ወንጌላዊው ቅዱስ ሉቃስ

በሀገረ አንጾኪያ ከአሕዛብ ወገን የተለወደው አይሁዳዊው ሉቃስ ከሰባ ሁለቱ አርድእት የተቆጠረ ባለ መድኃኒትና ወንጌልን የጻፈ ቅዱስ ሐዋርያ ነው፡፡ ሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያን በወንጌል ትርጓሜያቸው ስሙ ‹ዓቃቤ ሥራይ› ወይም ‹ባለ መድኃኒት› የሚል ትርጉም በውስጡ የያዘ መሆኑን ያስረዳሉ፡፡ በላቲን ቋንቋ ‹ሉካስ› ማለት ‹ብርሃናማ፣ ብርሃን የያዘ› ማለት ነው፡፡ መጽሐፈ ስንክሳር ደግሞ ብልህና ጥበበኛ በማለት ይገልጸዋል፡፡

ቅዱስ ዮሐንስ ሐጺር

በዐሥራ ስምንት ዓመት ዕድሜው የመነኮሰ፣ ትዕግሥቱ እጅግ የበዛ እንዲሁም የመታዘዝ ጸጋ የተሰጠው ቅዱስ አባታችን ዮሐንስ ሐጺር የዕረፍት መታሰቢያ ጥቅምት ሃያ ቀን ነው፡፡ ሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያን እንደሚገልጹትም ይህ ጻድቅ ከቅዱሳን አባቶች መካከል በቁመት እንደ እርሱ አጭር ስላልነበረ ‹‹ቅዱስ ዮሐንስ ሐጺር፤ አጭሩ አባ ዮሐንስ›› ተብሏል፡፡ የእርሱን ቁመትና የቅድስና ሕይወቱን ሲያነጻጽሩም ‹‹ቁመቱ እጅግ ያጠረ ጽድቁ ግን ከሰማይ የደረሰ ቅዱስ ዮሐንስን ሰላም ሰላም እንለዋለን›› በማለት ተናግረዋል፡፡

ሊቀ ዲያቆናትና ቀዳሜ ሰማዕት ቅዱስ እስጢፋኖስ

ውድ የእግዚአብሔር ልጆች እንዴት አላችሁልን? ትምህርት እንዴት ነው? መቼም በክረምቱ የዕረፍት ጊዜያችሁ ትምህርት እስኪከፈት በጣም ጓጉታችሁ እንደነበር እናስባለን! ይኸው ተከፈተላችሁ! እንግዲህ በርትታችሁ ከአሁኑ መማር፣ ማጥናት፣ የቤት ሥራን መሥራት፣ ያልገባችሁን መጠየቅ ይገባችኋል፡፡ ገና ነው እያላችሁ እንዳትዘናጉ ጥናቱን አሁኑኑ ጀምሩ! የጨዋታም ሆነ ቴሌቪዥን የምታዩበት ጊዜ ከትምህርታችሁ ጋር በማይጋጭ መልኩ መሆን አለበት፡፡ ከሁሉም ትምህርታችሁን አስቀድሙ! ውድ እግዚአብሔር ልጆች! ለዛሬ ያዘጋጀንላችሁ የሊቀ ዲያቆናትና የቀዳሜ ሰማዕት ቅዱስ እስጢፋኖስን ታሪክ ነው፡፡

ረብሐ ግሥ

የተወደዳችሁ አንባብያን! እንደምን ሰነበታችሁ? የእግዚአብሔር አምላካችን ስም የተመሰገነ ይሁን! የጥቅምት ወር የመጀመሪያ ክፍለ ጊዜያችን ወደ ሆነው ትምህርት ከመግባታችን በፊት ስለ ባለፈው ጥቂት እናስታውሳችሁ፡፡ ከዘመን መለወጫ ጋር ተያይዞ ለንግግር የሚጠቅሙንን የመግባቢያ ዓረፍተ ነገሮችና የንግግር ስልቶች አቅርበንላችሁ ነበር፡፡ ይህም ለእናንተ የንግግር ክህሎት በሚረዳ መልኩ አዘጋጅተን ያቀረብንላችሁ በ፳፻፲፬ ዓመተ ምሕረት በድረ ገጹ በቀረቡት ትምህርቶች የተማራችኋቸውን ቃላትም ሆነ ግሦች በመጠቀም እንድትለማመዷቸው በማሰብ ነው፤ ይህንን ተግባራዊ እንዳደረጋችሁትም ተስፋችን ነው፡፡

ታስታውሱ እንደሆነ ያለፈው ዓመት የመጨረሻ ትምህርታችን ስለ ነገረ ግሥና አገባብ ነበር፤ እንደሚታወቀው ዓረፍተ ነገሮችን ለመሥራት የሚጠቅሙን ከስሞች ቀጥሎ በዋነኛነት ግሦች በመሆናቸው በእነርሱ ላይ የበለጠ ትኩረት አድርገን በዚህ ሳምንት ያቀረብንላችሁ ትምህርት ከግሥ ዓይነቶች አንዱ ስለሆነው ‹ረብሐ› ግሥ ነው፡፡

መልእክተ ቅዱስ ፓትርያርክ

‹‹ብርሃን ይሁን!›› (ዘፍ.፩፥፫)

በሥነ ፍጥረት መጀመሪያ ቀን ‹‹ብርሃን ይሁን›› በማለት የተናገረው አምላካችን ልዑል እግዚአብሔር ነው፡፡ (ዘፍ.፩፥፫) ‹‹ብርሃን ይሁን›› በማለት በተናገረ ጊዜም ጨለማ ተገፈፈ፡፡ መጽሐፈ ሥነ ፍጥረት እንደሚነግረን ቅዱሳን መላእክትም ይህ ብርሃን ዕውቀት ሆኗቸው አምላካቸው እግዚአብሔርን ‹‹ቅዱስ ቅዱስ ቅዱስ›› በማለት በአዲስ ምስጋና አመሰገኑት፡፡ ‹‹እኔ ፈጣሪያችሁ ነኝ›› ያለ የሰይጣን ክህደትም በብርሃኑ ተጋለጠ፡፡ (ሊቀ መዘምራን ሞገስ ዕቁበ ጊዮርጊስ መጽሐፈ ሥነ ፍጥረት)

ዓለመ ሰማይ

በዓለመ ሰማይ እግዚአብሔር አምላክ ፍጥረቱን መፍጠር በጀመረበት በመጀመሪያው ቀን እሑድ አስቀድሞ የተፈጠሩት ሰባቱ ሰማያትና መላእክት ናቸው፡፡ ሰማያቱም እንደ ስያሜያቸው የራሳቸው ትርጓሜ አላቸው፡፡

ልሂድ አደን!

ልቤ ተነሣስቶ ጽድቅህን ፍለጋ

ከማዳንህ ጋራ አንተኑ ሊጠጋ

ልሂድ ወደ ዱሩ ከአባቶች ማደሪያ

ከለምለሙ መስክህ ከጽድቅ መነኻርያ

ተአምራትን ፍለጋ

በዚህ ምድር እንደ ክርስቲያን ሆነን ስንኖር የሚገጥሙን ፈተናዎችና አጣብቂኞች ይኖራሉ፡፡ የሚገጥሙንም አንዳንድ ፈተናዎችም ከማስጨነቃቸው የተነሣ በእግዚአብሔር ተአምር እናመልጣቸው ዘንድ እንመኝ ይሆናል፡፡ ይሁን እንጂ ፈተናዎቹ ጸጋና ክብር ሊያሳጡንም ጭምር ስለሚችሉ ተአምራት ተደርገውልን ከምናመልጣቸው በሃይማኖትና በምግባር ጸንተን፣ በጾም በጸሎት ታግሠናቸው ድል ብንነሣቸው የበለጠ ክብርን ልናገኝባቸው እንችላለን፡፡ ከጻድቁ ኢዮብ፣ ከሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ፣ ከደቀ መዝሙሩ ከቅዱስ ጢሞቴዎስም ተግባራዊ ሕይወት ይህን እንማራለን፡፡

እግዚአብሔርን ለማመን በቤቱ ጸንቶ ለመኖር ለሚገጥሙን የዚህ ዓለም መሰናክሎች ሁል ጊዜ ተአምራትን መሻት እግዚአብሔር የሚወደው መንገድ አይደለም፡፡ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በመዋዕለ ሥጋዌ በሚያስተምርበት ወራት ጻፎችና ፈሪሳውያን ወደ እርሱ ቀርበው ‹‹መምህር ሆይ ከአንተ ምልክት እንድናይ እንወዳለን›› አሉት፡፡ እርሱ ግን መልሶ ‹‹ክፉና አመንዝራ ትውልድ ምልክትን ይሻል፤ ከነቢዩም ከዮናስ ምልክት በቀር ምልክት አይሰጠውም፡፡ ዮናስ በዓሣ አንበሪ ሆድ ሦስት ቀንና ሦስት ሌሊት ይኖራል፤ የነነዌ ሰዎች በፍርድ ቀን ተነሥተው ይፈርዱበታል፤ በዮናስ ስብከት ንስሓ ገብተዋልና፤ እነሆም ከዮናስ የሚበልጥ ከዚህ አለ፡፡ ንግሥተ አዜብ በፍርድ ቀን ከዚህ ትውልድ ጋር ተነሥታ ትፈርድበታለች፤ የሰሎሞንን ጥበብ ለመስማት ከምድር ዳር መጥታለችና፡፡ አነሆም ከሰሎሞን የሚበልጥ ከዚህ አለ›› አላቸው፡፡ (ማቴ.፲፪፥፴፰‐፵፪)

ምልክትን (ተአምርን) የሚፈልግ ትውልድ ለምን ክፉና አመንዝራ ተባለ? ‹ክፉ› የተባለው እምነቱን በተአምራት ላይ ስላስደገፈና ስለሚያስደግፍ ነው፡፡ ‹አመንዝራ› የተባለበትም ምክንያት አመንዝራ ሰው ነገሩ አንድ ሲሆን ዕለት ዕለት ሴት (ወንድ) ሊለወጥለት እንዲወድ አይሁድና የአይሁድን መንገድ የሚከተሉ ሰዎችም ዕለት ዕለት ትምህርትና ተአምራት ሊለወጥላቸው ይወዳሉና ነው፡፡

‹‹የለመንከኝን ሁሉ አደርግልህ ዘንድ ቃል ኪዳንን ሰጥቼሃለሁ››

ለሰማንያ ዓመት በጫካ ውስጥ ከአንበሶችና ከነብሮች እንዲሁም ከአራዊት ጋር መኖርን ሳይፈሩ እስከ ሞት ድረስ የታገሡ እንዲሁም በዝቋላ ተራራ ባለው ባሕር ውስጥ መቶ ዓመት ተዘቅዝቀው ለኢትዮጵያ ሰዎች ምሕረትን የለመኑ አባታችን አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ቃል ኪዳን የተቀበሉበትን ጥቅምት አምስት ቀን እናከብር ዘንድ ይገባል፡፡ በሀገረ ግብጽ የተወለዱት ጻድቁ አባት የእግዚአብሔር ትእዛዝ ሆኖ ስለ ኢትዮጵያ ይለምኑና ይማልዱ ዘንድ ፈቃዳቸውም ስለነበር ቤተሰቤን ሆነ ሕዝቤን ሳይሉ ወደ ሀገራችን በመምጣት በጭንቅላታቸው ተዘቅዝቀው ደማቸው ፈሶ እስኪያልቅና ሥጋቸውም አልቆ አጥንቶቻው እንደበረዶ እስኪሆን ድረስ የጸለዩ ታላቅ አባታችን ናቸው፡፡