ዝርዝር ርባታ
የተወደዳችሁ አንባብያን! እንደምን ሰነበታችሁ? የእግዚአብሔር አምላካችን ስም የተመሰገነ ይሁን! በተከታታይ በሁለት ክፍል የግሥ ዝርዝር ርባታ እንዳቀረብንላችሁ ይታወቃል፤ በዚህ የትምህርት ክፍለ ጊዜያችን ደግሞ የመጨረሻውን ክፍል ይዘንላችሁ ቀርበናል፤ በጥሞና ተከታተሉን!
This author has not written his bio yet.
But we are proud to say that Mahibere Kidusan contributed 1043 entries already.
የተወደዳችሁ አንባብያን! እንደምን ሰነበታችሁ? የእግዚአብሔር አምላካችን ስም የተመሰገነ ይሁን! በተከታታይ በሁለት ክፍል የግሥ ዝርዝር ርባታ እንዳቀረብንላችሁ ይታወቃል፤ በዚህ የትምህርት ክፍለ ጊዜያችን ደግሞ የመጨረሻውን ክፍል ይዘንላችሁ ቀርበናል፤ በጥሞና ተከታተሉን!
ለዓለም ሁሉ ድኅነት መድኃኒዓለም ኢየሱስ ክርስቶስ መጋቢት በባተ በ፳፯ኛው ቀን በመስቀል ላይ ተሰቀለ፡፡ በክርስቶስ ክርስቲያን የተባልን ልጆቹም ይህን እናዘክር ዘንድ ዓይን ልቡናችንን ወደ ቀራንዮ እናንሣ!
በጎ አገልጋይ ለጌታው ታምኝ እንደመሆኑ ‹‹ገብር ኄር›› ይባላል፡፡ ይህም ስያሜ ለዐቢይ ጾም ስድስተኛ ሳምንት እንደተሰጠ የቤተ ክርስቲያን አስተምህሮ ይገልጻል፡፡ የስያሜው መነሻ የሚገኘው ደግሞ በዕለቱ ሥርዓተ ቅዳሴ ከሚነበበው በማቴዎስ ወንጌል ክፍል ነው፡፡ (ማቴ.፳፭፥፲፬-፴)
የዓለም መድኃኒት አምላካችን ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ዘንባባና ልብስ ተነጥፎለት በአህያ ውርንጭላዋ ተጭኖ ቤተ መቅደስ የገባበት ዕለት ‹‹ጥንተ ሆሣዕና›› በቅድስት ቤተ ክርስቲያናችን ይዘከራል፡፡ ሆሣዕና ማለት ‹‹አሁን አድን›› ማለት ነው፤ (ማሕቶተ ዘመን ገጽ ፻፷)
ከኢየሩሳሌም በስተምሥራቅ የሚገኝ ቦታ የሚገኘው ተራራ ደብረ ዘይት የጸሎተ ሐሙስ ማታ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የተያዘበት ነው፡፡ ቤተ ፋጌ እና ቢታንያ በኮረብታው ጫፍ እና በምሥራቅ ዳገት ላይ ይገኛሉ። ጌታችን ኢየሱስ ስለ ቤተ መቅደሱ መፍረስ፣ ስለ ዓለም ፍጻሜና ስለ ዳግም ምጽአት በዚህ ተራራ ላይ ተናገሯል።
ውድ አንባብያን! እንደምን ሰነበታችሁ? የእግዚአብሔር አምላካችን ስም የተመሰገነ ይሁን! ባለፈው የትምህርታችን ክፍለ ጊዜ የግሥ ርባታ የመጀመሪያውን ክፍል አቅርበንላችኋል፤ እንደተረዳችሁት ተስፋ እንዳርጋለን፤ ለዛሬ ደግሞ ሁለተኛውን ክፍል እንደሚከተለው አቅርበንላችኋል፤ በጥሞና ተከታተሉን!
ውድ የእግዚአብሔር ልጆች! እንዴት አላችሁ?! የጾምን ወቅት እንዴት እያሳለፋችሁት ነው? አባቶቻችን ሊቃውንት ስለ ጾም እንዲህ ይላሉ፤ ጾም ማለት ከምግብና ከውኃ መከልከል ብቻ ሳይሆን ከክፉ ሥራም መታቀብ (መከልከል) ነው፤ ጾም የጽድቅ በር ናት፤ ጾም ለመልካም ነገር የምታነሣሣን ናት፡፡
ውድ እግዚአብሔር ልጆች! ከጸሎትና ከስግደት ጋር እንዲሁም ትምህርት በማይኖረን በዕረፍት ጊዜያችን ደግሞ ቤተ ክርስቲያን በመሄድ በማስቀደስ፣ ታዛዦች በመሆን የጾሙን ጊዜ ልናሳልፍ ይገባል፡፡ መልካም!
ባለፈው የትምህርት ክፍለ ጊዜ ስለ ዐቢይ ጾምና በጾሙ ወቅት ስላሉት ሳምንታት እስከ እኩለ ጾም ድረስ ተመልክተናል፤ ለዛሬ ደግሞ ቀጥሎ ያለውን እንመለከታለን፤ መልካም ንባብ!!!
ለሠላሳ ስምንት ዓመታት በደዌ ዳኛ በአልጋ ቁራኛ ተይዞ የነበረው አንድ በሽተኛ ሰው በጌታችን ቃል ተፈውሶና አልጋውን ተሸክሞ ወደ ቤቱ መሄዱ በቅዱስ መጽሐፍ ተመዝግቧል፡፡
የክብር ባለቤት ጌታችን አምላካችንና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የተሰቀለበት መስቀል የተገለጠበትና የተገኘበት መጋቢት ፲ ግማደ መስቀሉን የምንዘክርበት ዕለት ነው። የዚህም የከበረ ዕፀ መስቀል መገለጡና መገኘቱ ሁለት ጊዜ ሆኗል። መጀመሪያ የጻድቁ ንጉሥ የቈስጠንጢኖስ እናት በሆነች በንግሥት ዕሌኒ እጅ ነው።
ቤተ መቅደስ ከሁለት ጥምር ቃላት የተገኘ ትርጓሜው ‹የተቀደሰ ቤት› የሚል ሲሆን ይህም የእግዚአብሔር አምላካችን ማደሪያ ወይም ቤት ነው፤ ቤተ መቅደስን የሚወክሉ አካላትም ሦስት ናቸው፡፡
