የቅድስት አርሴማ ጽላት በቁፋሮ ተገኘ።

 በተስፋዬ አእምሮ
 የካቲት 29፣2003 ዓ.ም
የሰሜን ሸዋ ሀገረ ስብከት አንጎለላና ጠራ ወረዳ በቂጣልኝ ቀበሌ የቅድስት አርሴማ ጽላት በቁፋሮ ተገኘ፡፡
 
ጽላቱ አባ ኃይለ ሥላሴ ለማ በተባሉ አባት አስተባባሪነት ዋሻ ውስጥ የተገኘ ሲሆን፥ ዋሻው በግራኝ ወረራ ዘመን የተዘጋ እንደሆነ ይታመናል፡፡ 
 
ከዚህ በፊት በዋሻው ውስጥ የተለያዩ ቅርሶች የተገኙ ሲሆን ሌሎች ቅርሶችን ለመፈለግ ቁፋሮ ሲካሄድ ይህ ጽላት እንደተገኘ ለቅርሱ እውቅና የሰጡት የአካባቢው ባሕልና ቱሪዝም ቢሮ እና ማኅበራዊ ፍርድ ቤት አረጋግጠዋል፡፡

የወረዳው ቤተ ክህነትና የኩሉ ወይን ቅዱስ ጊዮርጊስ ሰበካ ጉባኤም ለሚመለከታቸው አካላት እንዳሳወቁና በአሁኑ ጊዜም ጽላቱ ወደ ሀገረ ስብከቱ ሊቀ ጳጳስ ተወስዶ እንዲባረክና አገልግሎት መስጠት እንዲጀምር ለማድረግ ምእመናን በዝግጅት ላይ መሆናቸውን የደብረ ብርሃን ማዕከል ያደረሰን መረጃ ያመለክታል፡፡