ውኃ የሌለባቸው ምንጮች

ውኃ ከምንጭ ተገኝቶ እየፈሰሰ የፍጥረትን ጥማት ያረካል፡፡ በውኃ ሰው ሕይወቱን ያለመልማል፤ እንስሳትና አራዊትም እንዲሁ፡፡ ዕፅዋትና አዝርዕትም ያለ ውኃ አይለመልሙም፤ አይበቅሉምም፡፡ በቅዱሳት መጻሕፍት እንደ የአገባቡ መምህራን በውኃ ምንጭ ተመስለዋል፡፡ ከምንጭ ንጹሕ ውኃ ተገኝቶ ፍጥረትን እንደሚያረሰርስ ከመምህራንም አንደበት በውኃ የሚመስል ቃለ እግዚአብሔር እየፈሰሰ የሰው ልጆችን በጽድቅ እንዲኖኑ ያደርጋል፡፡ ምእመናን ውኃ ቃለ እግዚአብሔር ከሚገኝባቸው እውነተኞች መምህራን እግር ሥር ተገኝቶ በመማር ከድርቀት ኃጢአት ወደ ልምላሜ ጽድቅ ይመጣሉ፤ የመንፈስ ፍሬንም ያፈራሉ፡፡

ቅድስት አርሴማ

ውድ የእግዚአብሔር ልጆች! ለከበረው ጤንነታችሁ እንዴት አላችሁ! የክረምት ወቅት አልፎ አዲሱን ዓመት ተቀብለናልና ለዚህ ያደረሰንን ፈጣሪያችንን ማመስገን ይገባል! ልጆች! መስቀል በዓል እንዴት ነበር? በሰላም በፍቅር አከበራችሁ አይደል? የእኛን ምክርም ተቀብላችሁ ለመጪው የትምህርት ዘመን ዝግጅት ስታደርጉ እንደቆያችሁ ደግሞ ተስፋችን ነው፡፡ አሁን ደግሞ ትምህርት ስለጀመራችሁ በርትታችሁ መማርን እንዳትዘንጉ! ከአሁኑ ጀምራችሁ መምህራን የሚነግሯችሁን በንቃት ተከታተሉ፤ መጻሕፍትን አንብቡ፤ ያልገባችሁን ጠይቁ፤ የቤት ሥራችሁን በአግባቡ ሥሩ፤ የጨዋታ ጊዜያችሁንና ቴሌቪዥን የምታዩበትን ጊዜ መቀነስ አለባችሁ፤ አሁን የእናንተ ተግባር፣ እይታ፣ ሥራ፣ ጉዳይ ሁሉ ትምህርት እና ትምህርት ብቻ ስለሆነ ጎበዝ ተማሪዎች ሁኑ፤ መልካም!

ውድ የእግዚአብሔር ልጆች! ለዛሬ ያዘጋጀንላችሁ ታሪክ የቅድስት አርሴማን ነው፤

ቃላተ አንጋር

የተወደዳችሁ አንባብያን! እንደምን ሰነበታችሁ? የእግዚአብሔር አምላካችን ስም የተመሰገነ ይሁን! በዘመነ ሉቃስ የመስከረም ወር ሁለተኛ ክፍለ ጊዜያችን የሆነውን ትምህርት ከማቅረባችን በፊት በባለፈው ትምህርታችን በግእዝ ቋንቋ የምንጠቀምባቸውን ዓረፍተ ነገሮች ከቤተሰቦቻችሁ፣ ከዘመዶቻችሁ፣ ከጓደኞቻችሁ እንዲሁም ከጎረቤቶቻችሁ ጋር እንድትለማመዷቸው አቅርበንላችሁ እንደነበር በማስታወስ በሚገባ ተረድታችሁ እንደተለማመዳችሁትና በቃላችሁ እንደያዛችኋቸውም ተስፋ እናደርጋለን!

የዚህ ሳምንት ትምህርታችን ደግሞ በግእዝ ቋንቋ ውስጥ የምንጠቀምባቸው የንግግር ስልቶች (ቃላተ አንጋር) ላይ ያተኮረ ነው፡፡ ስለዚህም በመጀመሪያ በግእዝ ቀጥሎም በአማርኛ ስልቶቹን አከታትለን አቅርበንላችኋልና ተከታተሉን!

የጽጌ ወር

ምድር በአበቦችና በዕፅዋቶች ተሞልታ የምታሸበርቅበት ወቅት የጽጌ ወር በክርስቲያናዊ ሕይወታችን ውስጥ ትልቅ ትርጉም አለው፡፡ የመዳኛችን ተስፋ የሆነችውና የዓለምን ቤዛ የወለደችን ቅድስት ድንግል ማርያም አበባውን በሚያስገኙት ዕፀዋትና በምድር፣ የተወደደ ልጇ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ደግሞ በአበባው እንደሚመሰሉ ቀደምት ነቢያት አስተምረውናል፡፡

ግሽን ማርያም

በሀገራችን ኢትዮጵያ በወሎ ክፍለ ሀገር አምባሰል አውራጃ የሚገኘው ታላቁ የግሸን ማርያም ደብር የግማደ መስቀሉ መገኛ በመሆኑ ለሕዝበ ክርስቲያኑ ትልቅ ተስፋና መመኪያ ነው፡፡ መስቀል የክርስትናችን መገለጫ፣ የብርሃናችን ዐምድ እንዲሁም የሰላማችን መገኛ ነውና፡፡

ጉባኤ ኒቅያ

ጉባኤ ኒቅያ ቤተ ክርስቲያን አንድነቷን የጠበቀችበት፣ አርዮስና አርዮሳውያን የተወገዙበት፣ የጌታችን የመድኃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ የባሕርይ አምላክነት፣ አዳኝነት፣ ጌትነት፣ መድኃኒትነት የተመሠከረበት፣ ኦርቶዶክስ የሚለው ስም ትምክህት የሆነበት ነው፡፡ ቤተ ክርስቲያን ይህን ጉባኤ ትቀበላለች፤ ትልቅም ስፍራ አላት፡፡

ጨረቃ

እስኪ እንጀምር ከልደቷ

በፍጥረቱ በውልደቷ

ከቀን በዐራተኛ መገኘቷ

በረቡዕ በዐራተኛ

ከተራራ ከፍ ያለች ከፀሐይ መለስተኛ

ቅዱስ መስቀል

ውድ የእግዚአብሔር ልጆች! እንዴት አላችሁ? እንኳን ከዘመነ ማርቆስ ወደ ዘመነ ሉቃስ አሸጋግሮ በሰላም ለዚህ ዕለት አደረሳችሁ! ዕንቁጣጣሽ እንዴት አለፈ? መቼም ደስ ብሏችሁ እንዳሳለፋችሁ ተስፋችን እሙን ነው፡።  መልካም! የአዲስ ዓመት ትምህርት ለመጀመር እንዴት እየተዘጋጃችሁ ነው? ባለፈው ዓመት በትምህርታችን ደከም ያለ ውጤት አስመዝግበን የነበርን ዘንድሮ በርትተን በመማር በጥሩ ውጤት ከክፍል ክፍል ለመሻገር ከአሁኑ ማቀድና መበርታት አለብን፡፡ እንዲሁም ደግሞ ለአገርና ለቤተ ክርስቲያን እየጸለይን የሰላምን ዘመን ተስፋ እናድርግ! መልካም!

ውድ የእግዚአብሔር ልጆች! ባለፉት ጊዜያት ለእናንተ ያስተምራሉ በማለት በጻፍንላችሁ በርካታ ቁም ነገሮችን ስንማማር እንደነበር ታስታውሳላችሁ አይደል? አሁን ደግሞ ስለ ቅዱስ መስቀሉ በዓል ጥቂት ልናካፍላችሁ ወደድን፤ መልካም ቆይታ!

‹‹ሥዕሏ ሥጋን የለበሰች ትመስል ከሠሌዳዋም ቅባት ይንጠፈጠፈ ነበር››

ሕዝበ ክርስቲያን ከሚያከብሩት ከእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ፴፫ቱ በዓላት አንዱ ጼዴንያ ማርያም በቅድስት ቤተ ክርስቲያናችን በመስከረም ፲ ቀን ይከበራል፡፡ በተለይም በሀገራችን ኢትዮጵያ በአዲስ አበባ  ቡራዮ አካባቢ ጼዴንያ ማርያም በምትባል ቤተ ክርስቲያን በዕለቱ ታቦተ ክብሩ ከመንበሩ ወጥቶ በደማቁ ተከብሮ ይውላል፡፡ ጼዴንያ በምትባል ሀገር ሥጋ የለበሰች ከምትመስል ሥዕል ከሠሌዳዋ ቅባት እየተንጠፈጠፈ አምላክን የወለደች የእመቤታችን የድንግል ማርያም ተአምር ተገልጧልና፤ ይህችን ድንቅ ሥዕልም ቅዱስ ሉቃስ እንደሣላት ይነገራል።

የግእዝ መግባቢያ ዓረፍተ ነገሮች

የተወደዳችሁ አንባብያን! እንደምን ሰነበታችሁ? የእግዚአብሔር አምላካችን ስም የተመሰገነ ይሁን! እንኳን ለዘመነ ሉቃስ አደረሳችሁ! እግዚአብሔር አምላክ አዲሱን ዓመት የሰላምና የደስታ እንዲያደርግላችሁ ከወዲሁ እንመኝላችኋለን!

አዲሱ ዓመት ቤተሰቦቻችንን፣ ዘመዶቻችንን፣ ጓደኞቻችንን እንዲሁም ጎረቤቶቻችንን የምንጠይቅበትና እንኳን አደረሳችሁ የምንልበት ጊዜ ነውና ከሰዎች ጋር ንግግር የምናደርግባቸው የመግባቢያ  ዓረፍተ ነገሮች በግእዝ ምን እንደሆኑ ታውቁ ዘንድ እንደ ዐውደ ዓመት ስጦታ እነሆ ብለናችኋል!