ሰባቱ ምስጢራተ ቤተክርስቲያን

በብፁዕ አቡነ ጎርጎርዮስ ካልዓይ
 
ቤተ ክርስቲያን የመንፈስ ቅዱስ የጸጋው ግምጃ ቤት ስለሆነች መስቀል ላይ የተሰጠውን አምላካዊ ጸጋ በእምነት ለሚቀርቧት ሁሉ ታድላለች ፣ ትምህርቷን አምነው የተቀበሉ ሁሉ የዚህ ጸጋ ተካፋዮች ናቸው፡፡ ይህን ጸጋ ለምዕመናን የምታድልባቸውን መሳሪያዎች ምሥጢራት ትላቸዋለች፡፡