ምሕረት ሥጋዊና ምሕረት መንፈሳዊ

የምሕረት አምላክ ቸሩ ፈጣሪያችን እግዚአብሔር ኃጢአት በደላችንን ሁሉ ታግሦ እንደ ሥራችን ሳይሆን እንደ ቸርነቱ ለአዲሱ ዓመት አበቃን፡፡ ዕድሜ ለንስሓ ዘመን ለፍስሐ ያደለን አምላካችን በሰጠን የተፈጥሮ ጸጋ ተጠቅመን ከክፉ መንገዳችን እንድመልስ፣ ከኃጢአት እንድንነጻ እንዲሁም በጎ ሥራ እንድሠራ ነው፡፡ ምሕረቱ የበዛ ቁጣውም የራቀ ቸርነቱ አያልቅምና በእርሱ ጥላ ሥር ተጠልለን በሥነ ምግባር እንድንኖር መልካም ፈቃዱ ሆነ፡፡ ይህንንም በቅዱሳን ልጆቹ ላይ ፈጽሞ አሳይቶናል፡፡ በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ስም ክርስቲያን የተባልን በሙሉም ምሕረትን ስለማድረግ ልናውቅ ያገባናል፡፡ ሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያን ምሕረት በሁለት እንድሚከፈል ያስተምሩናል፤ እነርሱም ምሕረት ሥጋዊና ምሕረት መንፈሳዊ ናቸው፡፡

መልእክተ ቅዱስ ፓትርያርክ

የብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት የእንኳን አደረሳችሁ ቃለ በረከት!

በዓለ መጥምቀ መለኮት ቅዱስ ዮሐንስ

መጥምቀ መለኮት ቅዱስ ዮሐንስ በሰማዕትነት ያረፈበት ዕለት መስከረም ሁለት የተከበረ ነው፡፡ ይኸውም ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የመጥምቁን ክብር ‹‹እውነት እላችኋለሁ፥ ከሴቶች ከተወለዱት መካከል ከመጥምቁ ዮሐንስ የሚበልጥ ማንም የለም” በማለት መሥክሮለታል፡፡ (ማቴ. ፲፩፥፲፩፣ ሉቃ ፯፥፳፰)

ርእሰ ዐውደ ዓመት

አምላካችን እግዚአብሔር ዕድሜ ለንስሓ ዘመን ለፍስሐ የሰጠን መልካም እንድንሠራበት ነውና በመጪው ዘመን የትላንት ስሕተታችንን አርመን፣ የተጣላን ታርቀን፣ የበደልን ክሰን፣ ያለው ለሌለው እያካፈለ ለመኖር ማቀድ ይገባናል!

በዓለ ቅዱስ ሩፋኤል

ጳጉሜን ሦስት ቀን የሊቀ መላእክት የቅዱስ ሩፋኤል በዓል በየዓመቱ ይታሰባል፤ ይከበራልም፡፡ መልአኩ የጦቢትን ዓይን ያበራና ወለተ ራጉኤልን ተቆራኝቷት ከነበረው ጋኔን ያላቀቀ ነውና፡፡ ሊቀ መላእክት ቅዱስ ሩፋኤል ከመላእክት አለቆች ሦስተኛ የሆነ ነው፡፡ ደግሞም ከእስክንድርያ ውጭ በደሴት የታነጸች ቤተ ክርስቲያን በከበሩ ሊቀ ጳጳሳት ቴዎፍሎስ ዘመን በውስጧ ተአምር የተገለጸበትና የከበረችበት ዕለት ነው፡፡

የጳጉሜን ወር

በዓመት ውስጥ ካሉት ወራት የተለየች፣ ቀኖቿም ጥቂት እንዲሁም አጭር በመሆኗ የጳጉሜን ወር ተናፋቂ ያደርጋታል፡፡ እግዚአብሔር አምላካችን ለሀገራችን ኢትዮጵያ ካደላት ስጦታ አንዷ የሆነችውም ይህች ወር በዘመነ ዮሐንስ ስድስት ቀናት እንዲሁም ደግሞ በዘመነ ማርቆስ፣ በዘመነ ሉቃስና በዘመነ በማቴዎስ አምስት ቀናት ብቻ አላት፡፡ በቤተ ክርስቲያናችን አስትምህሮ የጳጉሜን ወር የዓመት ተጨማሪ ወር እንላታለን፡፡  ምዕራባዊያኑ ግን ተጨማሪ ቀን እንደሆነች በማሰብ በዓመቱ ባሉ ወራት ከፋፍለዋታል፡፡

ጳጉሜን የሚለው ስያሜ “ኤፓጉሜኔ” ከሚለው የግሪክ ቃል የመጣ ሲሆን ትርጉሙም “ጭማሪ” ማለት ነው፡፡ በግእዝ “ወሰከ-ጨመረ” ከሚለው የግእዝ ግስ የወጣ ተውሳክ (ተጨማሪ) ማለት ነው፡፡ (አለቃ ኪዳነ ወልድ ክፍሌ፤ መዝገበ መጽሐፈ ሰዋስው ወግስ ወመዝገብ ቃላት፤ ገጽ ፱፻፭)

ዕረፍተ ዘአበዊነ አብርሃም፣ይስሐቅ ወያዕቆብ

የአባቶቻችን የአብርሃም፣ የይስሐቅና የያዕቆብን መታሰቢያቸውን እናደርግ ዘንድ የቤተ ክርስቲያን መምህራን አባቶቻችን አዘውናል፤ ከእርሳቸው ዘለዓለም የሚኖር ርስትን ተቀብለናልና፡፡ የእነዚህንም አባቶች ገድላቸውን እንዘክር ዘንድ ተገቢ ነው፡፡

ነገረ ግሥ ወአገባብ

የተወደዳችሁ አንባብያን! እንደምን ሰነበታችሁ? የእግዚአብሔር አምላካችን ስም የተመሰገነ ይሁን! ባለፉት ክፍሎች ዘመድ የሙሻ ዘርን የመጨረሻውን ክፍል አቅርበንላችኋል። በዚህ የትምህርታችን ክፍለ ጊዜ ደግሞ ስለ ‹‹የነገረ ግሥ ወአገባብ›› ይዘንላችሁ ቀርበናል። በጥሞና ተከታተሉን!

በዓለ አቡነ ተክለ ሃይማኖት

አምላካችን እግዚአብሔር ለነቢዩ ኤርምያስ “በሆድ ሳልሰራህ አውቄሃለሁ፤ ከማኅፀን ሳትወጣ ቀድሸሃለሁ” በማለት እንደተናገረ የገናናው ጻድቅ የአባታችን ተክለ ሃይማኖት ዜና ሕይወቱን እንዘክራለን፡፡ (ኤር.፩፥፭)

ቅድስት ክርስቶስ ሠምራ

ውድ የእግዚአብሔር ልጆች!  ለከበረው ጤንነታችሁ እንዴት አላችሁ? የጾመ ፍልስታ ወቅት እንዴት ነበር? እንኳን አደረሳችሁ!  የክረምት ወቅት አልፎ አዲሱን ዓመት ልንቀበል ቀናት ብቻ ቀርተውናል! እህቶቻችንን ለዚህ ያደረሰንን ፈጣሪ በዝማሬ ያመሰግናሉ፤ ልጆች! ለመሆኑ አበባ አየሽ ወይ? እያልን የምንዘምረው “የተዘራው ዘር በቅሎ ቅጠል ከዚያም ደግሞ አበባን ሰጥቷል፤ ቀጥሎ ደግሞ ፍሬን ይሰጣል” በማለት የምሥራችን እያበሠሩ ለዚህ ያደለንን ፈጣሪ ያመሰግናሉ፡፡ ልጆች! ሌላው ደግሞ መዘንጋት የሌለባችሁ ነገር ለመጪው የትምህርት ዘመን ዝግጅት ማድረግ እንዳለባችሁ ነው፤ መልካም!
ውድ የእግዚአብሔር ልጆች! ለዛሬ ያዘጋጀንላችሁ ታሪክ የቅድስት ክርስቶስ ሠምራን ነው፤