የትምህርተ ሃይማኖት መቅድም
በሊቀ ጉባኤ አባ አበራ በቀለ አሚንሰ መሰረት ይእቲ ወካልአኒሃ ሕንጻ ወንድቅ እሙንቱ- እምነት መሠረት ናት ፤ ሌሎቹ ግን ሕንጻና ግንብ ናቸው:: በማለት ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ የሚያስገነዝበን እንደ ሕንጻና ግንብ ከሚቆጠሩት ከምግባርና ከትሩፋት ሁሉ በፊት የሃይማኖትን ቀዳሚነትና መሠረትነት ነው፡፡ መሠረት ሕንጻውን ሁሉ እንደሚሸከም እምነትም ምግባራትን ሁሉ ትይዛለች ፤ ሕንጻ ያለ መሠረት እንደማይቆም ምግባርም ያለ ሃይማኖት አይኖርም፡፡ […]