Entries by Mahibere Kidusan

ጌቴሴማኒ

ሥርወ ቃሉ ከዕብራይስጥ ቋንቋ የሆነው ጌቴሴማኒ “ጋት እና ስሜኒ” ከሚሉ ከሁለት ጥምር ቃላት የተገኘ ነው፡፡ ትርጉሙም “የዘይት መጭመቂያ”  ማለት ነው፡፡ ጌቴሴማንኒ የአትክልት ቦታ ዙሪያውን በወይራ ዛፎች የተከበበ ነው፡፡…ይህም ስፍራ አምላካችን እግዚአብሔር ፍርዱን የሚያደረግበት እንደሆነ ይታመናል፡፡

ታላቁ አባ መቃርስ

ከ፹ ዓመት በላይ በበረሃ የተጋደሉ፣ በአስቄጥስ ገዳም ፭፼ መነኮሳትን በመመገብ የመሩ፣ የጌታችን የመድኃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስን ሥጋ ወደሙን ተቀብለው ስለ ሥጋ ወደሙ ክብር ሲሉ ለ፷ ዓመት ምራቃቸውን ሳይተፉ የኖሩት ታላቁ አባት አባ መቃርስ በነሐሴ ፲፱ ፍልሰተ አጽማቸው ሳስዊር ከሚባል ሀገር ወደ አስቄጥስ የተፈጸመበት የከበረ በዓል ነው፡፡

በዓለ ትንሣኤ ወዕርገታ ለቅድስት ድንግል ማርያም

ከዚህ ዓለም ውጣ ውረድና ድካም በ፷፬ ዓመቷ በጥር ፳፩ ቀን በ፵፱ ዓ.ም ያረፈችው እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ትንሣኤዋም ሆነ ዕርገቷ በክብር የተፈጸመ እንደመሆኑ እኛም ልጆቿ ይህችን የተባረከች ቀን እናከብራለን፡፡

ትዕግሥተኛዋ እናት ቅድስት እንባመሪና

ውድ የእግዚአብሔር ልጆች!  ለከበረው ጤንነታችሁ እንዴት አላችሁ? የጾምን ወቅት እንዴት እያሳለፋችሁት ነው? አባቶቻችን ሊቃውንት ስለ ጾም እንዲህ ይላሉ፤ ጾም ማለት ከምግብና ከውኃ መከልከል ብቻ ሳይሆን ከክፉ ሥራም መታቀብ (መከልከል) ነው፤ ጾም የጽድቅ በር ናት፣ ጾም ለመልካም ነገር የምታነሣሣን ናት፤ ውድ እግዚአብሔር ልጆች! ስንጾም ከጸሎትና  ከስግደት ጋር፣ ቤተ ክርስቲያን በመሄድ በማስቀደስ ፣ታዛዦች በመሆን የጾሙን ጊዜ ልናሳልፍ ይገባል፡፡ መልካም!

ውድ እግዚአብሔር ልጆች! ለዛሬ ያዘጋጀንላችሁ ታሪክ የቅድስት እንባመሪናን ነው፡፡

ሙሻ ዘር

የተወደዳችሁ አንባብያን! እንደምን ሰነበታችሁ? የእግዚአብሔር አምላካችን ስም የተመሰገነ ይሁን! ባለፉት ክፍሎች ዘመድ ሙሻ ዘርን እና ባዕድ ሙሻ ዘርን ሰዋስውን ከሰዋስው ሳቢን ከተሳቢ እያናበቡ ዘጠኝ አገባባትን ሲያወጡ አይተናል። ከዚያ ቀጥለን ደግሞ ዛሬ የመጨረሻውን ክፍል እናያለን። መልካም ቆይታ!

በዓለ ደብረ ታቦር

በተከበረች በነሐሴ ፲፫ በታቦር ተራራ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ብርሃነ መለኮቱን የገለጠበት ዕለት በቅድስት ቤተ ክርስቲያናችን ”በዓለ ደብረ ታቦር‘ ተብሎ ይከበራል፡፡

ፅንሰታ ለማርያም

ለዓለም ሁሉ የድኅነት መገኛ የሆነች ክብርት እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም የተፀነሰችበት ዕለት ነሐሴ ሰባት የተባረከች እንደመሆና መላው ክርስቲያን በዓሏን ሊያከብር ይገባል፤ የመፀነሷ ነገርም እንዲህ ነው፡፡…

ማርኩሽ በለኝ!

አንተን ይዛ በተሰደደችው

በርሃ አቋርጣ ግብጽ በገባችው

በድንግል እናትህ በአምስቱ ኀዘኗ

ማርኩሽ በለኝ ስለ ቃል ኪዳኗ!

ጾመ ፍልሰታ

አምላክን የወለደች እመቤታችን ድንግል ማርያም ከዕረፍቷ በኋላ ከእርሳቸው ስለመለየቷ ሐዋርያት ፈጽሞ እያዘኑ ነበር፡፡ ከዚህም በኋላ የክብር ባለቤት ጌታችን ኢየሱስ ተገለጠላቸው፤ እርሷን በሥጋ ያዩ ዘንድ እንዳላቸውም ተስፋ ሰጣቸው፡፡

ወንጌላዊ ዮሐንስም እስያ በሚባል አገር እያስተማረ ሳለ በነሐሴ ወር ዐሥራ ስድተኛ ቀን ተድላ ደስታ ወደአለባት ገነት በመንፈስ ቅዱስ ተነጠቀ፡፡ የክብር ባለቤት ጌታ ኢየሱስ ክርስቶስን የእመቤታችን ማርያም ሥጋዋ ካለበት ከዕፀ ሕይወት ዘንድ ተቀምጦ አየው፡፡ የንጽሕት እናቱንም ሥጋ ታወጣ ዘንድ ምድርን እንዲጠሩዋት ሰባቱን የመላእክት አለቆች አዘዛቸው፤ እነርሱም ”የንጽሕት እናቱን ሥጋ ታወጪ ዘንድ እግዚአብሔር አዞሻል‘ አሏት፡፡ያን ጊዜም ከዕፀ ሕይወት በታች ካለ መቃብር የእመቤታችን ማርያም ሥጋዋ ወጣ፡፡…

ሙሻ ዘር

የተወደዳችሁ አንባብያን! እንደምን ሰነበታችሁ? የእግዚአብሔር አምላካችን ስም የተመሰገነ ይሁን! ባለፈው የትምህርታችን ክፍለ ጊዜ ‹‹እርባ ቅምር›› በሚል ርእስ የሁለተኛውን ክፍል ይዘንላችሁ ቀርበን ነበር፡፡ በዚህ ሳምንት ደግሞ ለሰጠናችሁ መልመጃ ምላሽና ስለ ‹‹ሙሻ ዘር›› እናስተምራችኋለን፤ በጥሞና ተከታተሉን!