Entries by Mahibere Kidusan

የዝቋላ ደን ቃጠሎ ተጨማሪ እርዳታ እንደሚያስፈልገው ተገለጠ፡፡

መጋቢት 11/2004 ዓ.ም

በተ/ሥላሴ ጸጋ ኪሮስ

የዝቋላ ደብረ ከዋክብት አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ገዳም ደን ቃጠሎ ተጨማሪ እርዳታ እንደሚያስፈልገው ተገለጠ፡፡

በቦታው የተገኙት የማኅበረ ቅዱሳን ሰብሳቢ ሊቀ ትጉሃን ቀሲስ ዶ/ር ሙሉጌታ ሥዩም እንደገለጡልን በቦታው በርካታ ምእመናን ተገኝተው እሳቱን ለማጥፋት ጥረት ቢያደርጉም በአስቸጋሪው የአየር ጠባይ የተነሣ ፍህሙ እየተነሳ እንደገና እንዲያገረሽ ስለሚያደርገው ከፍ ያለ እርዳታ እንደሚያስፈልግ ተናግረዋል፡፡

A Burning Heaven in This World – Mt. Zeqwala Monastery

March 20/2012                                                                                  Hiruy Simie

ZeqwalaThe area of Mt. Zeqwala is a product of intense volcanic activity during a quaternary period. The cooling age produced a well preserved cone structure form of the volcanic eruption. The vent formed after the cooling of the eruption was filled by rain to become a huge crater lake. Written Church sources came to mention the place after the coming of his holiness Abune Gebre Menfes Kidus and his founding of the monastery that is still dedicated to him in 1168 Ethiopian calendar. However, the story of a church built by King Gebre Meskel and St. Yared on the mountain which vanished miraculously is told by the local monks. (read more)

በዝቋላ ደብረ ከዋክብት አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ገዳም የደን ቃጠሎ በባሰ ሁኔታ ላይ ይገኛል!

መጋቢት 10/2004 ዓ.ም.

በእንዳለ ደምስስ


እሳት ወይስ መአት?


በዝቋላ ደብረ ከዋክብት አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ገዳም የደን ቃጠሎ በባሰ ሁኔታ ይገኛል፡፡ ቅዳሜ መጋቢት 8/2004 ዓ.ም. ከቀኑ 6፡00 በኋላ ልዩ ስሙ አዱላላ ከሚባለው አቅጣጫ የተቀሰቀሰው ቃጠሎ በመነኮሳትና በአካባቢው ምእመናን ለማጥፋት ከፍተኛ ጥረት  እያደረጉ እንደሚገኙና ከደብረ ዘይት የአየር ኀይል አባላት ትላንት ምሽት መጥተው እገዛ ለማድረግ ጥረት ማድረጋቸውን የገዳሙ ጸሐፊ አባ ወ/ሩፋኤል ቢገልጹም መፍትሔ እንዳልተገኘ ታውቋል፡፡

 

የዝቋላ ደብረ ከዋክብት አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ገዳም ደን እየተቃጠለ ነው፤ የምእመናንን እገዛ ይሻል፡፡

መጋቢት 10/2004 ዓ.ም. በተ/ሥላሴ ጸጋ ኪሮስ ቅዳሜ መጋቢት 8 ቀን 2004 ዓ.ም ከቀኑ 6፡00 በኋላ የጀመረው የገዳሙ ቃጠሎ እየተባባሰ እንደሆነ የገለጹልን ያነጋገርናቸው የገዳሙ መነኮሳት እሳቱን ለማጥፋት የምእመናንን እርዳታ እንደሚሻ አሳስበዋል፡፡   አያይዘውም ለእርዳታ የሚመጡ ምእመናን ስንቅ እንዲይዙና በውኃ ጥም እንዳይቸገሩ ከቻሉ ውኃ እንዲይዙ፤ ቦቴ መኪና ያላቸውም እንዲተባበሩ ጠይቀዋል፡፡   በአሁኑ ወቅት ምእመናን ከደብረ ዘይትና አዲስ […]

ቦጅ ትጮሀለች!

መጋቢት 10/2004 ዓ.ም.

በዲ/ን ኅሩይ ባየ

ኘሮቴስታንቲዝም በምዕራቡ ዓለም ተጸንሶ ተወልዶና አድጐ የጐለበተ ከካቶሊካዊት ቤተክርስቲያን ያፈነገጠ የእምነት ተቋም ነው፡፡ ተወልዶ ባደገበት ሀገር ይዞታውን አንሰራፍቶ ለጊዜው የዘለቀው ኘሮቴስታንቲዝም በሀገሩ ባይተዋር ሲሆን “ጅብ ባለወቁት ሀገር ቁርበት አንጥፉልኝ አለ” እንደሚባለው ወደ ድሃ ሀገሮች በመዝመት ባንድ እጁ ዳቦ በአንድ እጁ እርካሽ እምነቱን ይዞ ገባ፡፡ በዚህ እኩይ ተልዕኰ የተወረሩ በርካታ የአፍሪካ ሀገሮች ባሕላቸውን ትተው፣ ቋንቋቸውን እረስተው ዘመን አመጣሽ የሆነውን አዲስ እምነት ለመቀበል ተገደዋል፡፡

{gallery count=1 width=350 height=300 counter=1 links=0 alignment=center animation=3000}bogi{/gallery}

ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ሲኖዳ 3ኛ አረፉ፡፡

በተ/ሥላሴ ጸጋ ኪሮስ
የቅብጥ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን ፓትርያርክ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ሲኖዳ 3ኛ አረፉ፡፡
የቅብጥ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን ሊቀ ጳጳስና የቅዱስ ማርቆስ መንበር 117ኛ ፓትርያርክ ብፁዕ አቡነ ሲኖዳ ትናንት መጋቢት 8 ቀን 2004 ዓ.ም. አረፉ፡፡
ቢቢሲ የግብፅን ብሔራዊ የቴሌቪዥን ጣቢያ ጠቅሶ እንደዘገበው ቅዱስነታቸው በካንሰር ሕመም ምክንያት በ88 ዓመታቸው አርፈዋል፡፡
በሰሜናዊ ግብፅ፣ አስዩት ውስጥ ሐምሌ 27 ቀን 1915 ዓ.ም ሲወለዱ ናዚር ጋይድ የሚል መጠሪያ ከቤተሰባቸው የተሰጣቸው ቅዱስነታቸው፣  ቅስናን ሲቀበሉ አባ እንጦንስ ተብለው ይጠሩ የነበር ሲሆን አቡነ ሲኖዳ የተባሉት በ1955 ዓ.ም የክርስትና ትምህርት ኤጲስ ቆጶስ ተብለው በተሸሙበት ወቅት ነበር፡፡
ቅዱስነታቸው አቡነ ሲኖዳ የቅብጥ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን 117ኛ ፓትርያርክ ሆነው በወንጌላዊው ቅዱስ ማርቆስ መንበር ላይ የተሾሙት ከተአምር ሠሪው ፓትርያርክ ከብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ቄርሎስ 6ኛ በኋላ ኅዳር 4 ቀን በ1964 ዓ.ም ነበር፡፡፡
ቅዱስነታቸው ከ5ኛው ክፍለ ዘመን በኋላ የቲዎሎጂ ሴሚናሪ ዲን የሆኑ የመጀመሪያው ፓትርያርክ ሲሆኑ በአገልግሎት ዘመናቸው ከ3 የአሜሪካን እንዲሁም ከ1 የጀርመን ዩኒቨርስቲ የክብር ዶክትሬት ተቀብለዋል፡፡
ቅዱስነታቸው ሕይወታቸው የትሕርምት፣ የጸሎትና የአገልግሎት እንደነበር የሕይወት ታሪካቸውን የሚዘግቡ ድርሳናት የሚገልጹ ሲሆን ባለፉት 20 ዓመታት የዓለምን ሕዝብ ያስተማሩባቸው 80 መጻሕፍትን ደራሲና የቤተ ክርስቲያኗ ኦፊሴላዊ መጽሔት ኤል-ኬራዛ ዋና አዘጋጅ ነበሩ፡፡
በግብፅ ርዕሰ ብሔር አንዋር ሳዳት ጊዜ አክራሪ ሙስሊሞች በክርስቲያኖች ላይ የሚያደርሱት ጥቃት መጨመርና መፋፋም ያሳሰባቸው ቅዱስነታቸው በመንግሥቱ ላይ ባነሱት ተቃውሞ፣ ለ40 ወራት ከመንጋዎቻቸው ተለይተው ወደ ቅዱስ ቢሶይ ገዳም ተግዘው የአባቶቻቸውን በረከት ተካፍለው እንደነበር የሚታወቅ ሲሆን በኋለኛው መሪ ሆስኒ ሙባረክ ዘመን ወደ መንበራቸው ተመለሰው እስከ ዛሬ ድረስ ጠቦቶችን ሲጠብቁ፣ ግልገሎችና በጎችን ሲያሰማሩ ቆይተው አርፈዋል፡፡
በግብፅ ሕዝብ በተለይም በኦርቶዶክሳውያን ዘንድ ተወዳጅ አባት እንደሆኑ የሚነገርላቸው ቅዱስነታቸው በግብፃውያን ክርስቲያኖችና ሙስሊሞች መካከል ያለውን ግንኙነት ለማሻሻልና ሰላማዊ ለማድርግ ደከመኝ ሰለቸኝ ሳይሉ እንደደከሙ ይመሠከርላቸዋል፡፡
ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ሲኖዳ ኢትዮጵያን  ሁለት ጊዜ የጎበኙ ሲሆን ከመጀመሪያው ጉብኝታቸው 30 ዓመታት በኋላ በ2000 ዓ.ም ሚያዝያ ወር ላይ ያደረጉት ጉበኝት የቅርብ ጊዜ ትዝታ ነበር፡፡
ጸሎታቸው ከሁላችን ጋር ይሁን፣ ማኅበራችን ማኅበረ ቅዱሳን ለግብፃዉያን ወንድም እህቶቻችንና ቅዱስነታቸውን ለሚወዱ ሁሉ መጽናናትን ይመኛል፡፡
መጋቢት 9/2004 ዓ.ም.

በተ/ሥላሴ ጸጋ ኪሮስ

የቅብጥ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን ፓትርያርክ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ሲኖዳ 3ኛ ዐረፉ፡፡ የቤተ ክርስቲያኗ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳትና የቅዱስ ማርቆስ መንበር 117ኛ ፓትርያርክ የቅዱስነታቸው ዕረፍት የታወቀው ትናንት መጋቢት 8 ቀን 2004 ዓ.ም. ነበር፡፡

 

ቢቢሲ የግብፅን ብሔራዊ የቴሌቪዥን ጣቢያ ጠቅሶ እንደዘገበው ቅዱስነታቸው በካንሰር ሕመም ምክንያት በ88 ዓመታቸው ከዚህ ዓለም ድካም ዐርፈዋል፡፡
baba shenouda
በሰሜናዊ ግብፅ፣ አስዩት ውስጥ ሐምሌ 27 ቀን 1915 ዓ.ም ሲወለዱ ናዚር ጋይድ የሚል መጠሪያ ከቤተሰባቸው የተሰጣቸው ቅዱስነታቸው፣  ቅስናን ሲቀበሉ አባ እንጦንስ ተብለው ይጠሩ የነበር ሲሆን አቡነ ሲኖዳ የተባሉት በ1955 ዓ.ም የክርስትና ትምህርት ኤጲስ ቆጶስ ተብለው በተሸሙበት ወቅት ነበር፡፡ ቅዱስነታቸው አቡነ ሲኖዳ የቅብጥ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን 117ኛ ፓትርያርክ ሆነው በወንጌላዊው ቅዱስ ማርቆስ መንበር ላይ የተሾሙት ከተአምር ሠሪው ፓትርያርክ ከብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ቄርሎስ 6ኛ በኋላ ኅዳር 4 ቀን በ1964 ዓ.ም ነበር፡፡

የአብነት ትምህርት ቤት ለመደገፍ የግንባታና የቋሚ ገቢ ማስገኛ ፕሮጀክት ቀረበ

መጋቢት 7/2004 ዓ.ም.

በዳዊት ደስታ


በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የሰንበት ትምህርት ቤቶች ማደራጃ መምሪያ ማኅበረ ቅዱሳን የአዲስ አበባ ማእከል የማኅበራዊ አገልግሎትና ልማት ክፍል በሰሜን ሸዋ ሰላሌ ፍቼ ሀገረ ስብከት፣ በሰንዳፋ አዳማ በበኬ ደብረ ምሕረት ቅድስተ ማርያም ቤተ ክርስቲያን የሚገጥመን የአብነት ትምህርት ቤት ለመደገፍ የግንባታና የቋሚ ገቢ ማስገኛ ፕሮጀክት ዕቅድ ከባለድርሻ አካላት ጋር የካቲት 18 ቀን 2004 ዓ.ም. በደብሩ የስብከተ ወንጌል አዳራሽ ቀረበ፡፡

የዐቢይ ጾም ስብክት (ክፍል 5)

መጋቢት 7/2004 ዓ.ም.

በአያሌው ዘኢየሱስ

 

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ፤

 

የዐቢይ ጾም አምስተኛ ሳምንት ሰንበት «ደብረ ዘይት» ተብሎ ይጠራል፡፡ ደብረ ዘይት ከኢየሩሳሌም በስተ ምሥራቅ የሚገኝ ተራራ ነው፡፡ ተራራው በዚህ ስም የሚጠራው ለዘይት የሚሆን የወይራ ተክል በብዛት ስለሚበቅልበት ነው፡፡ ጌታችን ቀን ሲያስተምር ውሎ በደብረ ዘይት ያድር ነበር፡፡ ለደቀ መዛሙርቱም ለሕዝቡ በምሳሌ ያስተማረውን ይተረጉምላቸው ነበር፡፡ የዓለም ፍጻሜና የዳግም ምጽአቱን ምልክት ለደቀ መዛሙርቱ ያስተማራቸው በዚሁ ተራራ ላይ ነውና የጌታን ዳግም ምጽአት የምናስብበት አምስተኛው የዐቢይ ጾም ሰንበት ስሙን ከተራራው ወስዷል ማለት ነው፡፡ ደብረ ዘይት በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ምዕመናን ዘንድ «እኩለ ጾም» ተብሎ ይጠራል፡፡ በዚህ ስያሜ የሚጠራውም የጾሙ ሳምንታት አጋማሽ ወይም እኩሌታ ስለሆነ ነው፡፡ አንዳንድ የቤተ ክርስቲያን አባቶች መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በዕለተ እሑድ፣  የደብረ ዘይት ዕለት ይመጣል ብለው ስለሚያስተምሩ በዚህ ሰንበት የሚበዙት ምዕመናን ዕለቱን በታላቅ ዝግጅት ማለትም በንስሓና በቅዱስ ቁርባን ይቀበሉታል፡፡ በዚህ ዕለት የሚሰበከው ምስባክ፣ የሚሰጠው የወንጌል ትምህርትና የሚነበቡት የሐዋርያት ሥራና የመልእክታት ንባባት በሙሉ የጌታችንን የኢየሱስ ክርስቶስን ሁለተኛ አመጣጥ የሚናገሩ ናቸው፡፡

ደብረ ዘይት(ለሕጻናት)

መጋቢት 06/2004ዓ.ም

በቴዎድሮስ እሸቱ

 

5debrezeit

ልጆች እንኳን ለጾመ እኩሌታው /ለደብረ ዘይት/ በሰላም አደረሳችሁ፡፡ ይህ አምስተኛው ሳምንት ደብረ ዘይት ይባላል፡፡ የጾሙ እኩሌታ በመሆኑ በቤተ ክርስቲያናችን ታላቅ በዓል ነው፡፡ ልጆች በዚህ ቀን ጌታ በደብረ ዘይት ስለዳግም ምጽአቱ ያስተማረው ትምህርት ይነገራል፡፡ ጌታ ይህን ዓለም ለማሳለፍ ለሁሉም እንደየሥራው ለመክፈል፣ በግርማ መንግሥቱ ይመጣል፡፡