Entries by Mahibere Kidusan

‹‹በንስሓ ተመለሱና በሕይወት ኑሩ›› (ሕዝ.፲፰፥፴፪)

ዓለም ኃጢአተኝቱን ላለማመን ይህንን የመጣብንን መቅሠፍት (ኮሮና ቫይረስ) ‹‹እንዲህ የምትባል ሀገር ናት ያመረተችው፤ ከእንትና ቤተ ሙከራ አፈትልኮ የወጣ ቫይረስ ነው፤›› በማለት የተለያዩ የሽፍጥ ምክንያቶችን ትደረድራለች፡፡ ይሁን እንጂ ማንም ምንም ቢል እውነታው ግን ‹‹የኃጢአት ደመወዝ ሞት ነው›› ተብሎ እንደተጻፈ የሰው ልጅ የኃጢአት ደመወዙን ከእግዚአብሔር እጅ እየተቀበለ ነው፡፡ (ሮሜ.፮፥፳፫)

“ዐርገ ሰማያተ በዐምደ ደመና፤ በደመና ወደሰማይ ዐረገ” (ቅዱስ ያሬድ)

ጌታችን ኢየሱስ በደመና ዐረገ መባሉ ሊቃውንት እንደሚነግሩን ደመና ክብሩና ልዕልናው በመሆኑ ነው። “ዘበእንተ ዕበይከ ትትሜሰል በደመና፤ ስለ ልዕልናህ በደመናት ትመሰላለህ” እያሉ ሊቃውንቱ ያመሰግኑታል። በሐዋርያት ሥራም “ወነሥአቶ ደመና ወዐርገ ሰማየ እንዘ እሙንቱ ይኔጽሩ ኀቤሁ፤ ደመናም ተቀበለችው፤ እነርሱም ወደእርሱ እያዩ ወደሰማይ ዐረገ” ተብሎ ተጽፏል። ነቢየ እግዚአብሔር ቅዱስ ዳዊትም “ዐርገ እግዚአብሔር በይባቤ ወእግዚእነ በቃለ ቀርን፤ እግዚአብሔር በዕልልታ ጌታችንም በመለከት ድምፅ ዐረገ” በማለት እንደነገረን በክብር በይባቤ መላእክት ማረጉን ያስረዳል። (ሐዋ.፩፥፱፤ መዝ.፵፮፥፭)

‹‹እምነትም ተስፋ ስለምናደርገው ነገር የሚያስረግጥ፥ የማናየውንም ነገር የሚያስረዳ ነው›› (ዕብ. ፲፩፥፩)

ማንኛውም የሕይወት ውጣ ውረድ ቢያጋጥመን በእምነት ከጸናን የማናልፈው ነገር የለም፡፡ የማንዘለው የችግር እና የመከራ ግንብ፣ የማንሻገረው ባሕር እና መሰናክል አይኖርም፡፡ ነቢየ እግዚአብሔር ቅዱስ ዳዊት በእምነት ከእግዚአብሔር ጋር ከኖርን የሚያስፈራን አንዳች ነገር አለመኖሩን ሲያስረዳ ‹‹በሞት ጥላ መካከል እንኳን ብሔድ፤ አንተ ከእኔ ጋር ነህና ክፉን አልፈራም፤ በትርህና ምርኩዝህ እነርሱ ያጽናኑኛል›› ብሏል፡፡ (መዝ. ፳፪፥፬)

‹‹ድኀነት››

የሰው ልጅ በኃጢአት ምክንያት ያጣውን የተፈጥሮ ጸጋ ክብር በአዲስ ተፈጥሮ እንደገና ለመታደል መብቃቱን ለመግለጽ የሚነገር ልዑል ቃል ‹‹ድኀነት›› ነው፡፡ ድኀነት የሚለው ቃል አዳም በክርስቶስ የታደለውን የሕይወተ ሥጋና ሕይወት ነፍስ፣ በረከተ ሥጋና በረከተ ነፍስ ጸጋ ወይም በሌላ አነጋገር የሞተ ሥጋና የሞተ ነፍስ ድቀት የደረሰበት አዳም በክርስቶስ ኢየሱስ ያገኘው ትንሣኤውና ሕይወት የሚገለጽበት ሕያው ቃል ነው፡፡

‹‹የሱራፌል አምሳላቸው ቅዱስ ያሬድ››

እግዚአብሔር አምላክን ‹‹ቅዱስ ቅዱስ ቅዱስ›› እያሉ በመንበሩ ፊት ቆመው እንደሚያመሰግኑ ሁሉ ኢትዮጵያዊ ማኅሌታይ ቅዱስ ያሬድ ‹‹ቅዱስ ቅዱስ ቅዱስ›› እያለ በመላእክት ቋንቋ ፈጣሪውን በማመስገኑ እና ዜማውን ከእነርሱ በመማሩ በመጽሐፈ ስንክሳር ‹‹አምሳሊሆሙ ለሱራፌል፤ የሱራፌል አምሳላቸው›› ተብሏል፡፡

“ደኅንነት ከእግዚአብሔር ዘንድ ነው” (ትንቢተ ዮናስ ፪፥፲)

እግዚአብሔር ከበሽታ ይፈውሳል፤ ከችግርና መከራም ይሰውራል፡፡ በየጸበል ቦታው ተጠምቀው ከኤች አይ ቪ፣ ከካንሰር እና ከሌሎች በሽታዎች የተፈወሱ ሰዎች እንዳሉ ዓይናችን እንዲሁም የሕክምና ማስረጃዎች ምስክሮች ናቸው፡፡ እግዚአብሔር ኃያል አምላክ፤ ሥራውም ድንቅ ነው፤ ተአምራትንም ያደርጋል፡፡ ነገር ግን ድኅነተ ሥጋንም ሆነ ድኅነተ ነፍስን ከእርሱ ለማግኘት እምነት ያስፈልጋል፡፡

“በመከራዬ ሳለሁ ወደ አምላኬ ወደ እግዚአብሔር ጮኽሁ” (ትንቢተ ዮናስ ፪፥፫)

በመጀመሪያ ራሳችን “በደለኛው እኔ ነኝ፤ ኃጢአተኛ ነኝ፤” ብለን አምነን መጸጸት አለብን፤ ጸጸትም ወደ ንስሓ ይመራናል፡፡ እግዚአብሔር ልብንና ኩላሊትን የሚመረምር አምላክ ነውና ውስጣችንን ከክፋት ሳናነጻ በሐሰተኛ አንደበት በንጸልይና ምሕረትን ብንለመን ልመናችንን አይቀበለንም፤ ሁሌም እርሱን በመፍራት መኖር እንዳለብን ቃሉ ይገልጻል፤ “ነገር ግን ቀኑን ሙሉ እግዚአብሔርን በመፍራት ኑር” (መጽሐፈ ምሳሌ ፳፫፥፲፯) እንደተባለው እግዚአብሔርን አምላክን በንጹሕ ልቡና ልንማጸን ይገባል፡፡

“የክርስቶስን ሕግ ፈጽሙ” (ገላ. ፮፥፪)

የክርስቶስ ሕግ ፍጻሜ ፍቅር ነው። ፍቅር አንድ ሰው ከሌላው ጋር በየዕለቱ የሚያደርገው ግንኙነት፣ በመተሳሰብ ላይ የተመሠረተ ልባዊ መዋደድና ጥልቅ መንፈሳዊ ጸጋ ነው። በሰዎች መካከል በሚኖረው መልካም ግንኙነት የተነሳ አንዱ ለሌላው የሚያደርገው መልካም ነገር ሁሉ ፍቅር ነው።