ሥርዓተ ንባብ
ውድ አንባብያን ባለፈው ትምህርታችን ስለወዳቂ ንባብ መጻፋችንና ከላይ የቀረበውን ምንባብ መሠረት በማድረግ የግንዛቤ ማስጨበጫ ጥያቄዎችንም ማቅረባችን ይታወቃል። መልሱን እንደሚከተለው እናቅርብና ወደሚቀጥለው ትምህርት እናመራለን።
This author has not written his bio yet.
But we are proud to say that Mahibere Kidusan contributed 977 entries already.
ውድ አንባብያን ባለፈው ትምህርታችን ስለወዳቂ ንባብ መጻፋችንና ከላይ የቀረበውን ምንባብ መሠረት በማድረግ የግንዛቤ ማስጨበጫ ጥያቄዎችንም ማቅረባችን ይታወቃል። መልሱን እንደሚከተለው እናቅርብና ወደሚቀጥለው ትምህርት እናመራለን።
«እምነትስ፣ ተስፋ ስለምናደርገው ነገር የምታረጋግጥ፥ የማናየውንም ነገር የምታስረዳ ናት» (ዕብ. ፲፩፥፩) እንደተባለው ሰው ተስፋን ከአምነት ያገኛል፡፡ አዳም ቢበድልም እንኳን ቸሩ አምላክ እግዚአብሔር በኋላ ዘመን ከልጅ ልጁ ተወልዶ እንደሚያድነው ቃል በጋባለት ጊዜ ተስፋ አግኝቷል፡፡ የመዳኑን ነገር በእምነቱ ተስፋ ሆነለት፡፡ እምነት ለእግዚአብሔር ያለንን ፍቅር የምንገልጥበት፣ እርሱን ደስ የምናሰኝበት የሕይወት መሠረት ነው፡፡ ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ ይህን ሲያስረዳ «ያለ እምነትም እግዚአብሔርን ደስ ማሰኘት አይቻልም» ብሏል፡፡ (ዕብ.፲፩፥፮)
እግዚአብሔርን በመፍራት መኖር ሲገባ በየዕለት ተግባራችን በአዕምሮአችን ክፋት በማሰብና ተንኮል ለመሥራት በመሻት፣ ከሰብአዊነት ይልቅ ጭካኔ በልባችን ሞልቶ ጥቅምን በማስበለጥ ኃጢአትንና ክፋትና እየሠራን አንውላን፡፡ ፈሪሀ እግዚአብሔር የሌላቸው ሰዎች ፈጣሪን ስለሚረሱ ባዕድነትን ይላመዳሉ፤ ግብዝም ይሆናሉ፤ ይህም ማንነታቸውን አስለውጦ ወደ ርኩስነት ይለውጣቸዋል፡፡ መጥፎ መንፈስ በውስጣቸው በሚገባበትም ጊዜ መንፈስ ቅዱስ ስለሚርቃቸው ጥሩውን በመጥላት ክፋትን ይወዳሉ፤ በመጥፎነታቸውም ይመካሉ፡፡ እግዚአብሔር አምላክን መዳፈር ይጀምራሉ፤ ሕጉን በተላለፉና ሥርዓቱን በጣሱ ቁጥርም በዓለማዊ ኑሮአቸው፣ በአምልኮት እና በተቀደሱ ሥፍራዎች ጭምር ኃጢአትን ይፈጽማሉ፡፡ ይህም አምላክን ያስቆጣል፤ ለመቅሰፍትም ይዳርጋል፤ ለመርገምና ለመከራ አሳልፎ ይሰጣል፤ በአገልግሎት፣ በክርስትናና በመንፈሳዊ ሕይወትም ዝለትን፤ በሃይማኖትና በምግባር ጉድለትን ያመጣል፤ ከእግዚአብሔር መንግሥት ይለያል፤ ለዘላለም ሞትም አሳልፎ ይሰጣል፡፡ ለዚህ ነው መጽሐፍ ቅዱስ ‹‹የኃጢአት ደመወዝ ሞት ነው›› የሚለን (ሮሜ.፮፥፳፫)
በዘመነ ሥጋዌ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ከናዝሬት ወደ ቅፍርናሆም በሔደ ጊዜ የገሊላ፣ የኢየሩሳሌም፣ የይሁዳ እና የዮርዳኖስ ሕዝብ ዝናውን ሰምተው ወደ እርሱ መጡ፡፡ በዚያም የመንግሥቱንም ወንጌል ሲሰብክ ‹‹……ልበ ንጹሐን ብፁዓን ናቸው፤ እግዚአብሔርን ያዩታልና…….ደስ ይበላችሁ፤ሐሤትንም አድርጉ፤ ዋጋችሁ በሰማያት ብዙ ነውና፤ ከእናንተ አስቀድሞ የነበሩ ነቢያትንም እንዲሁ አሳድደዋቸው ነበርና›› ብሎ አስተማራቸው፡፡ (ማቴ.፭፥፩-፲፪)
የወይራ ተራራው ደብረ ዘይት ምሥጢር የሚነገርበት እና የወይራ ፍሬ ምሥጢራት የሚፈጸሙበት ስለነበር ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በዚያ ይገኝ ነበር። ደቀ መዛሙርቱም ለብቻቸው ወደ እርሱ ቀርበው ስለዳግም ምጽአት «የዓለሙ ፍጻሜስ ምልክቱ ምንድነው?» ሲሉ ጠየቁት። (ማቴ.፳፬፥፫) እርሱም አስቀድሞ «ማንም እንዳያስታችሁ ተጠንቀቁ» አላቸው፤
ከጥንት ጀምሮ ዓለም በእንደዚህ ዓይነት በሽታ ስትጠቃ እንደቆየች ታሪክ ምስክር ነው፤ እንደ ኤች.አይ.ቪ ኤድስ ቫይረስና የቅርብ ጊዜ ክስተት የሆኑት ኢቦላና ሳርስ በሽታዎች ሰዎችን በተለያዩ መንገድ በመያዝና በማሠቃየት ለሞት ዳርገዋል፡፡ ሀገራችን ኢትዮጵያም ከተጠቁት የዓለም ክፍላት ውስጥ አንዷ ናት፤ በኤች.አይ.ቪ ኤድስ ሺዎችን አጥታለች፤ አሁንም እንደ ሰደድ እሳት እየተዛመተ ያለው ኮሮና ቫይረስ ዋና ከተማዋ አዲስ አበባ እንደገባ ምንጮች የሕክምና ማስረጃ ምንጮ ይፋ አድርገዋል፡፡
በዓለም ዙሩያ በሕክምናው ዘርፍ ያሉ ባለሙያዎች ለበሽታው መድኃኒት በማጣታቸው መንግሥታት ለዜጎቻቸው ቅድመ ጥንቃቄ እንዲያደርጉ አስጠንቅቀዋል፤ መከላከያ ሊሆኑ ይችላሉ የሚሏቸውን መንገዶች አስታውቀዋል፡፡
ነገር ግን ቤተክርስቲያናችን ሰዎች በክፉ ደዌ ሲያዙ ፈውሰ ሥጋን የሚያገኙት በጸበል፤ በጾምና በጾሎት እንደሆነ ታስተምራለች፤ እንደነዚህ ዓይነቱ ተዛማች በሽታም የእግዚአብሔር ቁጣ መሆኑን ታስረዳለች፡፡ ልበ አምላክ ዳዊትም በመዝሙሩ ‹‹አቤቱ÷ በመዓትህ አትቅሠፈኝ÷ በመቅሰፍትህም አትገሥጸኝ›› ሲል አምላኩን ተማጽኗል፡፡ (መዝ. ፴፯፥፩)
ቅድስት ዕሌኒም መስከረም ፲፯ ቀን ቁፋሮ እንዲጀመር አዘዘች፡፡ ቁፋሮውም ሰባት ወር ያህል ከፈጀ በኋላ መጋቢት ፲ ቀን ሦስት መስቀሎች በአንድነት ተገኙ፡፡ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የተሰቀለበትን መስቀል መለየት ግን አልተቻለም ነበር፡፡ ስለዚህም ሦስቱን መስቀሎች ወደ ሞተ ሰው በመውሰድ በተራ በተራ አስቀመጧቸው፤ ያን ጊዜ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የተሰቀለበት መስቀል የሞተውን ሰው በማስነሳቱ መስቀሉ ተለየ፤ ተአምሩም ተገለጸ፡፡ ቅድስት ዕሌኒና መላው ክርስቲያን ለመስቀሉ ሰገዱለት፡፡
በዚህ ዓመት ታኅሣሥ ወር ፳፬ ቀን ጸጥታ አስከባሪዎች በሁለት ወጣት ኦርቶዶክሳውያን ላይ በግፍ የገደሉትን ስፍራ የ ‹‹፳፬ ቀበሌ›› ወደ ቀደመ ክብሩ ተመልሶ ሕንጻ ቤተክርስቲያን እንዲሠራበት በተላለፈው ውሳኔ መሠረት ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ፓትርያክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት በተገኙበት መጋቢት ፮ ፳፻፲፪ ዓ.ም. የመሠረት ድንጋይ ተጥሏል፡፡
ቤተ ክርስቲያናችን ሁሉንም በሥርዓት የምታከናውን ስንዱ እመቤት ናትና በዐቢይ ጾም ከሚገኙት ሰንበታት ውስጥ ዐራተኛውን ሰንበት መጻጉዕ ብላ ሰይማዋለች፡፡ አምላካችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ብንወድቅ እንደሚያነሣን፣ ብንታመም እንደሚፈውሰን ለማስተማር፣ እንዲሁም ደግሞ ከመጻጉዕ ሕይወት እንማር ዘንድ መታሰቢያውን አደረገች፡፡ “ዳግመኛ እንዳትበድል ተጠንቀቅ” እንዳለ ከኃጢአት ወደ ጽድቅ፣ ከሞት ወደ ሕይወት፣ እንሸጋገር ዘንድ፣ የአምላካችንን ቃል መፈጸም እንደሚገባን፣ እሰከ ሞትም መታመን እንዳለብን ያስተምረናል፡፡