Entries by Mahibere Kidusan

ቅዱስ ኤፍሬም

ውድ የእግዚአብሔር ልጆች! እንዴት አላችሁ? ወርኃ ክረምትን እንዴት እያሳለፋችሁ ነው? ዘመናዊ ትምህርት ተጠናቆ አሁን ዕረፍት ላይ እንደመሆናችሁ መጠን ጊዜያችሁን በተገቢው መንገድ እየተጠቀማችሁበት እንደሆነ ተስፋ እናደርጋለን! በጥሩ ውጤት ከክፍል ክፍል እንደተዘዋወራችሁም ተስፋ አለን፡:ልጆች! ዛሬ የምንነግራችሁ የቅዱስ ኤፍሬምን ታሪክ ነው፡፡

ለሲኖዶሳዊ ልዕልና መከበር የምእመናን ድርሻ አስፈላጊ ነው!

ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ግን ቤተ ክርስቲያን የመልካም አስተዳደር ችግሮች እና የቅዱስ ሲኖዶስ ልዕልና አለመከበር እንዲሁም በርካታ ምእመናን በቤተ ክርስቲያን አስተዳደራዊ ጉዳዮች  ባይታዋር የሆኑበት፣ ቤተ  ክርስቲያንን ለካህናቱና ጳጳሳቱ ብቻ እየተው የመጡበት ሁኔታ ይታያል፡፡

ቅድስት ቤተ ክርስትያንን ፖለቲከኞች፣ አማሳኞች፣ ምንደኞች አገልጋዮች እንዲሁም የውስጥም ሆነ የውጭ ጠላቶቿ  አጀንዳ ሲያደርጓት፣ ባልዋለችበት ሲያውሏት፣ የማይገልጻትን ጥላሸት ሲቀቧት፣ ታሪኳን ሲሰርዙ፣ ሲደልዙ፣ የፕሮፖጋንዳ ሰለባ ሲያደርጓት፣ በባሰ ሁኔታ ኵላዊትነቷን፣ ዓለማቀፋዊነቷን  ወደ ጎን በማለት በርካሽ የጎሳ ከረጢት ሊከቷት ሲሞክሩ እያዩ ዝም ማለታቸው ነው፡

እግዚአብሔር ዝም ይላልን?

በየግል ሕይወታችን ችግር ሲገጥመን መፍትሔ ለማግኘት ወደ እግዚአብሔር እንደምንጮኸው ሁሉ በቤተ ክርስቲያን ላይ መከራ ሲመጣም እንዲሁ ከርሱ መፍትሔ እንጠብቃለን። በእኛ መረዳት የዘገየ ወይም ዝም ያለ ሲመስለን “ለምን?” እንላለን። “ካህናት እየታረዱ፣ አብያተ ክርስቲያናት እየተቃጠሉ፣ ምእመናን እየተፈናቀሉ፣ ቅዱሳት መጻሕፍት እየተቆነጸሉ፣ ቤተ መቅደሱ እየተደፈረ፣ እንዴት እግዚአብሔር ዝም ይላል?” እንላለን። እንደዚህ የምንለው ምናልባትም አንዳች መቅሠፍት ወርዶ እንዲህ የሚያደርጉ ሰዎችን ያጠፋቸው ይሆናል ብለን ስለምንጠብቅና እንዳሰብነው ሳይሆን ሲቀር ሊሆን ይችላል። ምንም እናስብ ብቻ እኛ በጠበቅነው መንገድ ነገሮች ስላልሆኑ ግራ እንጋባለን፤ ከዚያም አልፈን ተስፋ እንቆርጣለን።

‹‹አቤቱ በፊትህስ ባለሟልነትን አግኝቼ እንደሆነ ባሪያህን አትለፈው›› (ዘፍ.፲፰፥፫)

ሥላሴ ሊቃውንት ‘የወይራ ዛፍ’ ብለው በተረጎሙት በመምሬ ዛፍ ሥር ተገለጠ፤ አብርሃምም ጎልማሳ እንግዶች መስለውት ወደ ቤቱ ወስዶ ያስተናገዳቸው ዘንድ ወደ እነርሱ ሮጠ፤ ‹‹ባያቸውም ጊዜ ሊቀበላቸው ከድንኳኑ ደጃፍ ሮጠ›› እንዲል (ዘፍ.፲፰፥፪)። ቀርቦም ከምድር ወድቆ እጅ ነሣ፤ እንዲህም አላቸው። ‹‹አቤቱ በፊትህስ ባለሟልነትን አግኝቼ እንደሆነ ባሪያህን አትለፈው፤ ውኃ እናምጣላችሁ፤ እግራችሁን እንጠባችሁ።›› (ዘፍ.፲፰፥፫)

‹‹እስከ ሞት ድረስ የታመንክ ሁን›› (ራእ.፪፥፲)

የክርስትናን ሕይወትና ጉዞ መጀመር ቀላል ሲሆን ዳገት የሚሆነው መፈጸሙ ነው፡፡ ‹‹እስከ ሞት›› የመባሉም ዋናው ምክንያት ይህ ነው፡፡ ጌታችን አምላካችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ስለ ዕለተ ምጽአቱ ባስተማረበት የወንጌል ክፍልም ከዚህ ኃይለ ቃል ጋር በእጅጉ አንድ በሆነ መንገድ ‹‹እስከ መጨረሻ የሚጸና እርሱ ይድናል››  በማለት ያስተማረው ትምህርት መፈጸም እንደመጀመር ቀላል እንዳልሆነ የሚያስረዳን ነው፡፡ (ማቴ.፳፬፥፲፫)

እግዚአብሔር ዝም ይላልን?

በዓለም ስንኖር መከራና ደስታ፣ ውድቀትና ስኬት፣ ድካምና ብርታት ልዩ ልዩ ነገሮች ይፈራረቁብናል። በርግጥ ይህ አዲሳችን አይደለም። “በዓለም ሳላችሁ መከራ አለባችሁ” ተብለናልና! እንኳን በክርስትና ሕይወት ውስጥ ያለንና መንፈሳዊ ጠላት ያለብን ሰዎች ማንኛውም ሰው ሰው በመሆኑ ብቻ ውጣ ውረድ ያጋጥመዋል። (ዮሐ.፲፮፥፴፫)

ወርኃ ክረምት

ውድ የእግዚአብሔር ልጆች! እንዴት አላችሁ? የዓመቱ ትምህርት ጊዜ ተጠናቆ ፈተና ተፈትናችሁ ጨረሳችሁ አይደል? ውጤት እንዴት ነው? በጥሩ ውጤት ከክፍል ወደ ክፍል እንደተዘዋወራችሁ ተስፋ እናደርጋለን፤ አሁን ደግሞ የክረምት ጊዜ ስለመጣ ለዛሬ ልናስተምራችሁ የወደድነው ስለ ወርኃ ክረምት ነው፡፡

‹‹በልቅሶ የሚዘሩ በደስታ ይሰበስባሉ›› (መዝ.፻፳፭፥፭)

የሰው ልጅ በዚህ ምድር ከሚፈራረቁበት የስሜት ነጸብራቆች ዋነኞቹ ኀዘን (ልቅሶ)ና ደስታ ናቸው። እርግጥ ነው እግዚአብሔር የሰውን ልጅ የፈጠረው እያመሰገነው በደስታ ይኖር ዘንድ ነበር፡። ስለዚህም እግዚአብሔር ሰውን የሚያስፈልገውን ሁሉ ካዘጋጀለት በኋላ በአትክልት ሥፍራ ኤደን ገነት በደስታ እንዲኖር አስቀመጠው፡፡ ነገር ግን የሰው ልጅ በገዛ ፈቃዱ ደስታ የሚሰጠውን ሕግ አፍርሶ የደስታ ምንጭ የሆነውን እግዚአብሔርን አጣ፤ በማጣት ብቻም አልቀረም ‹‹…ስለዚህ የተገኘባትን መሬት ያርስ ዘንድ እግዚአብሔር አምላክ ደስታ ከሚገኝባት ገነት አስወጣው…›› (ዘፍ. ፫÷፳፫)። የሰው ልጅ በድሎ ከኤደን ገነት ወደ ምድር (ዓለመ መሬት) ከመጣ በኋላ እግዚአብሔርን አሳዝኖ ጸጋውን አጥቷልና በሕይወቱ ኀዘን (ልቅሶ) ሰፊውን ጊዜ የሚወስድበት ፍጡር ሆነ። ለ፭ሺ ፭መቶ ዘመን የሰው ልጅ ፍጹም በሆነ ኀዘን ውስጥ ከኖረ በኋላ እግዚአብሔር ወልድ በተለየ አካሉ ሥጋን ተዋሕዶ በመገለጥ ለአዳም (ለሰው ልጅ) ካሣ በመሆን ወደ ፍጹም ደስታ መልሶታል።

ተስፋ

ሕይወታችን ያለ ተስፋ ባዶ ነው፤ ያለ ተስፋ መኖር አንችልም፤ ተስፋ ከሌለን ማንኛውንም ዓይነት የኑሮ ገጠመኝና ችግር ማሳለፍ አይቻለንም፡፡ የሰው ልጆች ዋነኛው ብርታት ተስፋ ማግኘትና በተስፋ መኖር ነው፡፡ የመጀመሪያው ሰው አዳም የአምላካችን የእግዚአብሔርን ሕግ ተላልፎ አትብላ የተባለውን ዕፀ በለስ ከበላ በኋላ የሞት ፍርድ ተፈርዶበት በምድር ላይ ሲኖር በኀዘንና በጭንቅ ነበር፡፡ ሆኖም ግን ፈጣሪ የልቡን ጭንቀትና ኀዘን ተመልክቶ ሊምረው ስለወደደ ከልጅ ልጁ ተወልደ እንደሚያድነው ቃል ገባለት፡፡ ይህም ለአዳም ትልቅ ተስፋ ስለነበረ ትንቢቱ ይፈጸም ዘንድ በተስፋ ጠብቋል፡፡