የዝቋላ ደብረ ከዋክብት አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ገዳም ደን እየተቃጠለ ነው፤ የምእመናንን እገዛ ይሻል፡፡

መጋቢት 10/2004 ዓ.ም.


በተ/ሥላሴ ጸጋ ኪሮስ


ቅዳሜ መጋቢት 8 ቀን 2004 ዓ.ም ከቀኑ 6፡00 በኋላ የጀመረው የገዳሙ ቃጠሎ እየተባባሰ እንደሆነ የገለጹልን ያነጋገርናቸው የገዳሙ መነኮሳት እሳቱን ለማጥፋት የምእመናንን እርዳታ እንደሚሻ አሳስበዋል፡፡

 

አያይዘውም ለእርዳታ የሚመጡ ምእመናን ስንቅ እንዲይዙና በውኃ ጥም እንዳይቸገሩ ከቻሉ ውኃ እንዲይዙ፤ ቦቴ መኪና ያላቸውም እንዲተባበሩ ጠይቀዋል፡፡

 

በአሁኑ ወቅት ምእመናን ከደብረ ዘይትና አዲስ አበባ ዙሪያ ወደ ገዳሙ ለእርዳታ እየተጓዙ እንደሆነ ያገኘናቸው መረጃዎች ያመለክታሉ፡፡

 

ዝርዝር ሁኔታውን በቀጣዩ እናቀርባለን፡፡

አምላከ ገብረ መንፈስ ቅዱስ በምሕረቱ ይታረቀን፡፡