አጠንተ መንበሩ!
አልፋና ኦሜጋ የሆነው አምላካችን ቅድመ ዓለም አስቀድሞ ሲለሠስ ሲቀደስ እንደኖረ ሁሉ ድኅረ ዓለም በፍጥረታቱ ሁሉ ሲመሰገን፣ ሲቀደስና ሲከበር ይኖራል፡፡ ስሙን ለመቀደስ ክብሩን ለመውረስ የፈጠራቸው መላእክትና ሰውም ይህን ግብር የሚሠሩ ቀደምት ፍጥረታት ናቸው፡፡ (መጽሐፈ አክሲማሮስ ዘእሑድ)
This author has not written his bio yet.
But we are proud to say that Mahibere Kidusan contributed 1057 entries already.
አልፋና ኦሜጋ የሆነው አምላካችን ቅድመ ዓለም አስቀድሞ ሲለሠስ ሲቀደስ እንደኖረ ሁሉ ድኅረ ዓለም በፍጥረታቱ ሁሉ ሲመሰገን፣ ሲቀደስና ሲከበር ይኖራል፡፡ ስሙን ለመቀደስ ክብሩን ለመውረስ የፈጠራቸው መላእክትና ሰውም ይህን ግብር የሚሠሩ ቀደምት ፍጥረታት ናቸው፡፡ (መጽሐፈ አክሲማሮስ ዘእሑድ)
ጽዮን “”ጸወን” ከሚለው የግእዝ ቃል የተገኘ ሲሆን “አምባ፣ መጠጊያ” ማለት ነው፡፡ እመ ብዙኀን የሆነችውን የአምላክ እናት ቅድስት ድንግል ማርያምን የሚገለጽ መሆኑን “ማኅደረ አምላክ” በሚለው ትርጒም እንረዳለን፡፡ ጽዮን የሚለው ስያሜ በቁሙ ለታቦት፣ ለጽላት ሲያገለግል በትንቢታዊ ምሥጢሩ ግን ለድንግል ማርያም፣ ለቤተ ክርስቲያንና ለዘለዓለማዊት ርስተ መንግሥተ ሰማያት ያገለግላል::
የማንነት ጥያቄ በሁላችንም አእምሮ ውስጥ የሚታሰብ ነው፤ ምላሽ አግኝተን የተሻለ መረዳት ያለን ስንቶቻችን እንደሆንን ማወቅ አዳጋች ቢሆንም በዘመናት ሂደት በሰዎች ታሪክ ውስጥ ካካበትነው ዕውቀት አልያም ደግሞ ባሳለፍነው ተሞክሮ የተወሰነ መረዳት ሊኖረን እንደሚችል መገመት አያዳግትም፡፡ በተለይም የአምላክን ቅዱስ ቃል ተምረን የምናውቅበት የቤተ ክርስቲያን አስተምህሮ በመጠኑ እንኳን ካለን የመፈጠራችን ምክንያት ወይም የመኖራችን ትርጒም ይገባናል፡፡
የአዳም ዘር በሙሉ በኃጢአት ባርነት ተይዞ፣ ለ፶፻፭፻ ዓመታት በፍዳ አረንቋ ውስጥ ሲኖር ተስፋ ሲያደርግ የነበረው የእግዚአብሔር አብ ልጅ እግዚአብሔር ወልድ ለአዳም የገባለትን የመዳን ቃል ኪዳን ነው፡፡ ይህም ይፈጸም ዘንድ ነቢያት አስቀድሞ ትንቢት ተናግረዋል፡፡
አሸናፊና ኃያል፣ ሁሉን ቻይ የሆነ የእግዚአብሔርን ገናንነትና እርሱን የሚመስል አምላክ እንደሌለ የሚያመለክት የስሙ ትርጓሜ “መኑ ከመ አምላክ፤ እንደ አምላክ እግዚአብሔር ያለ ማን ነው?” የሆነ፣ የመላእክት ሁሉ አለቃ ሊቀ መላእክት ቅዱስ ሚካኤል በኅዳር ፲፪ የተሸሞበት ቀን “እግዚኡ ረሰዮ ለውእቱ ሚካኤል እምኵሎሙ መላእክት ይትሌዓል መንበሩ፤ ጌታው ሚካኤልን ከመላእክት ሁሉ መንበሩን ከፍ ከፍ አደረገው” እየተባለ ይከበራል፡፡
ዓለምን በመላ ከእነ ጓዟ ድንቅ አድርጎ የፈጠረ የሁሉን ቻይ የአምላክን ክብር መግለጽ ማን ይቻለዋል? ለእርሱ ክብር የሚመጥንስ ዙፋን ከየት ይገኛል? መንበረ ሥላሴን መሸከምስ ምንኛ ድንቅ ነው? እኒህ ቅዱሳን ኪሩቤልና ሱራፌል ግን ለእዚያ ክብር በቅተዋልና በዓላቸውን እናደርግ ዘንድ ይገባል፡፡
ለማዳን ሰውን ከጽኑ ግርፋት
ከሲኦል ትላትል ቁንጥጫ ከገሃነመ እሳት
ለአዳም ዘር በሙሉ የነፍስ ድኅነት
ለምኝልን እናት አትተይን በእውነት
ውድ የእግዚአብሔር ልጆች! እንዴት አላችሁልን? በዘመናዊ ትምህርታችሁስ እየበረታችሁ ነው? ትምህርት ከተጀመረ ሁለት ወርን አስቆጥረናል፡፡ ምን ያህል ዕውቀትን ገበያችሁ? ጊዜ አለን ብላችሁ እንዳትዘናጉ የተማራችሁትን ወዲያው በመከለስ አጥኑ፤ ያልገባችሁን ደግሞ መምህራንን ጠይቁ፤ በሰንበት እሑድ ቤተ ክርስቲያን በመሄድ መማርና ማገልገልን እንዳትረሱ፡፡ መልካም! ባለፈው ትምህርታችን ስለ ቅዱሳት ሥዕላት በተማርነው ትምህርት ቅዱስ ማለት ምን ማለት እንደሆነ፣ ሥዕል ማለት ምን ማለት እንደሆነና ለምን ቅዱሳት ሥዕላት እንደሚሣሉ በመጠኑ ተመልክተናል፡፡ ለዛሬ ደግሞ ቀጣዩን ክፍል “ሥዕለ አድኅኖ” በሚል ርእስ ስለ ቅዱሳት ሥዕላት አሣሣል ይዘንላችሁ ቀርበናል፡፡
ጽድቃችንም የመርገም ጨርቅ ከንቱ ሆኖ
መኖሪያችን በሲኦል ቋት ተወስኖ
ለዘመናት ስንገረፍ በእሳት ላንቃ
ያበቃ ዘንድ ይህ እንግልት ይህ ሰቆቃ
እሰይ እሰይ ይኸው አሁን የምሥራች
የሞት ዐዋጅ ተሻረልን፤ ገነት ዳግም ተከፈተች
የጥሉ ግድግዳ ፍርሶ ሰላም ሆኗል ከላይም ከታች
፶፻፭፻ የንስሐ የጣር ዘመን ተፈፀመ
በደላችን ተሰርዞ በክርስቶስ ደም ታተመ::
በዐሥራ ሦስተኛው ክፍለ ዘመን በሮሜ ሀገር የተወለዱት ቅዱስ አባታችን አቡነ አቢብ የስማቸው ትርጓሜ “የብዙኀን አባት” አንድም ቡላ ማለት “የተወደደ፣ እግዚአብሔር የተለየ” ነው፡፡ መጽሐፈ ስንክሳር ታላቅና ክቡር የሆነ አቢብ የተባለ መስተጋድል አባ ቡላ ተብሎም የሚታወቅ አባት በከበረች ዕለት ጥቅምት ሃያ አምስት (፳፭) እንዳረፈ ይጠቅሳል፡፡
