵያውያን ነን፡፡ እነዚህን ቅርሶች ያቆየችልን ደግሞ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ናት” ብለዋል፡፡
ጥናቱ እንደተጠናቀቀ ማኅበረ ቅዱሳን በገዳማት ውስጥ እያከናወናቸው ከሚገኙ ተግባራት መካከል ለምሳሌነት የቀረቡ ገዳማትን በመጥቀስ የባሌ መካነ ሕይወት አቡነ ተክለ ሃይማኖት ገዳም፣ የአቃቂ ደብረ ገነት አባ ሳሙኤል ቤተ ደናግል ገዳም፣ የምድረ ከብድ አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ገዳም አበምኔቶችና እመምኔት ከማኅበረ ቅዱሳን ጋር ያከናወኑትን ሥራ አቅርበዋል፡፡ በተጨማሪም በትግራይ ክልል የሚገኙትን ገዳማት በመከታተል ከፍተኛ አገልግሎት እያበረከተች የምትገኘው ጸጋ ኪሮስ ግርማይ ሪፖርት አቅርባለች፡፡
የባሌ መካነ ሕይወት አቡነ ተክለ ሃይማኖት ገዳም መጋቢ አባ ክንፈ ገብርኤል “ማኅበረ ቅዱሳን ወደ ገዳማችን በመምጣትና ችግራችንን በማየት ባጠናው ጥናት መሠረት የከብት እርባታ ለመጀመር የሚያስችለን ፕሮጀክት በመንደፍ 2 የወተት ላሞችን ሰጥቶን ሥራችንን ጀመርን፡፡ ዛሬ 24 ደርሰውልናል፡፡ 27 ደግሞ ሸጠን ተጠቅመናል፡፡ 18 ሞተውብናል፡፡ ተጨማሪ ሥራዎችንም በመሥራት ላይ እንገኛለን፡፡ ውጤታማም ሆነናል” ብለዋል፡፡
ከአቃቂ ደብረ ገነት አባ ሳሙኤል ቤተ ደናግል የገዳሙ እመ ምኔት እማሆይ መብዐ ጽዮን ማኅበሩ ስላደረገላቸው ድጋፍ ሲገልጹ “አንድ የልብስ ስፌት መኪና፤4 ጣቃ ጨርቅ እንዲሁም 2 ላሞችን ሰጥቶን ሥራችንን የጀመርን ሲሆን ዛሬ 10 የወተት ላሞች አድርሰናል” ብለዋል፡፡ በተጓዳኝም 10 ሕጻናትንም እያሳደጉ እንደሚገኙ ገልጸዋል፡፡
የማኅበረ ቅዱሳን የቅዱሳት መካናት ልማትና ማኅበራዊ አገልግሎት ዋና ክፍል ከገዳማት ጋር ባደረገው የተቀራረበ ሥራ ከ1992 ዓ.ም. ጀምሮ ከፍተኛ አፈጻጸም ላሳዩ ገዳማት የዋንጫ ሽልማት ማበርከቱ አንዱ የመርሐ ግብሩ አካል ነበር፡፡ ለሽልማት የበቁትም የባሌ መካነ ሕይወት አቡነ ተክለ ሃይማኖት ገዳም፣ የአቃቂ ደብረ ገነት አባ ሳሙኤል ቤተ ደናግል ገዳምና የደቡብ ጎንደር ገዳመ ኢየሱስ የተዘጋጀላቸውን ሽልማት ተቀብለዋል፡፡
በዐውደ ጥናቱ ላይ ከቀረቡት መርሐ ግብሮች መካከል የአባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ እና የአባ በጸሎተ ሚካኤል ገድል ምረቃ ሲሆን ከምረቃው በፊት በገድሉ ዙሪያ አጭር ትንታኔ በማኅበረ ቅዱሳን የኤሌክትሮኒክስና ሚዲያ የቴሌቪዥን ክፍል አስተባባሪ በዲያቆን ሄኖክ ኀይሌ ተሰጥቷል፡፡
የአባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ ገድል ለመተርጎም ከሦስት ዓመታት በላይ መውሰዱንና ገድሉን ሦስት ተርጓሚያን እንደተሳተፉበት፤ በ350፣000 ብር ለመታታመም እንደበቃ ተጠቅሷል፡፡በመጽሐፉ የሚገኘው ገቢም ሙሉ ለሙሉ ለአባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ ገዳም ሁለገብ ሕንፃ ግንባታ እንደሚውል ተገልጿል፡፡
በተጨማሪም ለገዳሙ ሁለገብ ሕንፃ ማሠሪያ ደራሲት ፀሐይ መላኩ “የንስሐ ሸንጎ” የተሰኘውን መጽሐፋቸው አበርክተዋል፡፡
ሁለቱንም መጻሕፍት ብፁዕ አቡነ ናትናኤል የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ዐቃቤ መንበር በመመረቅና በመባረክ የማኅበሩ ዋና ጸሐፊ ዲ/ን ሙሉጌታ ኃይለማርያም ተረክበዋል፡፡ ደራሲት ጸሐይ መላኩ “እመምኔት” የተሰኘው መጽሐፋቸው ለማኅበሩ ሕንፃ ግንባታ እንዲውል ከዚህ ቀደም ማበርከታቸው ይታወሳል፡፡
በዐውደ ጥናቱ ላይ ከተገኙት ተጋባዥ እንግዶች መካከል የቀድሞው የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ባለ አደራ ከንቲባ የነበሩት አቶ ብርሃነ ደሬሳ ሲሆኑ በዚህ መርሐ ግብር ላይ በመገኘታቸው መደሰታቸውን ገልጸው መልእክታቸውን አስተላልፈዋል፡፡
“ማኅበረ ቅዱሳን የሚመሰገንና ብዙ ቁም ነገር እየሠራ ያለ ማኅበረ ነው፡፡ አንድ ምክር ልለግሳችሁ፡፡ “ለነፍሳችሁ ብቻ ሳይሆን ለሰላምም መሥራት አለባችሁ፡፡ ሰላም ስትኖር ትረሳለች ሳትኖር ግን ታንገበግባለች፡፡ ማኅበሩ ለዚህ መቆም አለበት፡፡” ብለዋል፡፡
ገዳማትን አስመልክቶም ቅዱስ መጽሐፍ ኢትዮጵያ እጆቿን ወደ እግዚአብሔር ትዘረጋለች ይላል፡፡ የተዘረጉ የኢትዮጵያውያን እጆች የታጠፈበት ጊዜ ነበር እርሱም ደርግ እግዚአብሔር የለም ብሎ ቤተ ክርስቲያን ለመዝጋት በተነሣበት በ17ቱ ዓመት የቤተ ክርስቲያን የመከራ ወራት /ዘመን/ ነበር፡፡ በዚህን ጊዜም ቢሆን ያልታጠፉ ወደ እግዚአብሔር የተዘረጉ እጆች ነበሩ፡፡ እነዚህ እጆች የመነኮሳትና የመነኮሳይያት እጆች ናቸው፤ ለዚህ ያበቃን የገዳማውያኑ ጸሎት ነው፡፡ ስለዚህ መረዳት አለባቸው” ብለዋል፡፡ ለዚህም አገልግሎት ይረዳ ዘንድ 20 ሺህ ብር ለመሥጠት ቃል ገብተዋል፡፡
በመርሐ ግብሩ ላይ በክብር እንግድነት ከተገኙት መካከል በኢትዮጵያ የምሥራቅ አፍሪካ ፔፕሲ ኮላ ዋና ሥራ አስኪያጅ የሆኑት አቶ ደርቤ ሥነ ጊዮርጊስ ማኅበሩ ለገዳማት ለሚያከናውነው አገልግሎት 10 ሺህ ብር ለመሥጠት ቃል የገቡ ሲሆን “የኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን አጥታ አይደለም እንደዚህ የሚያስተባብርላት፣ ፕሮጀክት ቀርጾ አቅርቦ የሚፈጽም አካል ብቻ ነበር የጠፋው፡፡ እግዚአብሔር ይመስገን አሁን ማኅበረ ቅዱሳንን አስነሥቷል፡፡ የሚሠራውን ሥራ በተግባር ያየሁት በመሆኑ አብሬ እየሠራሁ ድጋፌን እቀጥላለሁ” ብለዋል፡፡
በመርሐ ግብሩ ማጠናቀቂያ ላይም በብፁዕ አቡነ ናትናኤል የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን መልካም ፈቃድ ብፁዕ አቡነ ጎርጎርዮስ የምሥራቅ ሸዋ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ቃለ ምዕዳን በመስጠት መልእክታቸውን አስተላልፈዋል፡፡ በሰጡት ቃለ ምዕዳንም “አባቶቻችን የገደሟቸውን ገዳማት ለእግረኞችም ሆነ ለፈረሰኞች አይመቹም፡፡ ከዛሬ 4ዐ ዓመት በፊት ከዋልድባ ተነሥተን የኢትዮጵያ ገዳማትን ሁኔታ ለማየት ተንቀሳቅሰን ነበር፡፡ ነገር ግን አልቻልንም፡፡ ዛሬ ባለቤት ያገኘ ይመስላል፡፡ ልጆቻችን እየወጡ እየወረዱ የተዘጉትን ገዳማት በማስከፈት እየተንቀሳቀሱ ነው፡፡ እግዚአብሔር እነዚህን ልጆቻችን ስለሰጠን እናመሰግነዋለን፡፡ ….የጉርምስና ጊዜ ለመንፈሳዊ ሥራ አይመችም፡፡ ይህንን ለመሥራት ከእግዚአብሔር መመረጥ፤ መታደል ያስፈልጋል፡፡ ልጆቻችን ከኑሮ ጋር እየታገሉ ጊዜያቸውን ለማኅበራችን እንስጥ በማለት ለቤተ ክርስቲያን መሥዋእት እየሆኑ ነው፡፡ እኔም ከማኅበሩ ጎን በመቆም እታዘዛለሁ፡፡ ብለዋል፡፡
ብፁዕ አቡነ ሉቃስ የሰቲት ሑመራ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስና በማኅበረ ቅዱሳን የጥናትና ምርምር ማእከል የአማካሪ ቦርድ ሰብሪሳቢ በሰጡት ቃለ ምእዳንም “ማኅበሩ ከገጠሪቱ ቤተ ክርስቲያን አንሥቶ የቤተ ክርስቲያናችን አእምሮና ልቡና እስከ ሆነው ገዳም ድረስ በመዝለቅ ከፍተኛ ሥራ እየሠሩ ነው፡፡ ገዳማት የምስጢር፣ የዜማ፤ የመጻሕፍት፤ የሊቃውንት፣ የካህናት መገኛ ናቸው፡፡ ልጆቻችን የሚሠሩት ሥራ እስከዚያ ዘልቋል፡፡ እግዚአብሔር ያስተማረው ሰው የእግዚብሔርን ሥራ ይሠራል፡፡ የእግዚአብሔርን ንብረት ይጠብቃል፡፡ ልጆቻችን ከእግዚአብሔር የተማሩት እየሠሩበት ነው፡፡ ከጎናቸው እንቁም፡፡ እኛም ከማኅበሩ ጎን ቆመን እንሠራለን፣ እንላላካለን፣ እንልካለንም፡፡” ብለዋል፡፡
በመጨረሻም አቡነ ናትናኤል የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ዐቃቤ መንበርና የአርሲ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ በሰጡት ቃለምዕዳንና ቡራኬ “ያሰባችሁት ሁሉ መልካም ነገር ነውና ያሰባችሁትን ሁሉ እንድትሠሩ እግዚአብሔር ይርዳችሁ፡፡ ማኅበሩን ያስፋልን ማኅበሩን ከስም አወጣጥ ጀምሮ እኛ የሰጠነው በመሆኑ አብረን እንሠራለን ብለዋል፡፡
በመርሐ ግብሩ ላይ ብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳት ሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያን፣ የገዳማት አበምኔቶችና እመምኔተች ካህናት የዩኒቨርሲቲ ምሁራንና ምእመናን ተገኝተዋል፡፡






ማእዱን እንደተመገቡ የማኅበረ ቅዱሳን ሰብሳቢ ቀሲስ ዶክተር ሰሙ ምትኩ የእንኳን ደህና መጣችሁ መልእክት ለማስተላለፍ ቅድሚያውን ወሰዱ፡፡ “የቤተ ክርስቲያን መሠረቷ ገዳማት ናቸው፡፡ ቤተ ክርስቲያን ጠነከረች የሚባለውም የገዳማት ጥንካሬ የሚያመጣው ነውና በዚህ ሁኔታ ላይ እንድንወያይ፤ ነገ ምን ማድረግ እንደሚገባን እንድንነጋገር፤ እኛም የምናስበውን ለማሳየት እንድንችል እንድትመክሩን፤ እንድተጸልዩልን ነው የተሰባሰብነው፡፡ እናንተን ለማየት በመታደላችን እጅግ ደስተኞች ነን፡፡ ቀሪውን ጊዜም መልካም ነገር የምናቅድበትና የምንፈጽምበት እንዲሆን እንመኛለን” ያሉ ሲሆን ደጆችሽ አይዘጉ መንፈሳዊ የአገልግሎት ማኅበር ላከናወነው አርአያነት ያለው ተግባር ምስጋናቸውን አቅርበዋል፡፡
ቢሰማቸው የማኅበሩ አባላት የሆኑ የሕክምና ዶክተሮችና ነርሶች 24 ሰዓት እነሱን ለማገልገል መመደባቸው ተገለጸላቸው፡፡ እንዲሁም ማንኛውንም አገልግሎት ቢፈልጉ እነሱን ለማገልገል የተመደቡ ወንድሞችና እኅቶች ስለሚገኙ የሚሹትን ነገር ሳይሰቀቁ እንዲጠይቁ በማሳሰብ የምሽቱ መርሐ ግብር በአባቶች ቡራኬ ተጠናቋል፡፡
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ተልእኮ ለማሳካት የገዳማት ድርሻ በሚል መሪ ቃል የተዘጋጀ አውደ ጥናት ታህሣሥ 6 ቀን 2005 ዓ.ም. ከቀኑ 7፡00 ሠዓት ጀምሮ 6 ኪሎ በሚገኘው በኢትዮጵያ ስብሰባ ማእከል ከሃምሳ በላይ የሚደርሱ ከታላላቅ ገዳማት የተውጣጡ አበምኔቶች በተገኙበት እንደሚካሄድ በማኅበረ ቅዱሳን የቅዱሳት መካናት ልማትና ማኅበራዊ አገልግሎት ዋና ክፍል ዳይሬክተር ዲያቆን አእምሮ ይሔይስ ገለጹ፡፡
በማኅበረ ቅዱሳን የስብከተ ወንጌል ማስፋፊያ ፕሮግራም አስተባበሪነት፤ በደቡብ ኦሞ ሀገረ ስብከት ሥር የሚገኙና በልዩ ልዩ ቤተ እምነቶች ውስጥ የነበሩ ከሰባት መቶ በላይ ኢትዮጵያውያን ሥርዓተ ጥምቀት ተፈጽሞላቸው ወደ እናት ቤተ ክርስቲያን ተመለሱ፡፡ በሜጸር የቅዱስ ሚካኤል እንዲሁም በቶልታ የቅድስት ሥላሴ አብያተ ክርስቲያናት ውስጥ ኅዳር 23 ቀን 2005 ዓ.ም. በተከናወነው ሥርዓተ ጥምቀት ሀብተ ወልድና ስመ ክርስትና ያገኙ ሰዎች በማኅበረ ቅዱሳን የጂንካ ማእከልና በሰንበት ትምህርት ቤት ጥምረት በሁለት ልዩ ልዩ የስብከት ኬላዎች አማካኝነት ሥርዓተ ቤተ ክርስቲያን ሲማሩ የቆዩ ናቸው፡፡
አዳዲስ ተጠማቂያኑ ለዝግጅት ክፍላችን በሰጡት አተያየት ፡ በተፈጸመላቸው ሥርዓት ጥምቀት እጅግ በጣም መደሰታቸውን ገልጸው፤ በአቅራቢያቸው ቤተ ክርስቲያን እንዲታነፅላቸው ጥያቄ አቅርበዋል፡፡ በጉዳዩ ላይ ያነጋገርናቸው ብፁዕ አቡነ ኤልያስ የደቡብ ኦሞ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስና የቅዱስ ሲኖዶስ አባል “የምእመናኑ ጥያቄ ተገቢ ነው፡፡ አብያተ ክርስቲያናቱ ሲቋቋሙ አብሮ መተዳደሪቸውም ሊታሰብ ይገባዋል፤ በአንዳንድ ቦታዎች ላይ እንዳስተዋልነው ምእመናን በቅንነት በዚህ ቦታ እንዲህ ያለ ታቦት ይተከልልን እኛ ሙሉ ወጪውን እንሸፍናለን በማለት ያሳነፅዋቸው አብያተ ክርስቲያናት ምእመናኑ በሕይወት እስካሉ ድረስ ያገለግሏቸውና፤ እነሱ ከዚህ ዓለም በሞተ ሥጋ ሲለዩ አገልግሎቱ እየተቋረጠ አብያተ ክርስቲያናቱ እስከ መዘጋት የደረሱባቸው ሁኔታዎች አሉ፡፡ ስለሆነም ቤተ ክርስቲያኗ እንዴት ትገለገላለች? በሚለው ላይ ማኅበረ ቅዱሳንን ጨምሮ በመላው ዓለም የሚገኙ የቤተ ክርስቲኒቱ ልጆች ሊያስቡበት ይገባል፡፡ አብያተ ክርስቲያናትም ሁል ጊዜ በልመና መተዳደር የለባቸውም” ብለዋል፡፡
የስብከተ ወንጌል ማስፋፊያው በቶልታና ሜጠር ቀበሌዎች ላስጠመቃቸው አዳዲስ ምእመናን በቀጣይ ለሚፈጽምላቸው እገዛ አስመልክተው ሊቀ ብርሃናት ሃማኖት ተስፋዬ እንዲህ ብለዋል፡፡ “የልጅነት ጥምቀት አግኝተው በቅርቡ ወደ ቅድስት ቤተ ክርስቲያን ለገቡ ምእመናን በአቅራቢያቸው ሥርዓተ አምልኮ የሚፈጽሙባቸውን አብያተ ክርስቲያናትን ማነፅና እነሱንም ማጽናት ይጠበቅብናል፡፡”
በማኅበረ ቅዱሳን የአዲስ አበባ ማዕከል ሥራ አሥፈጻሚ አባላትን ያቀፈ የልዑካን ቡድን በበኬ ደብረ ምሕረት ቅድስት ማርያም ቤተ ክርስቲያን እየተከናወነ የሚገኘውን የልማት ሥራ ለመመልከትና ከደብሩ አስተዳደር አካላት ጋር ለመወያየት ኅዳር 23 ቀን 2005 ዓ.ም. ጉብኝት አካሄደ፡፡
መሠረት በባለሙያ አስጠንቶ ዘመናዊ የግብርና ኤክስቴንሽን መርሐ ግብሮች ተግባራዊ ለማድረግ ጥረት ሲያደርግ ቆይቷል፡፡ በተያዘው እቅድ መሠረት እሰካሁን ከተከናወኑት ውስጥ ደግሞ የቤተ ክርስቲያኑ ይዞታ በሆነው 3 ሄክታር መሬት ላይ የተዘራው የጤፍ እርሻ የሚገኝበትን መቃኘት የመጀመሪያው የጉብኝቱ አካል ነበር፡፡
“የግብርና ኤክስቴንሽን መርሐ ግብሮችን ለመጠቀም ጥረት አድርገናል፡፡ ለማስተማር የፈለግነው የአካባቢው አርሶ አደሮችና ምእመናን ከቤተ ክርስቲያን በጎ ተሞክሮዎችን እንዲወስዱ ለማድረግ ነው፡፡ በበሬ ብቻ ሳይሆን በትራክተር እንዲታረስም አድርገናል፡፡ ከ3 ሄክታር መሬቱ ላይ ከ250 እሰከ 300 ካሬ ሜትሩ ለሙከራ ምርጥ ዘር ተጠቅመናል፡፡ የትኛው የተሻለ እንደሆነ ለሁሉም ለማሳየት የቻልንበት ነው፡፡ ገና ሳይታጨድ ልዩነቱም ጎልቶ ይታያል፡፡ በሚቀጥለው አመትም ጤፍ በመሥመር መዝራትን ተግባራዊ የምናደርግበት ሁኔታ እናመቻቻለን፡፡ ይህንን የምናደርገው ምእመናን የቤተ ክርስቲያናችንን ተሞክሮ ተመልክተው እነሱም እንዲጠቀሙበት ለማስተማር ነው፡፡” በማለት ወይዘሪት መቅደስ አለሙ በአዲስ አበባ ማእከል የማኅበራዊ አገልግሎትና ልማት ክፍል ሰብሳቢ በጉብኝቱ ላይ ገልጸዋል፡፡
የተዘጋጁ ናቸው፤ የሳር ፍራሽና ካርቱን አንጥፈውበታል፡፡ አንዱን ከአንዱ ለመለየት በማዳበሪያ ተከፋፍሏል፤ በአንዱ አዳራሽ ውስጥ አዳራቸውን የሚያደርጉት ተማሪዎች ብዛት ከአንድ መቶ ይበልጣል፡፡ አዳራሹ ውስጥ እሳት ቢነሣ ወይም በሽታ ቢገባ የሚተርፍ ያለ አይመስልም፡፡ አንድ የማብሰያ ክፍል ሲኖር ሁሉንም ማስተናገድ ስለማይችል የተወሰኑት ተማሪዎች ውጪ ሜዳው ላይ ምግባቸውን ለማብሰል ይገደዳሉ፡፡

የማኅበረ ቅዱሳን ዋና ጸሐፊ ዲያቆን ሙሉጌታ ኃይለ ማርያም የወርቅ ሜዳልያውን በተረከቡበት ወቅት ባስተላለፉት መልዕክት “የማኅበረ ቅዱሳን አባላት በግቢ ጉባኤያት ቆይታቸው በትምህርታቸው ከፍተኛ ውጤት በማስመዝገብ የተሸለሙትን ሜዳልያ ለማኅበሩ ሲያበረክቱ ይህ ለሁለተኛ ጊዜ ነው፡፡
ያዘጋጀው የውይይት መድረክ ኅዳር 22 ቀን 2005 ዓ.ም. ከቀኑ 8፡00 ስዓት ላይ በማኅበሩ ሕንፃ ላይ ተካሄደ፡፡
የውይይት መድረኩ በአቶ ወንድወሰን አዳነ በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ የኢትዮጵያ ቋንቋዎች ሥነ ጽሑፍ ትምህርት ክፍል መምህር የተመራ ሲሆን ዲያቆን ያረጋል አበጋዝ ለውይይት መድረኩ መነሻ የሚሆን ጥናታዊ ጽሑፋቸውን አቅርበዋል፡፡ ባቀረቡት ጽሑፍም “ሥነ ፍጥረት የሚነበብ መጽሐፍ ነው፡፡ መጽሐፍ እግዚአብሔር በመጀመሪያ ለፍጥረቱ የሰጠው ትልቁ ሥጦታ ነው፡፡” በማለት የጥናት ጽሑፋቸውን በመጀመር በመጽሐፍ ቅዱስ ስለ መጻሕፍት የተነገሩትን ጠቅሰዋል፡፡ ከእነዚህም መካከል” በእግዚአብሔር ቃል ሰማዮች ፀኑ፤ ሠራዊታቸውም ሁሉ በአፉ እስትንፋስ የባሕርን ውኃ እንደ ረዋት የሚሰበስብ ቀላዮችንም በመዝገቦች የሚያኖራቸው” መዝ.86፤6 “በእግዚአብሔር መጽሐፍ ፈልጉ አንብቡም አፌ አዟልና” (ኢሳይያስ 34፤16) በማለት ጠቅሰዋል፡፡ በተጨማሪም ከቅዱሳን አበው መካከል “ቅዱሳት መጻሕፍትን አለማወቅ የስህተት ሁሉ ምንጭ ነው” በማለት ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ ከተናገረው በመነሣት የቅዱሳት መጻሕፍት ጠቀሜታን አብራርተዋል፡፡
ጥናቱ ከቀረበ በኋላም በንባብ ባሕል ላይ ያተኮረ ውይይት የተካሄደ ሲሆን ሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያን፤ የዩኒቨርስቲ ምሁራንና ተማሪዎች እንዲሁም ተሳታፊዎች አስተያየቶቻቸውንና የመፍትሔ አሳቦቻቸውን አቅርበዋል፡፡ በአብዛኛው ከተጠቀሱት ውስጥም የንባብ ባሕላችንን ለማሳደግ በዋነኛነት ቤተሰብና ትምህርት ቤቶች ከፍተኛ ሓላፊነት እንዳለባቸው ፤ ልጆች ከሕፃንነት ጀምሮ ንባብን ባሕል አድርገው እንዲያድጉ ከፍተኛ ሥራ መሠራት እንደሚገባው አመላክተዋል፡፡
የአሰቦት ደብረ ወገግ ቅድሥት ሥላሴና አቡነ ሳሙኤል ገዳም 6 ኪሎ ሜትር የተራራው መውጫ መንገድ በሁለት በጎ አድራጊ ወጣቶች ሙሉ ወጪውን በመሸፈን የጥርጊያ መንገዱን ሥራ ከመስከረም 7 ቀን 2005 ዓ.ም. ጀምሮ በ17 ቀናት ውስጥ በመሥራት ተጠናቀቀ፡፡
ሥራውን ለመሥራት በገዳሙ በቆዩባቸው ጊዜያት ያስተዋሉትን ሲገልጹም “የገዳማውያኑ ስሜት ልዩ ነው፡፡ የገዳማውያን አባቶችና እናቶች ደስታ ተመልክተናል፡፤ እንኳን እነሱ ለዘመናት የተቸገሩት ቀርቶ እኛም የተሰማን ስሜት መግለጽ ከምንችለው በላይ ነው፡፡ ደስታቸው አስደስቶናል፡፡ ሰዎች ለእግዚአብሔር በሰጡ ቁጥር የሚጎድልባቸው የሚመስላቸው አሉ፡፡ ነገር ግን እግዚአብሔር የተሻለ ነገር እንደሚሰጣቸው ማመን አለባቸው፡፡ ለእግዚአብሔር መስጠት አያጎድልም ይጨምራል እንጂ፡፡ የእኛን ደስታ ሌሎችም እንዲጋሩት እንፈልጋለን፡፡ ያደረግነው ነገር ትንሽ ቢሆንም ከእግዚአብሔር ጋር ከሆንክ ትረካለህ፡፡ ወደፊትም አቅማችን እያዳበርን ሌሎች ገዳማትን የመርዳት እቅድ አለን፡፡” በማለት ሁለቱ በጎ አድራጊ ወጣቶች ተናግረዋል፡፡