መልካሟ ርግብ
ከቀለማት ሁሉ በላይ በሆነው፣ የፍጹምነት መገለጫ፣ ሰማያዊ ክብር በሚገለጽበት በጸአዳ ብሩኅነት ደምቃ፣ የንጽሕናን ሞገስ ተከናንባና አሸብርቃ በሰማይ ትበራለች፡፡ ከውልደቷ ጀምሮ የፈጠራት ይህን ሰማያዊ ጸጋ ሲያላብሳት እርሷም “አሜን” ብላ ተቀብላ ሰማያዊ መናን እየተመገበችና በሰማያት ሠራዊት እየተጠበቀች ከምድር ከፍ ከፍ ብላ መብረርን ለምዳ ከቤተ ሰቦቿ ተለየች፡፡
This author has not written his bio yet.
But we are proud to say that Mahibere Kidusan contributed 975 entries already.
ከቀለማት ሁሉ በላይ በሆነው፣ የፍጹምነት መገለጫ፣ ሰማያዊ ክብር በሚገለጽበት በጸአዳ ብሩኅነት ደምቃ፣ የንጽሕናን ሞገስ ተከናንባና አሸብርቃ በሰማይ ትበራለች፡፡ ከውልደቷ ጀምሮ የፈጠራት ይህን ሰማያዊ ጸጋ ሲያላብሳት እርሷም “አሜን” ብላ ተቀብላ ሰማያዊ መናን እየተመገበችና በሰማያት ሠራዊት እየተጠበቀች ከምድር ከፍ ከፍ ብላ መብረርን ለምዳ ከቤተ ሰቦቿ ተለየች፡፡
ሀገራችን ኢትዮጵያ የብዙ ጸጋዎች ባለቤት ናት፡፡ በብዙ ሰው ሠራሽና ተፈጥሯዊ ጸጋዎች የተሞላች ግን ደግሞ በውል ይህን እውነት የማንረዳ ብዙ ዜጎችም ያላት ሀገር ናት፡፡ “አንድ ሰው ጸጋውን የሚያውቀው ሲያጣው ነው” እንደሚባላው መንፈሳዊና ቁሳዊ፣ ተፈጥሯዊና ሰው ሠራሽ ጸጋዎቿን የምንረዳበትና ጠብቀን ተንከባክበን የምንጠቀምበት ዘመን ይመጣ ዘንድ እንመኛለን፡፡
የዚህች ሀገር ልዩ ጸጋዎች ከሆኑት መካከል ወቅቶች አንዱና ዋነኛው ነው፡፡ ምክንያቱም የዐሥራ ሦስት ወር ጸጋ የታደለች በክረምትና በበጋ፣ በጸደይና በበልግ በዐሥራ ሦስት ወር ወራት የተዋቀረ፣ ለሰው ልጆች ሁሉ ተስማሚ ወቅት ያላት ሀገር በመሆኗ ይህ በብዙዎች ዘንድ የማይገኝ ጸጋ ነው፡፡
ውድ የእግዚአብሔር ልጆች! እንዴት አላችሁልን? የዕረፍት ጊዜያችሁ እንዴት ነው? ጊዜያችሁን በአግባቡ ተጠቀሙ፤ በጨዋታ ብቻ ልታሳልፉት አይገባም፡፡ ልጆች! የክረምት ወቅት ከበድ ያለ ዝናም የሚዘንብበት ወቅት በመሆኑ በእያንዳንዱ ነገር ጥንቃቄ ማድረግ አለባችሁ! በባለፈው ትምህርታችን ስለ ሰባቱ ምሥጢራት ምንነት መግቢያውን ተምረናል፡፡ አሁን ደግሞ ስለ ምሥጢራት አፈጻጸም እንማራለን፤ ተከታተሉን!
ሥራው ግሩም የሆነ አምላካችን እግዚአብሔር ማዳንም መግደልም የሚችል የባሕርይ አምላክ ነው፡፡ (መዝ.፷፭፥፫) በእርሱ የሚታመኑት ቅዱሳን ሰማዕታት የሚደርስባቸውን መከራና ፈተና ሁሉ በጽናት፣ በልበ ሙሉነት የሚያልፉት ለዚህ ነው፡፡…ወርቅና ብር በእሳት ተፈትነው እንደሚጠሩ ቅዱሳን ሰማዕታትም በመከራ ውስጥ ተፈትነው እግዚአብሔርን አስደስተው ለእኛም የጽናት ምልክት ሆነው የክብር አክሊልን በመቀዳጀት ከገቡ መውጣት፣ ካገኙ ማጣት እና መከራ ወደ ሌለበት ዘለዓለማዊ ማረፊያቸው ይሄዳሉ፡፡
ነጭ አይሉት ጥቁር፣ አመዳማም አይደል ቀለሙ ይለያል፡፡ብዙዎች ስለ መልኩ መናገር ያዳግታቸውና ዝምታን ይመርጣሉ፤አያሌዎች ደግሞ በተፈጥሮው ተማርከው ውበቱን ያደንቃሉ፤ መግለጽ ግን ያቅታቸዋል፡፡
ውድ የእግዚአብሔር ልጆች! እንዴት አላችሁልን? የክረምትን ወቅት እንዴት እያሳላፋችሁ ነው? በአቅራቢያችሁ ወዳለው ቤተ ክርስቲያን በመሄድ መንፈሳዊ ትምህርት እየተማራችሁ እንደሆነ ተስፋ እናደርጋለን፤ ምክንያቱም ትምህርት ተዘጋ ብለን ጊዜውን በጨዋታ ብቻ ልናሳልፈው አይገባም፡፡ ለመጪው የትምህርት ዘመን አዲስ ለምትገቡበት ክፍል ቅድመ ዝግጅት በማድረግ (መጻሕፍትን በማንበብ) ጊዜውን ልትጠቀሙበት ያስፈልጋል፡፡
ውድ የእግዚአብሔር ልጆች! የክረምት ወቅት ከበድ ያለ ዝናም የሚዘንብበት ወቅት በመሆኑ በእያንዳንዱ ነገር ጥንቃቄ ማድረግ አለባችሁ! መልካም! ከዚህ ቀደም በተከታታይ መሠረታዊ የሆነ የቤተ ክርስቲያን ትምህርት ሥነ ፍጥረት፣ አምስቱ አዕማደ ምሥጢራትን ስንማማር ቆይተናል፤ አሁን ደግሞ ስለ ሰባቱ ምሥጢራት እንማራለን!
ሰው በልዩ ልዩ ሁኔታዎች ውስጥ ሲገኝ የሚሰማውን ስሜት በስሜት ሕዋሳቱ አማካኝነት ይገልጣቸዋል፡፡ ደስታ፣ ቁጣ፣ ፍርሃት፣ ሕመም፣ ፍቅር እና የመሳሰሉት ስሜቶቻችን ናቸው፡፡ ሰው እነዚህን ስሜቶቹን በስሜት ሕዋሳቱ በዐይኑ፣ በእጁ፣ በእግሩ፣ በአንደበቱ፣ በፊት ገጽታውና በሰውነት እንቅስቃሴው ይገልጣል፡፡ እነዚህ ስሜቶች ከሚቀሰቀሱበት ሁነቶች፣ ድርጊቶችና ክስተቶች አንጻር በፍጥነት ምላሽ ሳይሰጥ ነገሮችን በዕርጋታ የሚመረምር ሰው በሳል ወይም ባለ አእምሮ ይባላል፡፡ በተቃራኒው ለጉዳዮች ፈጣን ምላሽ የሚሰጠውን ደግሞ ስሜታዊ እንለዋለን፡፡ ባለ አእምሮ ሰው በመረጋጋቱ ብዙ ሲያተርፍ ስሜታዊ ሰው ግን የሚያጸጽቱና ግላዊ፣ ማኅበራዊ እንዲሁም ሀገራዊ ጥፋቶችን የሚያስከትሉ ዋጋዎችን ይከፍላል፡፡ በመሆኑም መጽሐፍ “እንግዲህ እንደ ባለ አእምሮ አስቡ” በማለት ያስተምረናል፡፡ (፩ኛጴጥ.፬፥፯-፰)
ድሮ ድሮ ልቡ ሲቀና ሕሊናውን መግዛት ተስኖት፣ አእምሮውን ወጥሮ ሲይዘው፣ ሐሳቡን መሰብሰብና አቅንቶ ማየት ያቅትውና ይጨነቅ ነበር፤ ቀጥተኛውን መንገድ ጠማማ፣ ከፍተኛውን ኮረብታ ዝቅተኛ፣ አባጣ ጎርባጣውን ምቹ አድርጎ ሲመለከት ለመልካም ነገር መወሰን ይሳነዋል፤ ፍቅር ግን ይህን ሁሉ ቀየረለት፤ በትዕቢት የታወረውን ዓይኑን አብርቶ፣ ትምክህቱንና ጭንቀቱን አጥፍቶ የውስጥ ዕረፍት ሰጥቶታልና፡፡
ውድ አንባብያን! እንደምን ሰነበታችሁ? አሜን! የአምላካችን የእግዚአብሔር ስም የተመሰገነ ይሁን! በዓለ ቅድስት ሥላሴን በተመለከተ አጭር ጽሑፍ አቅርበንላችኋል፤
ቅድስት ቤተ ክርስቲያናችን አባቶቻችን ሐዋርያትን ሰማዕትነት በተቀበሉበት ቀናት በዓላት ሰይማ ታከብራቸዋለች፡፡ እንዲሁም በስማቸው የተሰየመውን ጾም በመጾም አሠረ ፍኖታቸውን ይከተሉ ዘንድ ምእመናንን ታሳስባለች፡፡ በሐምሌ ፭ ቀን ደግሞ የደጋጎቹን ሐዋርያት የቅዱስ ጴጥሮስና የቅዱስ ጳውሎስን በዓል ታደርጋለች፡፡ የእነዚህ ቅዱሳን አባቶቻችን በዓል መደረጉ በአንድ ቀን ሰማዕትነት በመቀበላቸው ነው፡፡