Entries by Mahibere Kidusan

ሕገ ቤተ ክርስቲያን ስለ ቅዱስ ሲኖዶስና ስለ ቅዱስ ፓትርያርክ ምን ይላል?

ግንቦት 11፣2003ዓ.ም

ቅዱስ ሲኖዶስ በ1991 ዓ.ም ባወጣው ሕገ ቤተ ክርስቲያን ውስጥ ስለ ቅዱስ ሲኖዶስና ስለ ቅዱስ ፓትርያርክ የሚናገሩ ምዕራፎች እና አንቀጾችን አቅርበናል፡፡

ምዕራፍ ሁለት

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ

አንቀጽ 5
የቅዱስ ሲኖዶስ ልዕልና /የበላይነት/

1.    በመንፈስ ቅዱስ የሚመራው ቅዱስ ሲኖዶስ የመንበረ ሐዋርያት ወራሽ ስለሆነ በቤተ ክርስቲያኒቱ የመጨረሻው ከፍተኛ ሥልጣን ባለቤት ነው፡፡

2.    ከማንኛውም የቤተ ክርስቲያኒቱ የሥልጣን መዋቅር ሁሉ የበላይ አካል ቅዱስ ሲኖዶስ ስለሆነ ሕጐችን፣ ልዩ ልዩ ደንቦችንና መመሪያዎችን የማውጣትና የዳኝነት ሥልጣን አለው፡፡

ቅዱስ ሲኖዶስ ጠንካራ ውሳኔ ያሳልፋል ተብሎ ይጠበቃል

ግንቦት 10/2003 ዓ.ም.

በቤተክርስቲያኒቱ አጠቃላይ ሁኔታ ላይ የሚመክረው የቅዱስ ሲኖዶስ ጉባኤ በቀጣይ በቤተክርስቲያኒቱ አገልግሎት መጠናከርና በገጠሟት ችግሮች ላይ መፍትሔን የሚሰጥ ጠንካራ ውሳኔ ያሳልፋል ብሎ እንደሚያምን ማኅበረ ቅዱሳን አስታወቀ፡፡ የማኅበሩ ሰብሳቢ ቀሲስ ዶ/ር ሙሉጌታ ሥዩም እንዳስታወቁት፤ ዘንድሮ ከግንቦት 10 ቀን ጀምሮ የሚካሔደው ዓመታዊ መደበኛ የቅዱስ ሲኖዶስ ጉባኤ በእግዚአብሔር አጋዥነት እና በመንፈስ ቅዱስ የሚመራ በመሆኑ ጠቃሚ ሀሳቦች የሚነሡበት፤ ለቅድስትቤተክርስቲያን የሚበጁ ጠንካራ ውሳኔዎች የሚተላለፉበት እንደሚሆን ማኅበረ ቅዱሳን በፅኑ ያምናል፡፡

«እርሳቸው የያዙት መንገድ ሙሉ በሙሉ የኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያንን ማዳከም ነው፡፡ » ማኅበረ ቅዱሳን

 ግንቦት 9/2003ዓ.ም
ማኅበረ ቅዱሳን ተመሥርቶ በሰ/ት/ቤቶች ማደራጃ መምሪያ ሥር አገልግሎት ከጀመረ አንስቶ ወደ 10 የሚጠጉ የመምሪያ ኃላፊዎች ተፈራርቅዋል፡፡ እስከ አሁን ምንም ያልተባለለት የማኅበሩና ማደራጃ መምሪያው ግንኙነት፣ የአሁኑ የመምሪያው ኃላፊ አባ ሠረቀብርሃን ከመጡ ከ6 ዓመት በፊት ጀምሮ፣ ችግሮች እየገጠሙት እንደሆነ ይነገራል፡፡ ማኅበሩም አሁን ያሉት የመምሪያው ኃላፊ አላሠራኝ አሉ በማለት ይወቅሳል፡፡ ይህንን በተመለከተ ከማኅበሩ ዋና ጸሐፊ ዲ/ን ሙሉጌታ ኃ/ማርያም ጋር ቆይታ አድርገናል፡፡ መልካም ንባብ፡፡
 

ማኅበረ ቅዱሳን የስብከተ ወንጌል ማስፋፊያ ፕሮግራም ቢሮ ያከናውናቸውን ተግባራት አስታወቀ።

በይብረሁ ይጥና

ሥራዎቹንም የሚያሳይ ዓውደ ጥናት በኢትዮጵያ የስብሰባ ማእከል እንደሚካሔድ ተገልጧል

በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ሰንበት ትምህርት ቤቶች ማደራጃ  መምሪያ ማኅበረ ቅዱሳን በትምህርትና ሐዋርያዊ አገልግሎት ዋና ክፍል የስብከተ ወንጌል ማስፋፊያ ፕሮግራም ማስተባበሪያ ቢሮ እስካሁን ያከናወናቸውንና በቀጣይ ሊሠራ ያቀዳቸውን ተግባራት አስታወቀ፡፡

ሶርያዊው ቅዱስ ኤፍሬም (ክፍል ሦስት)

ዲ/ን ዮሐንስ ልሳነወርቅ

ግንቦት 4፣ 2003ዓ.ም

ከክፍል ሁለት የቀጠለ

5.የሥጋ(ሰውነት) ክብር (The value of the Body)

ቅዱስ ኤፍሬም የሥጋን ክብር ለመንቀፍ  ከሚሹ ከተወሰኑ የቀድሞ የክርስትና ልማዶች መገለጫ ከሆኑት ከፕላቶናዊ ወይም ከምንታዌ ዝንባሌዎች  ፣  በእጅጉ የራቀ ነው። ለቀና አመለካከቱ መነሻው ነጥብ ሥጋ ከእግዚአብሔር ፍጥረታት መካከል ስለሆነ ሊጠላ አይገባዉም የሚል እውነታ ነው፤ በየትኛዉም መንገድ  ክፉ ተደርጎ ከሚታሰበው አስተሳሰብ  የራቀ ይሁን። ግና በተጨማሪ ቅዱስ ኤፍሬም ሦስት ጠቃሚ ግንዛቤዎች አሉት።

የሆሣዕና ምንባብ17(ዮሐ.5÷11-31)

እርሱም መልሶ÷ “ያዳነኝ እርሱ፡- አልጋህን ተሸክመህ ሂድ አለኝ” አላቸው፡፡ አይሁድም÷ “አልጋህን ተሸክመህ ሂድ ያለህ ሰውዬው ማነው?” ብለው ጠየቁት፡፡ ያ የተፈወሰው ግን ያዳነው ማን እንደ ሆነ አላወቀም፤ ጌታችን ኢየሱስ በዚያ ቦታ በነበሩት ብዙ ሰዎች መካከል ተሰውሮ ነበርና፡፡ ከዚህም በኋላ ጌታችን ኢየሱስ ያን የዳነውን ሰው በቤተ መቅደስ አገኘውና÷ “እነሆ÷ ድነሃል፤ ግን ከዚህ የባሰ እንዳያገኝህ ደግመኛ እንዳትበድል ተጠንቀቅ” […]

የሆሣዕና ምንባብ16(ሐዋ.28÷11-ፍጻ.)

 ከሦስት ወር በኋላም በዚያች ደሴት ወደ ከረመችው ወደ እስክንድርያ መርከብ ወጣን፤ በዚያች መርብ ላይም የዲዮስቆሮስ ምልክት ነበረባት፤ ይኸውም “የመርከበኞች አምላክ” የሚሉት ነው፡፡ ከዚያም ሄደን ወደ ሰራኩስ ደረስን፤ በዚያም ሦስት ቀን ተቀመጥን፡፡ ከዚያም ሄደን ሬቅዩን ወደምትባል ሀገር ደረስን፤ በማግሥቱም ወጣን፤ ከአንድ ቀንም በኋላ ከጐንዋ ነፋስ በነፈሰ ጊዜ በሁለተኛው ቀን ወደ ፑቲዮሉስ ደረስን፡፡ በዚያምም ወንድሞችን አግኝተን ተቀበሉን፤ […]

የሆሣዕና ምንባብ15(1ኛጴጥ.4÷1-12)

 ክርስቶስ ስለ እኛ በሥጋው ከተሰለቀ÷ እናንተም ይህቺን ዐሳብ ጋሻ አድርጋችሁ ኑሩ፤ በሥጋዉ መከራ የተቀበለ ከኀጢአት ድኖአልና፡፡ ከእንግዲህ ወዲህ በሥጋው ከሕይወቱ ዘመን የቀረውን÷ በሰው ፈቃድ ሳይሆን በእግዚአብሔር ፈቃድ እንዲፈጽም ነው እንጂ፡፡ የአሕዛብን ፈቃድ፡- ዝሙትንና ምኞትን÷ ስካርንና ወድቆ ማደርን÷ ያለ ልክ መጠጣትንና ጣዖት ማምለክን ያደረጋችሁበት ያለፈው ዘመን ይበቃችኋልና፡፡ እንግዲህ ወደዚህ ሥራ እንዳትሮጡ ዕወቁ፤ ከዚች ጎዳናና መጠን ከሌለው […]

የሆሣዕና ምንባብ14(ዕብ. 9÷11-ፍጻ.)

 ክርስቶስ ግን ለምትመጣይቱ መልካም ነገር ሊቀ ካህናት ሆኖ÷ የሰው እጅ ወደ አልሠራት÷ በዚህ ዓለም ወደ አልሆነችው÷ ከፍተኛዪቱ ወደምትበልጠውና ወደምትሻለው ድንኳን÷ የዘለዓለም መድኀኒትን ገንዘብ አድርጎ÷ በገዛ ደሙ አንድ ጊዜ ወደ መቅደስ ገባ እንጂ በላምና በፍየል ደም አይደለም፡፡ የላምና የፍየል ደም÷ በረከሱትም ላይ የሚረጭ የጊደር አመድ÷ የሚያነጻና የረከሱትንም ሥጋቸውን የሚቀድሳቸው ከሆነ÷ ነውር የሌለው ሆኖ÷ በዘለዓለም መንፈስ ራሱን […]