ሌሎች መካነ ድሮች
ቅድስት ሥላሴ መንፈሳዊ ኮሌጅ አዲስ አበባ
ማኅበረ ቅዱሳን አሜሪካ ማዕከል
ማኅበረ ቅዱሳን ድምጸ-ተዋህዶ(አሜሪካ)
ማኅበረ ቅዱሳን አውሮፓ ማዕከል
ማኅበረ ቅዱሳን አውሮፓ ማዕከል ፓልቶክ
የግብፅ ኦርቶዶክስ ቤተ-ክርስቲያን
የግብፅ ኦርቶዶክስ ቤተ-ክርስቲያን መጽሐፍት 1
የግብፅ ኦርቶዶክስ ቤተ-ክርስቲያን መጽሐፍ
Normal 0 false false false EN-US X-NONE TH MicrosoftInternetExplorer4
የወርቃማው ዘመን ወርቃማ ደራሲ ሊቁ አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ
መጋቢት 12 ቀን ከሰዓት በኋላ 6 ኪሎ በሚገኘው የኢትዮጵያ ስብሰባ ማዕከል፡፡
ሀብዎሙ ዘይቤልዑ
የሚበሉትን ስጡአቸው(ክፍል አንድ)
ማቴ. 14.16
ለዘሪ ዘርን ለመብላትም እንጀራን በብዙ የሚሰጥ እርሱ የምድርን ፍሬ አንዲቷን ቅንጣት በመቶ፣ በሺሕ አብዝቶ የፈጠረውን ፍጥረት ዓለም ከተፈጠረ ዘመን ከተቆጠረ ጀምሮ ሳያቋርጥ ከትንኝ እስከ ዝሆን ከሰው እስከ እንስሳ ያለውን እርሱ ባወቀ መመገብ የሚገባውን ሁሉ የሚመግብ አምላክ ነው፡፡
ይቆየን፡፡
በዓለማችን የመጀመሪያ የሆነው የአባ እንጦንስ ገዳም በዐሥራ አራት ሚሊዮን ዶላር እድሳት ተደረገለት
ገዳሙ አንድ ሺሕ ስድስት መቶ ዓመታትን አስቆጥሯል
በሻምበል ጥላሁን
በዓለም የመጀመሪያው የምንኩስናና የገዳማውያን ኑሮ መሥራች የሆነው የአባ እንጦንስ ገዳም በግብፅ መንግሥት በዐሥራ አራት ሚሊዮን ዶላር ወጪ እድሳት ተደርጎለት ለአገልግሎት መዘጋጀቱን ቢቢሲ የካቲት 4 ቀን 2002 ዓ.ም ዘገበ፡፡ በግብፅ የሚገኘው የቅዱስ እንጦንስ ገዳም ከአንድ ሺሕ ስድስት መቶ ዓመት በላይ ዕድሜ ያለው ጥንታዊ ገዳም ነው፡፡
በግብፅ የሚገኘው የአባ እንጦንስ ገዳም
ገዳሙ ከዕድሜ ብዛት በእርጅና ከደረሰበት ጉዳት ተጠግኖ ለቱሪስት ኢንዱስትሪው ተጨማሪ አቅም እንዲፈጥር የግብፅ መንግሥት ከዐሥራ አራት ሚሊዮን ዶላር በላይ ወጪ እንዳደረገ ዘገባው ጠቁሞ፤ ገዳሙ መንፈሳዊ እሴቱና ታሪካዊ ዳራው እንዳይጠፋ ለማደስ ከስምንት ዓመት በላይ እንደፈጀም የዜና ምንጩ አስታውቋል፡፡
የቢቢሲ ዘገባ እንዳመለከተው፤ የገዳሙ መታደስ የሀገሪቱን የቱሪስት ኢንዱስትሪ ከማስፋፋቱም በላይ ከፍተኛ የኢኮኖሚ አቅም ለመገንባትም እንደሚያስችል አመልክቷል፡፡
በግብፅ ስዊዝ ከተማ የሚገኘው የአባ እንጦንስ ገዳም መታደስ፣ አገልግሎት ላይ መዋልና ለቱሪስት መስህብነት ክፍት መሆኑ፤ ሀገሪቱ የቀድሞ ታሪኳንና ቅርሷን ለመጠበቅ የምታደርገውን ጥረት እንደሚያሳይ ዛሒ ሐዋስ የተባሉት የግብፅ ዋና የቅሪተ አካል ተመራማሪ መናገራቸውንም የዜና ምንጩ አስታውቋል፡፡
ገዳሙ ቅዱስ እንጦንስ በሦስተኛው መቶ ከፍለ ዘመን በቀይ ባሕር አካባቢ በሚገኘው ተራራማና በረሐማ አካባቢ ለጸሎት የመነኑበት ቦታ ነው፡፡
በመልሶ ግንባታው ወቅት በገዳሙ የሚኙት ሁለት አብያተ ክርስቲያናትና ሁለት ማማዎች በጥንቃቄ መንፈሳዊና ታሪካዊ ይዘታቸው ሳይቀየር መሠራታቸውን ዘገባው አመልክቷል፡፡
የቅዱስ እንጦንስ ገዳም በግብፅ ኦርቶዶክሶችም ሆነ በአምስቱ ኦሪየንታል አኀት አብያተ ክርስቲያናት ዘንድ ታዋቂ ነው፡፡
በገና እንደርድር
በሰንበት ት/ቤቶች ማደራጃ መመሪያ ማኅበረ ቅዱሳን የተቋቋመው የአቡነ ጎርጎርዮስ ትምህርት ቤት በአብነት ትምህርትና በዜማ መሣሪያዎች እያሠለጠነ ማስመረቅ ከጀመረ ዓመታት ተቆጥረዋል፡፡ እንደ ት/ቤቱ ሥራ አስኪያጅ አቶ አዲስ ተፈራ ገለጻ የዛሬውን ጨምሮ አሥራ አራት ዙር አሠልጥኖ አስመርቋል፡፡
ሥራ አስኪያጁ የአብነት ትምህርትና የዜማ መሣሪያዎች ሥልጠና እሴቶቹን ከመጠበቅ ባሻገር የሚያስገኙትን መንፈሳዊና ማኅበራዊ ጠቀሜታዎች ሲዘረዝሩ «ለምስጋና፣ ለተመስጦ፣ ጭንቀትንና ርኩስ መንፈስን ለማራቅ፣ ለትምህርት፣ እንዲሁም የሀገርን ቅርስ ከነሙሉ ታሪኩና ጥቅሙ ለማስተዋወቅ፣ ትውፊትን ለትውልድ ለማውረስና በገና ከነበረው ጥቅም አንጻር ቀጣይ አገልግሎት እንዲኖረው ማድረግ ይቆይ የማይባል አገልግሎት ነው፡፡» ይላሉ፡፡
ወጣት ሚልካ ሐጎስ በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ የአምስት ኪሎ ኢንጂነሪንግ የ4ኛ ዓመት ተማሪ ናት፡፡ ከትምህርቷ በተጓዳኝ ትምህርተ ቤተ ክርስቲያን የምትከታተል የግቢ ጉባኤ ተማሪ ናት፡፡ በዚህ ሁሉ የጊዜ ጥበት ግን በአቡነ ጎርጎርዮስ ት/ቤት የሚሰጠውን የዜማ መሣሪያ ሥልጠና ወስዳ በበገና መደርደር ተመርቃለች፡፡ ሚልካ ጊዜዋን አጣጥማ በሳምንት ሁለት ቀን ለሁለት ሰዓት ተከታትላ በስድስት ወር ያጠናቀቀችውን ሥልጠና እንዴት ትገልጠዋለች)
«ጊዜአችንን በአግባቡ የምንጠቀም ከሆነ ሕልምን እውን ማድረግ እንችላለን፡፡ ጊዜዬን ተጠቅሜ በገና ተምሬአለው፡፡ ይህ ለእኔ መንፈሳዊ ሕይወት እጅግ አጋዤ ነው፡፡ ጊዜ መድቤ ደግሞ የአብነት ትምህርቱንና ተጨማሪ የዜማ መሣሪያዎችን ለመማር አስባለሁ፡፡ እድሜዬን ሁሉ አገልጋይ ሆንኩ ማለት አይደል፡፡ በእውነት በገና መደርደር መታደል ነው፡፡» ብላለች፡፡ ማኅበረ ቅዱሳንም ትምህርት ቤቱን ከፍቶ ኑና በገና እንደርድር ይላል፡፡
ከጋምቤላ ክልል የመጡ ሠልጣኞች ተመረቁ
ላሬ፣ ኝንኛንግ፣ ፒኝዶ፣ አበቦ፣ ጆር፣ ኢታንግ እና ጋምቤላ ዙሪያ ከሚባሉ ሰባት ወረዳዎች የመጡት ሠልጣኞች በቁጥር ዐሥራ ስድስት ሲሆኑ ሥልጠናው ዐሥራ አምስት ቀን እንደወሰደ ሓላፊው ተናግረዋል፡፡
ሥልጠናውን ለመሥጠት ከሰላሳ አምስት ሺሕ ብር በላይ ወጪ እንዳስፈለገ የጠቀሱት ሓላፊው ወደፊትም በሀገር ውስጥም ሆነ በውጭ የሚገኙ በጎ አድራጊዎች ይህንን መሰል መንፈሳዊ አገልግሎት ለማከናወን የእርዳታ እጃቸውን ከዘረጉ በርካታ የጠረፋማ አካባቢ ወገኖችን ለማስተማር እንደሚቻል አስረድተዋል፡፡
በአፍ መፍቻ ቋንቋ ተምሮ ማስተማር ውጤቱ ከፍተኛ በመሆኑም የክርስትናው እምነት ባልተዳረሰባቸው አካባቢዎች በቋንቋቸው በማስተማር ልንደርስላቸው ይገባል ብለዋል፡፡
ሠልጣኞቹ ሥነፍጥረት፣ ትምህርተ ሃይማኖት፣ የቤተክርስቲያን ታሪክ፣ ነገረ ቅዱሳን፣ የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናት፣ ሥርዓተ ቤተክርስቲያንና የስብከት ዘዴ በሚሉ ርእሶች ትምህርት እንደተሰጣቸው እና ወደ ክልላቸው ሔደው ምን መሥራት እንደሚገባቸው ምክክር እንደተደረገም ለማወቅ ተችሏል፡፡
ለገዳሙ ካህናትና ዲያቆናት መሠረታዊ የኮምፒውተር አጠቃቀም ሥልጠና ተሰጣቸው
የሰንበት ትምህርት ቤቱ ምክትል ሰብሳቢ ዲያቆን ደረጀ ነጋሽ በበኩሉ፤ የመጀመሪያውን ዙር መሠረታዊ የኮምፒዩተር ሥልጠና ሠልጥነው ያጠናቀቁት፤ አንድ መነኩሴ፣ አሥራ ሦስት ዲያቆናትና አንዲት የሰንበት ትምህርት ቤት አባል ወጣት እንደሆኑ አስረድቷል፡፡ በሥልጠናው ወቅት ያገኙትም የትምህርት ዓይነት ኤም ኤስ ዊንዶ፣ ወርድ፣ ኤክሴል፣ አክሰስና የኢንተርኔት አጠቃቀም የተመለከቱ መሆናቸውን ሰብሳቢው ጠቁሞ፣ ሥልጠናው አገልግሎታቸውን ለማቀላጠፍ እንደሚረዳ አስታውቋል፡፡
ሥልጠናውን ለስምንት ወራት የሰጡት ቀደም ሲል በሰንበት ትምህርት ቤቱ ተኮትኩተው ያደጉ ወጣቶች ሲሆኑ፤ አሠልጣኞች በአሁኑ ጊዜ በኮምፒዩተር ሳይንስ ሙያ በተለያዩ ተቋማት የሚያስተምሩ አባላት እንደሆኑ ምክትል ሰብሳቢው አስረድቷል፡፡ ለወደፊትም ሥልጠናውን ከገዳሙም በተጨማሪ ወደ ሌሎችም አጥቢያ አብያተ ክርስቲያናት በመሔድ ለአገልግሎትና ለሰንበት ትምህርት ቤት ወጣቶች ለመስጠት እቅድ መያዙን ተናግሯል፡፡
በምረቃ ሥነ ሥርዓቱ ላይ ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች የተገኙ ሲሆን በተለይ ቀደም ብሎ የሰንበት ትምህርት ቤቱ አባል የነበሩ አባቶች በሰጡት አስተያየት አባትና ልጅ በአንድ ሆነው መማራቸው በሰንበት ትምህርት ቤቱና በገዳሙ አባቶች መካከል ያለውን ፍቅርና አንድነት እንደሚያሳይ ገልጸዋል፡፡ሥራውም ለሌሎች ሰንበት ት/ቤት አርአያ እንደሚሆንም ተናግረዋል፡፡ ሰንበት ት/ቤቱ ከ1950 ዓ. ም. ጀምሮ እስከ 1993 ዓ. ም. ድረስ «ተምሮ ማስተማር ማኅበር» የሚል ስያሜን ይዞ ቤተ ክርስቲያንን እያገለገለ ነበር፡፡ ከ1993 ዓ. ም. ወዲህ «የተምሮ ማስተማር ሰንበት ት/ቤት» በሚል ስያሜ አገልግሎት እየሰጠ ይገኛል፡፡
ለሕንፃ ቤተ ክርስቲያን ሥራ ድጋፍ ተጠየቀ
የአዲሱን ሕንፃ ቤተ ክርስቲያን ዲዛይን ማኅበረ ቅዱሳን ሠርቶ ለኮሚቴው ያስረከበ መሆኑን የጠቀሱት ሰብሳቢው፤ ሥራውን ለመጀመር በሚደረገው ጥረት በሀገር ውስጥና ውጪ ያሉ ምእመናን እንዲሁም በጎ አድራጊ ድርጅቶችና ማኅበራት ድጋፍ እንዲያደርጉ ጠይቀዋል፡፡ በባንክ መላክ የሚፈልጉም በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ዲላ ቅርንጫፍ የባንክ ሒሳብ ቁጥር 15664 እንዲጠቀሙም ገልፀዋል፡፡
የቤተ ክርስቲያኑ አስተዳዳሪ መልአከ ገነት ተሾመ ወሰን በበኩላቸው፤ ሰበካ ጉባኤው፣ ሕንፃ አሠሪ ኮሚቴውና የወረዳው ቤተ ክህነት ከሕዝቡ ጋር በመተባበር ሕንፃ ቤተ ክርስቲያን ለማሠራት በብርቱ እንቅስቀሴ ላይ ናቸው፡፡ ሕንፃ ቤተ ክርስቲያን ለማሠራት የአካባቢው ሕዝብ አቅም ባይኖረውም ተሠርቶ የማየት ከፍተኛ ጉጉት እንዳለው አስተዳዳሪው ጠቅሰው በእስካሁኑ ሂደት ጥሩ ትብብር እያደረገ መሆኑን ተናግረዋል፡፡
በዚሁ በዓለ ንግሥ ዕለት ምእመናኑ ሃያ ሰባት ሺሕ ብር ድጋፍ ማድረጉ ታውቋል፡፡
ማኅበሩ የንብ እርባታ ፕሮጀክቱን አስረከበ
በማኅበሩ የመቀሌ ማእከል ጸሐፊ የማን ኃይሉ በዚሁ የርክክብ ሥነ ሥርዓት ላይ እንዳሉት፤ የገዳሙ መነኮሳትን ችግር ለማቃለል ማኅበረ ቅዱሳን ከ2000 ዓ.ም ጀምሮ የፕሮጀክት ጥናት በማካሄደ በ36ሺ 450 ብር ወጪ የንብ እርባታ አጠናቆ ለገዳሙ ማስረከብ ችሏል፡፡
ከቅዱስ ሲኖዶስ ከተሰጠው ሓላፊነቶች አንዱ ገዳማት አድባራትና የአብነት ት/ቤቶች በገቢ እራሳቸውን እንዲችሉ ማገዝ መሆኑን የጠቆሙት ጸሐፊው ወደፊትም ይህን ተግባሩን አጠናክሮ ይቀጥላል ብለዋል፡፡
ግብርናና ገጠር ልማት ጽ/ቤት ተወካይ አቶ ግደይ መለስ በዚሁ ወቅት ባስተላለፉት መልእክት፤ የገዳሙን ቅርስና ሀብት ለቀጣዩ ትውልድ ለማስተላለፍ በሚደረገው ጥረት ለገዳማውያኑ ጥሬ ገንዘብ እየሰጡ ተመፅዋች ከማድረግ ይልቅ እንደ ማኅበረ ቅዱሳን እራስን የሚያስችል ፕሮጀክት ማከናወን ውጤታማ ያደርጋል ብለዋል፡፡ ለፕሮጀክቱ ውጤታማነት ጽ/ቤቱ አስፈላጊውን ድጋፍ እንደሚያደርግም ቃል ገብተዋል፡፡
አበእምኔት መ/ር አባ ገ/ማሪያም ግደይ በበኩላቸው፤ «ገዳሙ ተዳክሞ መነኮሳቱም በችግር ምክንያት ፈልሰው ወደ መዘጋት በተቃረበበት ወቅት ማኅበሩ ደርሶ ለገዳሙ ፀሐይ አወጣለት» ሲሉ በገዳማውያኑ ስም ምስጋናቸውን አቅርበዋል፡፡
በቀጣይ ሊገጥመው የሚችለውን ችግሮች እየተከታተለ ይፈታ ዘንድ የተማፅንኦ ቃል ያሰሙት አበ ምኔቱ ለፕሮጀክቱ ውጤታማነት መነኮሳቱ ተግተው እንደሚሠሩም ተናግረዋል፡፡
በርክክቡ ወቅት የተገኙት የቆላ ተንቤን ወረዳ ቤተ ክህነት ሥራ አስኪያጅ መ/ር አባ እዝራ ሃይሉ ማኅበሩ በቤተ ክርስቲያን ውስጥ ሆኖ እያከናወነ ያለው ዘርፈ ብዙ አገልግሎት የሚያስመሰግነው መሆኑን ጠቅሰው መንገዱ እጅግ አድካሚና አስቸጋሪ በሆነ ቦታ መጥቶ ከጥናት ጀምሮ እስከ ትግበራ ያከናወነው ፕሮጀክት ለሌሎች አርአያ ለመሆን የሚያስችለው ነው፡፡
ማኅበሩ የሠራውን ፕሮጀክት ተንከባክበው ውጤታማ በማድረግ ሥርዓተ ገዳማቸውን እንዲያፀኑ አሳስበዋል፡፡ በሠራው የተባበሩትን ሁሉ አመስግነዋል፡፡
ጥር 4 ቀን 2002 ዓ. ም ማኅበሩ ፕሮጀክቱን ለገዳሙ ባስረከበበት ወቅት እንደተገለፀው በሀገራችን ካሉት ቀደምት ገዳማት አንዱ መሆኑ የሚነገርለት ይኸው ገዳም በጣሊያን ወረራ ወቅት ከፍተኛ ጉዳት የደረሰበት ከመሆኑ በተ ጨማሪ ከ1966 ዓ.ም. ለውጥ በኋላ የገዳሙ ይዞታ ሙሉ በሙሉ በመወረሱ ገዳሙ ከፍተኛ ችግር ውስጥ ነበር፡፡
ፕሮጀክት ድጋፍ እንዲውል የማኅበረ ረድኤት ትግራይ ከሃያ ስድስት ሺሕ ብር በላይ ግምት ያለው የማር ማጣሪያ ዘመናዊ ማሽን እና ተያያዥ ቁሳቁሶችን በእርዳታ መለገሱ በፕሮጀክቱ ርክክብ ወቅት ተገልጿል፡፡