ቃና ዘገሊላ
በቃና ዘገሊላ ወይም በገሊላዋ ቃና ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የፈጸመውን ተአምር በማሰብ ቅድስት ቤተ ክርስቲያናችን በዓል ታከብራለች፡፡ ይህም በጥምቀት በዓል ማግስት በጥር ፲፪ ነው፡፡
This author has not written his bio yet.
But we are proud to say that Mahibere Kidusan contributed 818 entries already.
በቃና ዘገሊላ ወይም በገሊላዋ ቃና ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የፈጸመውን ተአምር በማሰብ ቅድስት ቤተ ክርስቲያናችን በዓል ታከብራለች፡፡ ይህም በጥምቀት በዓል ማግስት በጥር ፲፪ ነው፡፡
በአዳምና በሔዋን በደል ምክንያት ልጅነታችንን በማጣታችን፣ ሰውን ወደ ቀደመ ክብሩ ሊመልሰው እግዚአብሔር ወልድ ከሰማያት ወርዶ፣ ከንጽሕት ቅድስት ድንግል ማርያም ተወልዶ፣ ድኅነትን ሊፈጽም ከጀመረባቸው አንዱ እና ዋነኛው የክርስትናችን መግቢያ በር ጥምቀት ነው፡፡
ውድ አንባብያን! እንደምን ሰነበታችሁ? ከዚህ ቀደም ከክፍል አንድ እስከ ክፍል ሦስት ድረስ ስለ መልካም አስተዳደር፣ የመልካም አስተዳደር እጦት በቤተ ክርስቲያን እና ያስከተለው ጉዳት ወይም ተጽእኖ በጥቂቱ አስነብበናችኋል፡፡ በዚህ በመጨረሻው ክፍል አራት ደግሞ የመልካም አስተዳደር መስፈን የሚያስገኛቸውን ጥቅሞችን በከፊል ይዘንላችሁ ቀርበናል፤ መልካም ንባብ!
አጋእዝተ ዓለም ሥላሴ በኃጢአት የተገነባውን የሰናዖር ግንብ ያፈረሱበት አንድነታቸውንና ሦስትነታቸውን በግልጽ ያሳዩበት ጥር ሰባት ቀን የከበረ በዓል እንደመሆኑ በቤተ ክርስቲያናችን በድምቀት ይከበራል፡፡
በቤተ ክርስቲያናችን አስተምህሮ ከጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ከርስቶስ ዘጠኙ ንዑሳን በዓላት አንዱና የመጀመሪው ሲሆን ይህም ግዝረተ ክርስቶስ ይባላል። በቅዱስ ሉቃስ ወንጌል እንደተጻፈው “ሊገርዙት ስምንት ቀን በሞላ ጊዜ፥ በማኅፀን ሳይረገዝ በመልአኩ እንደ ተባለ፥ ስሙ ኢየሱስ ተብሎ ተጠራ። እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያምም ወደ ግዘረት ቤት ወሰደችው፤ ገራዡ ምላጩን ይዞ ቀረበ፤ ነገር ግን ምላጩ እጁ ላይ ሳላ ውኃ ሆኖ ፈሰሰ። ጌታችንም በተአምራት የተገረዘ ሆኖ ተገኘ፡፡” (ሉቃ.፩፥፳፩)
አባታችን አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ሀገራቸው ንሂሳ ግብጽ ነው፡፡መላው ሕይወታቸውንም በምድረ በዳ የኖሩ አባት ናቸው፤ በዝቋላ ተራራ ባለው ባሕር ውስጥ ፻ (መቶ) ዓመት ተዘቅዝቀው ለኢትዮጵያውያን ምሕረትን በመለመን ለብዙዎች ድኅነት የሆኑ ታላቁ አባታችን አቡነ ገብረ መንፈስ የተወለዱት ታኅሣሥ ፳፱ ቀን ቢሆንም በጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ልደት በዓል ምክንያት ሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያን በሠሩልን ሥርዓት መሠረት ጥር ፭ በድምቀት እናከብራለን፡፡
ቁጣ የሚጫር የእሳት ክብሪት ማለት ነው፡፡ እሳት አንድ ጊዜ በክብሪት ከተጫረች በኋላ ሰደድ እሳት ትሆናለች፡፡ በቁጣ ሁሉም የኃጢአት ዓይነቶች ከመዛግብቶቻቸው ወጥተው ይቀጣጠላሉ፡፡ አንድን ሰው ድንገት አንድ ቁጡ ሰው ተነሥቶ ክፉ ቢናገረውና በይቅር ባይነት መንፈስ ቢያልፈው እንኳን ያ ቁጡ ሰው ቀኑን ሙሉ በቁጣ ላይ ሠልጥኖ ይውላል።
ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአኵስም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ በዓለ ልደትን አስመልክቶ ለመንፈስ ቅዱስ ልጆቻቸው ያስተላለፉት መልእክት።
ኧረ ይህች ቀን ምንኛ ድንቅ ናት!
በዓይን የማይታየው የተገለጠባት
የማይዳሰሰው በአካል የተገኘባት
አንድ አምላክ ፈጣሪ የተወለደባት
እርሱ ነው ተስፋችን የዓለም መድኃኒት
የሆነው ቤዛ ለሁሉ ፍጥረት!
ወልድ ተወለደልን መድኃኒዓለም
በከብቶች በረት በቤተ ልሔም!
ውድ የእግዚአብሔር ልጆች! እንዴት አላችሁልን! ትምህርት እንዴት ነው? አሁንማ ፈተና ደርሷል አይደል ልጆች? ስለዚህ ጨዋታ ሳያታልላችሁ በትኩረት በማጥናት፣ ያልተረዳችሁትን በመጠየቅ፣ የግማሽ ዓመት ፈተናውን በጥሩ ውጠየት ለማለፍ ማቀድ አለባችሁ!
ታዲያ በቀደሙት ትምህርታችን ስለ ጾመ ነቢያትና ስለ ነቢያት አባቶቻችን ስንማማር ነበር፤ አሁን ደግሞ የጌታችን መድኃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ የልደት በዓል እናከብራለን፤