አሥራ ሦስቱ ሕማማተ መስቀል

በሰሙነ ሕማማት ጠቅለል ባለ መልኩ የምናስባቸው የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስ ሕማማት አሥራ ሦስት ናቸው፡፡ እነርሱም አሥራ ሦስቱ ሕማማተ መስቀል ይባላሉ፡፡ ለክርስቲያኖች እነዚህን ሕማማተ መስቀል ማወቅና ዘወትር ማሰብ ተገቢ በመሆኑ እንደሚከተለው ቀርበዋል፡፡

1.     ተኰርዖተ ርእስ (ራስና በዘንግ መመታት)

መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ራሱን በዘንግ መመታቱንና መቀጥቀጡን የሚገልጥ ነው፡፡ ‹‹ተኰርዖት›› የሚለው ቃል ኩርዐ – መታ ከሚለው የግእዝ ግሥ የተገኘ ነው፡፡ ርእስ ደግሞ ራስ ማለት ነው፡፡ አገረ ገዥው ጲላጦስ ‹‹እኔ ከዚህ ጻድቅ ሰው ደም ንጹሕ ነኝ›› ብሎ እጁን ከታጠበ በኋላ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስን ገርፎ ለካህናት አለቆችና ለሽማግሎች አሳልፎ ሰጥቶት ነበር፡፡ በአይሁድ ሕግ የተገረፈ አይሰቀልም፤ የሚሰቀል ደግሞ አይገረፍም፡፡ እርሱ ጲላጦስ ግን ከገረፈው በኋላ፣ የበደል በደል፣ እንዲሰቅሉት አሳልፎ ሰጣቸው (ማቴ 27-24፤ ማር 15-15፤ ሉቃ 23-25፤ ዮሐ 18-39)፡፡
 
መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ተላልፎ ከተሰጠ በኋላ የእሾህ አክሊል ጐንጉነው ራሱ ላይ ደፍተውበታል፡፡ ራሱንም በዘንግ መትተውታል (ማር 15-19)፡፡ የሰው ዘር ከአዳም ጀምሮ በጠላቱ በዲያብሎስ በተጐነጐነ የኃጢአት እሾህ ራሱ ተይዞ ነበርና ይህንኑ ለማስወገድ ከሰማይ የወረደ ሰማያዊ የሆነ ዳግማዊ አዳም ክርስቶስ በጠላቶቹ በአይሁድ ተንኮል የተጐነጐነ አክሊለ ሦክ እንደ ዘውድ ደፋ፡፡ በሲኦል ወድቆ በዲያብሎስ ተረግጦ ራሱ የሚቀጠቀጠውን የሰውን ልጅ ለማዳን መድኃኔዓለም ክርስቶስ ራሱን በመቃ ተቀጠቀጠ፡፡ ከራሱ ላይ በሚወርደው ደም ፊቱ ተሸፈነ፡፡
 
2.     ተፀፍዖ መልታሕት (በጥፊ መመታት)

አምላካችን ኢየሱስ ክርስቶስ እጃቸው በደም፣ ጣቶቻቸው በበደል በረከሰ በአይሁድ እጅ በጥፊ መመታቱን የሚገልጥ ነው፡፡ ‹‹ተፀፍዖ›› የሚለው ቃል ፀፍዐ በጥፊ መታ ከሚለው የግእዝ ግሥ የወጣ ነው፡፡ መልታሕት ደግሞ ፊት ጉንጭ ማለት ነው፡፡
 
ጌታችን ለሊቀ ካህናት ቀያፋ እውነትን መናገር እንደ ስድብ ተቆጥሮበት መላልሰው ፊቱን በጥፊ መትተውታል፡፡ ፊቱንም በጨርቅ ሸፍነው ‹‹ክርስቶስ ሆይ በጥፊ የመታህ ማነው? ትንቢት ተናገርልን›› እያሉ ዘብተውበታል፡፡ በጠላት ዲያብሎስ እጅ ወድቆ በነፍሱ ይቀለድበትና ይንገላታ የነበረውን የሰውን ልጅ ለማዳን ብሎ በጠላቶቹ በአይሁድ እጅ ወድቆ ተጐሰመ፤ ተንገላታ፤ በጥፊም ተመታ (ማቴ 27-27)፡፡ ጲላጦስ አሳልፎ ከሰጠው በኋላም አክሊለ ሦክ በራሱ ላይ አኑረው ቀይ ልብስ አልብሰው ‹‹የአይሁድ ንጉሥ ሆይ፣ ሰላም ለአንተ ይሁን›› እያሉ እየተሳለቁበት በጥፊ መትተውታል (ዮሐ 19-2-4)፡፡ አላወቁትም እንጂ እርሱ በመንግሥቱ ሽረት፣ በባሕርዩ ሞት የሌለበት የዘለዓለም አምላክ ነው፡፡
 
3.     ወሪቀ ምራቅ (ምራቅ መተፋት)

ርኩሳን አይሁድ በብርሃናዊው የክርስቶስ ፊት ላይ በሚያስጸይፍ ሁኔታ ምራቃቸውን እንደተፉበት የሚገልጥ ነው፡፡ ‹‹ወሪቅ›› የሚለው ቃል ወረቀ ካለው ግእዛዊ ግሥ የተገኘ ነው፡፡ ትርጉሙም እንትፍ አለ፣ (ተፋ) ማለት ነው፡፡ በነቢዩ በኢሳይያስ መጽሐፍ (ምዕራፍ 5ዐ-6) ‹‹ፊቴንም ከውርደትና ከትፋት አልመለስኩም›› ተብሎ እንደተነገረ እየዘበቱበት ምራቃቸውን ተፉበት (ማቴ 27-29-3ዐ፤ ማር 15-19)፡፡ በኃጢአት የቆሸሸውን የሰውን ሕይወት ለማጥራት የመጣው ንጹሐ ባሕርይ አምላክ ተተፋበት፡፡ በሥራው ከገነት ተተፍቶ፤ ተንቆ፤ ተዋርዶ የነበረውን የሰውን ልጅ ለማዳን ኃጢአትን ይቅር የሚል እርሱ ጌታችን ያለ ኃጢአቱ ተተፋበት፤ ተናቀ፤ ተዋረደ፡፡ እንኳን በአምላክ ፊት በሰው ፊት እንኳን መትፋት እጅግ ያስነውራል፡፡ እርሱ ግን የኃጢአታችንን ነውር ከእኛ ሊያጠፋ ነውር የሆነውን ምራቅ ተቀበለ፡፡
 
4.     ሰትየ ሐሞት (መራራ ሐሞት መጠጣት)

ጌታችንና አምላካችን ኢየሱስ ክርስቶስ በመልዕልተ መስቀል ሳለ ተጠማሁ ባለ ጊዜ መራራ ሐሞት መጠጣቱን የሚገልጥ ነው፡፡ ‹‹ሰተየ›› ማለት ጠጣ ማለት ነው፡፡ ሐሞት የሚለውም አሞት ተብሎ በቁሙ ይተረጐማል፡፡ በመዝሙር 68 ቁጥር 21 ላይ ‹‹ለመብሌ ሐሞት ሰጡኝ፣ ለጥማቴም ሆምጣጤ አጠጡኝ›› ብሎ ነቢዩ ዳዊትን ትንቢት ያናገረ የነቢያት አምላክ ኢየሱስ ክርስቶስ የመጽሐፉ ቃል ይፈጸም ዘንድ ‹‹ተጠማሁ›› ባለ ጊዜ ሆምጣጤ ተሞልቶበት ተቀምጦ ከነበረው ዕቃ ሆምጣጤውን በሰፍነግ ሞልተው ወደ አፉ አቀረቡለት፡፡ ውኃ አጠጡኝ ቢላቸው በሐሞት የተደባለቀ የወይን ጠጅ ሊጠጣ አቀረቡለት፡፡ ቀምሶም ሊጠጣው አልወደደም (ማቴ 27-34)፡፡ ጌታችንም ሆምጣጤውን ከተቀበለ በኋላ ‹‹ተፈጸመ›› አለ፡፡ ራሱንም አዘንብሎ ነፍሱን አሳልፎ ሰጠ (ማቴ 27-48፤ ማር 15-36፤ ሉቃ 23-36፤ ዮሐ 19-29)፡፡
 
ቢጠጡት ለዘለዓለም የማያስጠማ ውኃ የሚሰጥ አምላክ፤ የተጠማችውን ነፍስ የሚያረካ ጌታ፤ ለዘለዓለም የሚፈልቅ የሕይወት ውኃ ምንጭ የሚያድል ፈጣሪ በተጠማ ጊዜ የፈጠረውን ውኃ እንኳን የሚያጠጣው የሚያቀምሰውም አላገኘም (ኢሳ 55-1)፡፡ አርባ ዓመት ሙሉ በቃዴስ በረሃ ኳትነው ለነበሩ አባቶቻቸው ከሰማይ መና አውርዶ የመገባቸው፤ ከአለት ላይ ውኃ አመንጭቶ ያጠጣቸው ክርስቶስ በተጠማ ጊዜ ቀዝቃዛ ውኃ ነፈጉት (ዘዳ 16-1-2ዐ፤ 1ቆሮ 1ዐ-3)፡፡ የዝናማት፤ የባሕርና የውቅያኖስ ጌታ በውኃ ጥም ተቃጠለ፡፡
 
መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በሲኦል በረሃ ወድቀው በሕይወት ውሃ ጥም የተቃጠሉትን ነፍሳት ለማርካት ሲል እርሱ ተጠማ፡፡ በኃጢአት ወድቀው፣ በበደል ረክሰው፣ በነፍሳቸው ተጐሳቁለው፣ መራራ መከራን የሚቀበሉትንና ምረረ ገሃነም አፉን ከፍቶ ሆዱን አስፍቶ የሚጠብቃቸውን ሁሉ ለማዳን መራራ ሐሞትን ቀመሰ፤ ሆምጣጣውንም ጠጣ፡፡ የመረረውን የሰው ልጆችን ሕይወት ለማጣፈጥ የመረረውን መጠጥ ተቀበለ፡፡

5.     ተቀሥፎ ዘባን (ጀርባን መገረፍ)

መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ጀርባው እስኪላጥ ያለ ርኅራኄ የመገረፉን ነገር የሚገልጥ ነው፡፡ ‹‹ተቀሥፎ›› የሚለው ቃል ቀሠፈ- ገረፈ ካለው የግእዝ ግሥ የተገኘ ነው፡፡ ‹‹ዘባን›› ደግሞ ጫንቃ፣ ትከሻ፣ ጀርባ ማለት ነው፡፡ ከላይ እንደተገለጠው የተገረፈ አይሰቀልም፡፡ የሚሰቀል ደግሞ አይገረፍም ነበር፡፡ ጲላጣስ ግን ኢየሱስ ክርስቶስን አስገረፈው፡፡ ከደሙ ንጹሕ ነኝ ብሎ ከታጠበ በኋላ ክርስቶስን ያለ ኃጢአቱ በመግረፍ ለአይሁድም አሳልፎ በመስጠት ‹‹ታጥቦ ጭቃ›› እንዲሉ የታጠበ እጁን መልሶ አቆሸሸው (ማቴ 27-28፤ ማር 15-15፤ ዮሐ19-1)፡፡
 
መድኃኒታችን መንፀፈ ደይን ወድቆ በእግረ አጋንንት ተጠቅጥቆ በእሳት አለንጋ የሚገረፈውን የሰው ልጅ ለማዳን ሲል ጀርባውን ለግርፋት ሰጠ፡፡ ሥጋው አልቆ አጥንቱ እስኪቆጠር ተገረፈ፡፡ አይሁድ አገረ ገዥያቸው ጲላጣስ ላቀረበላቸው ምርጫ ይፈታላቸው ዘንድ ነፍሳትን ከሲኦል የሚያወጣውን ክርስቶስን ሳይሆን ራሱን እንኳን ከምድራዊ ወህኒ ማውጣት ያልቻለውን ወንበዴውን በርባንን መረጡ፡፡ መገረፍ ይገባው የነበረ በርባን ተለቀቀ፡፡ በነቢዩ በኢሳይያስ ‹‹ጀርባዬን ለገራፊዎች፣ ጉንጬንም ለጠጉር ነጪዎች ሰጠሁ›› (በኢሳ 5ዐ-6) ተብሎ እንደተነገረ ጀርባውን ለገራፊዎች አሳልፎ ሰጠ፤ ጽሕሙንም ተነጨ፡፡ ይህ ሁሉ የሆነው የሰው ልጅ ከሚያድነው አምላክ ይልቅ የሚገርፈውንና የሚዘርፈውን ወንበዴ መርጦ ስለተገኘ ነው፡፡
 
6.     ተዐርቆተ ልብስ (ከልብስ መራቆት)

አምላካችን ኢየሱስ ክርስስቶስ ልብሱን መራቆቱን የሚገልጥ ነው፡፡ ‹‹ተዐርቆተ›› ማለት ታረዘ፤ ተራቆተ ማለት ነው፡፡ ፀሐይና ከዋክብትን ብርሃን አልብሶ የፈጠረ አምላክ ተራቆተ፡፡ ጸጋውን ለዕሩቃን የሚያለብስ አምላክ ልብሱን ተገፍፎ ዕራቁቱን ቆመ፡፡ ጨለማን ለብሶ ጨለማን ተንተርሶ ይኖር የነበረውን ሰው መልሶ ብርሃን ያለብሰው ዘንድ የብርሃናት ጌታ፣ የጸጋ ሁሉ አምላክ ኢየሱስ ክርስቶስ ተገፈፈ፤ ተራቆተ፡፡
 
የሲኦል ወታደሮች የሆኑት አጋንንት የሰውን ልጅ ጸጋ ገፍፈውት ነበርና ጲላጦስ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስን አሳልፎ በሰጣቸው ሰዓት ወታደሮች ልብሱን ገፍፈውታል (ማቴ 27-27)፡፡ የሰው ልጅ ለቀረበለት ምርጫ የሰው ምላሽ ዘራፊው፤ ገራፊው ወንበዴ በርባን እንዲፈታለት ነበር፡፡ ‹‹አቅረብኩ ለከ እሳተ ወማየ፣ ደይ እዴከ ኅበ ዘፈቀድከ! እነሆ እሳትና ውኃን አቅርቤልሃለሁ፣ እጅህን ወደ ፈቀድከው ስደድ›› ሲባል የሰው ልጅ እጁን ወደ እሳት ሰደደ፡፡
 
7.     ርግዘተ ገቦ (ጎንን መወጋት)

መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ነፍሱን ለሞት አሳልፎ ከሰጠ በኋላ ጎኑን በስለታም ጦር መወጋቱን የሚገልጥ ነው፡፡ ‹‹ርግዘት›› የሚለው ቃል ረገዘ- ወጋ ከተሰኘ የግእዝ ግሥ የወጣ ነው፡፡ ገቦ ማለት ደግሞ ጎን ማለት ነው፡፡ ከጌታችን ከኢየሱስ ክርስቶስ አጠገብ፣ በግራና በቀኙ ሁለት ወንበዴዎች ተሰቅለው ነበር፡፡ ሥጋቸው በሰንበት በመስቀል ላይ እንዳይኖር ጭናቸው ተሰብሮ እንዲወርዱ አይሁድ ጲላጦስን በለመኑት መሠረት ጭፍሮቹ የሁለቱን ወንበዴዎች ጭን ጭናቸውን ከሰበሩ በኋላ ወደ ጌታችን ወደ ኢየሱስ ሲመጡ ፈጽሞ እንደሞተ አይተው ጭኑን አልሰበሩም፡፡ ነገር ግን ከጭፍሮቹ አንዱ ጎኑን በጦር ስለወጋው ወዲያው ከጎኑ ደምና ውኃ ፈሰሰ (ዮሐ 19-33)፡፡
 
አምላካችን ኢየሱስ ክርስቶስ ሞትን ድል ያደርገው ዘንድ ሞተ፤ የሰው ልጅ በዘለዓለማዊ ሞት ተይዞ ነበርና፡፡ ትልቁ ሞት በኃጢአት ምክንያት ከእግዚአብሔር መለየት ነው፡፡ በጌታችን ሞት ግን ሞት ራሱ ድል ተነሣ፡፡ የሞት መውጊያ በሆነ ኃጢአት የሞተውን ሰው ለማዳን ጎኑን በጦር ተወጋ፡፡ በሰው ልቡና ተተክሎ የነበረውን ኃጢአት ከነሥሩ ነቅሎ ስለጣለው ‹‹ሞት ሆይ መውጊያህ የት አለ?›› ተባለ፡፡ የሞት መውጊያው ኃጢአት ነበርና (1ቆሮ 15-54-55፤ ኢሳ 25-8፤ ሆሴ 13-14)፡፡
 
ከተወጋው የጌታችን ጎን ደምና ውኃ መፍሰሱም የእግዚአብሔርን ልጅነትና የዘለዓለምን ሕይወት አጥቶ የነበረው ሰው ልጅነቱና ሕይወቱ እንደተመለሰለት የሚያረጋግጥ ነው፡፡ ምክንያቱም ከጎኑ በፈሰሰው ውኃ ተጠምቆ ልጅነትን፣ ደሙንም ጠጥቶ የዘለዓለም ሕይወትን ያገኛልና (ዮሐ 3-5፤ ዮሐ 6-54)፡፡
 
8.     ተአሥሮተ ድኅሪት (ወደ ኋላ መታሠር)

ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ሁለት እጆቹን ወደኋላ የፊጥኝ መታሠሩን የሚገልጥ ነው፡፡ ‹‹ተአሥሮት›› የሚለው ቃል አሠረ (ሲነበብ ይላላል) ከሚለው የግእዝ ግሥ የተገኘ ሲሆን ትርጉሙም አሠረ ማለት ነው፡፡ ‹‹ድኅሪት›› የሚለው ቃል ደግሞ ተድኅረ- ወደኋላ አለ ከሚለው ግሥ የወጣ ነው፡፡ መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ጊዜው በደረሰ ሰዓት ራሱን ለአይሁድ አሳልፎ በሰጠባት በዚያች ዕለትና ሰዓት ሻለቃውና ጭፍሮቹ የአይሁድም ሎሌዎች እጁን የኋሊት አሥረው መሬት ለመሬት ጎትተውታል፡፡ አፍገምግመውታል (ዮሐ 18-12)፡፡
 
በኃጢአት ሰንሰለት የኋሊት ታሥሮ ጠላት ዲያብሎስ የሚያፍገመግመውን የሰው ልጅ ለማዳን፣ ሰውንም ከኃጢአት እሥራት ይፈታ ዘንድ ሲል መድኃኔዓለም ክርስቶስ በጠላቶቹ በአይሁድ እጅ የኋሊት ታሠረ፡፡
 
9.     አምሥቱ ቅንዋተ መስቀል

መድኃኒታችን በመስቀል ላይ የተቸነከረባቸውን ጠንካራ የብረት ችንካሮች (ምስማሮች) የሚገልጥ ነው፡፡ ‹‹ቅንዋት›› የሚለው ቃል ቀነወ- ቸነከረ ከሚለው የግእዝ ግሥ የተገኘ ነው፡፡ መስቀል ማለት ደግሞ ዝም ብሎ የቆመ ግንድ ሳይሆን አሁን በየሥፍራው እንደምናየው ምልክት የተመሳቀለ እንጨት ነው፡፡ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የተቸነከረባቸው አምስቱ ችንካሮች ሳዶር፣ አላዶር፣ ዳናት፣ አዴራ፤ ሮዳስ ይባላሉ፡፡ እነዚህም የአምሥቱ አዕማደ ምሥጢራት ምሳሌዎች መሆናቸውን አበው ያስተምራሉ፡፡
 
ሐዋርያው ቶማስ ከትንሣኤ በኋላ ወንድሞቹ ሐዋርያት ስለ ትንሣኤው በነገሩት ጊዜ ‹‹የችንካሩን ምልክት በዓይኖቼ ካላየእንኳን ብንሆን እግዚአብሔር ከኛ ጋር ከሆነ ማንም አያሸንፈንም፡፡ 

Melakit_Yemegebuat_Blatena.jpg

መላእክት የመገቧት ብላቴና

መ/ር መንግሥተአብ አበጋዝ

  Melakit_Yemegebuat_Blatena.jpg

እንደምን ሰነበታችሁ ልጆች? መላእክት በሰማይ የሚኖሩ የእግዚአብሔር አገልጋዮች መሆናቸውን ታውቃላችሁ አይደል? በመጽሐፍ ቅዱስ የሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ መልእክት ወደ ዕብራውያን ሰዎች ምዕራፍ 1 ቁጥር 7 ላይ ይገኛል፡፡

 

በጣም ጥሩ ልጆች ከዚህ በተጨማሪ መላእክት በማቴዎስ ወንጌል ምዕራፍ 18 ቁጥር 10 ላይ እንደተገለጸው፤ እኛን የሰው ልጆችን ሁሉ ከክፉ የሚጠብቁ እና በእግዚአብሔር ፊት የሚጸልዩልን ናቸው፡፡

ዛሬ የምንነግራችሁ ከቅዱሳን መላእክት አንዱ የሆነው ቅዱስ ፋኑኤል የተባለው መልአክ የፈጸመውን ተግባር ነው፡፡

ኢያቄምና ሐና የተባሉ የእግዚአብሔር ሰዎች በስዕለት ያገኟትን ልጃቸውን ለእግዚአብሔር ቤት ሊሰጧት በሦስት ዓመቷ ወደ ቤተ መቅደስ ይዘዋት መጡ፡፡
የቤተ መቅደሱም አገልጋዮች /ካህናት/ በኢያቄምና ሐና አሳብ ተገርመው ሕጿኗን ምን እንመግባታለን እያሉም ተጨነቁ፡፡

በዚህ ወቅት ነበር አንድ አስደናቂ ነገር በቤተ መቅደሱ ዙሪያ የታየው፡፡ ስሙ ፋኑኤል የተባለው መልአክ በእጁ ሕብስትና ወይን ይዞ መጥቶ ነበርና የቤተ መቅደሱ አካባቢ በብርሃን ተሞላ፡፡

የቤተ መቅደሱ ሓላፊ ካህኑ ዘካርያስ ለእርሱ መልእክት ሊያደርስ የመጣ መስሎት ወደ መልአኩ ተጠጋ፡፡ መልአኩ ግን ከእርሱ ራቀ፡፡ ደግሞም በየተራ ሕዝቡም ካህናቱም ወደ መልአኩ ቀረቡ መልአኩ ግን ከሁሉም እየራቀ ከፍ አለ፡፡

ከዚህ በኋላ ካህናቱ የእግዚአብሔር ጥበብ አይታወቅምና መልአኩ የመጣው ለብላቴናዋ /ለሕጻኗ/ ይሆናልና፤ ሐና ሆይ እስኪ ትተሻት እልፍ በይ አሏት፡፡ ሐናም ሕጻን ልጇን ትታት ራቅ አለች፡፡ በዚህ ጊዜ መልአኩ ብላቴናይቱን አንድ ክንፉን አንጥፎ አንድ ክንፉን ጋርዶ የሰው ቁመት ያህል ከመሬት ከፍ አደረጋትና መግቧት ወደ ሰማይ ተመለሰ፡፡

በእግዚአብሔር ሥራ ሕዝቡ ሁሉ ተደነቁ፡፡ ምን እንመግባታለን? እያሉ ይጨነቁ የነበሩት ካህናትም የምግቧን ነገር መልአኩ ከያዘልንማ ብለው ቤተ መቅደስ እንድትገባ አደረጓት፡፡ ብላቴናይቱም መላእክት እየመገቧት እስከ አሥራ አምስት ዓመቷ በቤተ መቅደስ ኖረች፡፡

ልጆች ይህች ብላቴና ማን ናት?

እናትና አባቷ ማን ይባላሉ? 

ይመግባት የነበረው መልአክ ስሙ ማን ነው? በሉ ደህና ሁኑ!
ወላጆች:- ለሕጻናት ተጨማሪ ጥያቄ በማቅረብ ታሪኩን በቃል እንዲያጠኑና እንዲነግሯችሁ አድርጉ፡፡

ጸሎትና ጥቅሙ

             

ልጆች ትምህርት ጥሩ ነው?ቤተ ክርስቲያን እሑድ እሑድ ትሔዳላችሁ ? በጣም ጥሩ ልጆች ! ዛሬ የምንማማረው ስለ ጸሎት ጥቅም ነው፡፡ ጸሎት ማለት ከእግዚአብሔር የምንገናኝበት እግዚአብሔርን የምናመሰግንበት ትልቅ ኃይል ማለት ነው፡፡

በጸሎት የእግዚአብሔርን ሩህሩህነት፣ ቸርነት ኃያልነት እንገልጻለን፡፡ በጸሎት እግዚአብሔር ያደረገልንን ሁሉ አስታውሰን ምስጋና እናቀርባለን፡፡  በጸሎት በደላችንን ለእግዚአብሔር እንናዘዛለን፡፡ ይቅርታውንም እንጠይቃለን፡፡ በጸሎት ከእግዚአብሔር የፈለግነውንና የጐደለንን ለማግኘት እንለምናለን፡፡ ጸሎት ይቅርታ መጠየቂያ በመሆኗ ከቅጣትና ከመከራ የምታድን ናት፡፡ እንግዲህ ልጆች በአጠቃላይ የጸሎት ጥቅም ተነግሮ የሚያልቅ አይደለም፡፡ ልጆች እናንተስ ጠዋት ከመኝታችሁ ስትነሡ ማታ ስትተኙ ትጸልያላችሁ ?
ወይንስ ዝም ብላችሁ ትተኛላችሁ፡፡ ትነሣላችሁ? ማታ ስትተኙ እግዚአብሔርን አመስግናችሁ ጠዋት ስትነሡ እግዚአብሔርን አመስግናችሁ ጸልያችሁ መዋል አለባችሁ፡፡ ልጆች ምግብም ስትመገቡ ጸሎት አድርሳችሁ መመገብ አለባችሁ፡፡ ልጆች ጸሎት ትምህርታችሁን ይገልጽላችኋል፡፡ ከብዙ ክፉ ነገር እግዚአብሔር ይጠብቃችኋል፡፡
እንግዲህ ልጆች ጸሎት ብዙ ዓይነት ነው፡፡ 1ኛ የግል ጸሎት፣ 2ኛ. የማኅበር ጸሎት 3ኛ. የቤተሰብ ጸሎት አለ፡፡ ስትጸልዩ በጸጥታና ካለወሬ መጸለይ ያስፈልጋችኋል፡፡ በአጠቃላይ የጸሎትን ጥቅም ማወቅ ይገባናል፡፡ እሺ ልጆች! ከብዙ በጥቂቱ የጸሎትን ጥቅም እንዳወቃችሁ ተስፋ እናደርጋለን፡፡

ሥነ ፍጥረት

ልጆች የምንነግራችሁ ስለ ሥነ ፍጥረት ነው፡፡ እግዚአብሔር የሚታየውን ዓለም የፈጠረው በስድስት ቀናት ውስጥ ነው፡፡ ይህም በአንድ ቀን ለመፍጠር አቅም አጥቶ አይደለም፡፡ እርሱ ባወቀ ሁሉን በሥርዐትና በአግባቡ ለማድረግ ብሎ ነው እንጂ፡፡ ደግሞም ፈቃዱና ጊዜውም ስለሆነ ፍጥረታትን በስድስት ቀናት ውስጥ አከናወነ፡፡ 

 
የዕለታት መጀመሪያ እሑድ ናት፡፡ እግዚአብሔር በዕለተ እሑድ በመጀመሪያው ቀን አራቱ ባሕርያት የተባሉትን መሬት፣ ውኃ፣ ነፋስ፣ እሳትን ፈጠረ፡፡ በሁለተኛዋ ዕለተ ሰኞ እግዚአብሔር ጠፈርን ፈጠረ፡፡
በሦስተኛው ቀን በዕለተ ማክሰኞ ልዑል እግዚአብሔር ምድርን፣ ዘርን የሚሰጥ ሣርንና ቡቃያን በምድርም ላይ እንደ ወገኑ ዘር ያለበትን ፍሬን የሚያፈራ ዛፍን ታብቅል ብሎ በዚያ መሬት፣ አትክልትን፣ አዝርዕትን፣ ዕፅዋትን አስገኘች /ዘፍ. 1፡12/ እነዚህ ከአራቱ ባሕርያት መካከል ከመሬት፣ ከውኃ፣ ከነፋስ ተፈጠሩ፡፡
ዓርብ በመጀመሪያው ሰዓት በመዓልት ልዑል እግዚአብሔር አዳምን ፈጠረው፡፡ ከአዳም በፊት የተፈጠሩት ፍጥረታት በሀልዮና በነቢብ የተፈጠሩ ሲሆን፤ እግዚአብሔር አዳምን የፈጠረው በእጆቹ በማበጃጀት ነው፡፡ እግዚአብሔር ሰውን ለመፍጠር ሰውን በመልካችንና በአርአያችን እንፍጠር አለ /ዘፍ. 1፡26/
በአራተኛው ቀን የረቡዕ ፍጥረት የሆኑት በሰማይ ጠፈር ብርሃን ይሁን ብሎ በቃል በማዘዝ ሦስቱን ፍጥረታት ፀሐይን፣ ጨረቃንና ከዋክብትን ፈጠራቸው፡፡ /ዘፍ.1፡14/ ሐሙስ ማለት አምስተኛ ዕለት ማለት ነው፡፡ በዕለተ ሐሙስ የተፈጠሩት ሦስቱ ፍጥረታት ዘመደ እንስሳ የሚባሉት ዓሣዎች ዘመደ አራዊት የሚባሉት አዞ፣ ጉማሬ፣ እንቁራሪት፣ ዘመደ አዕዋፍ የሚባሉት ዳክዬዎች ዝዬዎች ናቸው፡፡
በዕለተ ዓርብ እግዚአብሔር የፈጠራቸው ፍጥረታት በልብ የሚሳቡ በእግር የሚራመዱ በክንፍ የሚበሩ ናቸው፡፡ ሁሉንም የፈጠራቸው ሴትና ወንድ አድርጎ ነው፡፡ለምሳሌ የቤት እንስሳት ላም፣ በሬ፣ ፈረስ፣ በቅሎ፣ ፍየል፣ በግ ውሻ እና ድመት ናቸው፡፡
አዕዋፍ ዶሮ፣ ድንቢጥ፣ እርግብ ሌሎችም ናቸው፡፡ እንስሳት ለምሳሌ አጋዘን፣ ፊቆ፣ ሚዳቋ፣ ጎሽ፣ ዝሆን፣ ዋልያ የመሳሰሉት ናቸው፡፡
ቀዳሚት ሰንበት ማለት ቅዳሜ ማለት ነው፡፡ በዚች ዕለት ልዑል እግዚአብሔር ሊፈጥረው የወደደውን ሃያ ሁለቱን ሥነ ፍጥረት ፈጥሮ አከናውኖ አረፈባት፡፡ /ዘፍ.2፡2/ በመሆኑም እግዚአብሔር ባርኮ  የቀደሳትን ዕለት ማክበር ይገባል፡፡
ልጆች እስኪ ጥያቄ እንጠይቃችሁ
1ኛ. ሀልዮና ነቢብ ማለት ምን ማለት ነው?
2ኛ. ሔዋን እንዴት ተፈጠረች?
ልጆች በመጠኑም ቢሆን ሥነ ፍጥረትን እንዳወቃችሁ ተስፋ እናደር 
ጋለን፡፡ በተረፈ ሰንበት ትምህርት ቤት ሔዳችሁ ተማሩ እሺ ጎበዞች፡፡