‹‹ለጠቢብ ሰው ትምህርትን ስጠው፤ ጥበብንም ያበዛል›› (ምሳ. ፱፥፱)

ጥበብ ከእግዚአብሔር አምላክ የሚሰጥ፣ ከሁሉ የበለጠና የላቀ የዕውቀት ሥጦታ እንዲሁም ሰማያዊ ርስትን የሚያወርስ መንፈሳዊ ጸጋ ነው፡፡ በሰዎች አእምሮ ውስጥም ማስተዋልን ያጎናጽፋል፡፡ በዚህም ጸጋ የእውነት መንገድን ማወቅና ጽድቅን መሥራት ይቻላል፡፡ ጠቢቡ ሰሎሞን በምሳሌው እንደተናገረው ‹‹ለጠቢብ ሰው ትምህርትን ስጠው፤ ጥበብንም ያበዛል፤ ጽድቅንም አስተምረው ዕውቀትን ያበዛል፡፡›› (ምሳ. ፱፥፱)

የቤተ ክርስቲያን ሥርዓት

ውድ የእግዚአብሔር ልጆች! ለተከበረው ጤንነታችሁ እንደምን አላችሁ? ነቢየ እግዚአብሔር ንገሥ ክቡር ዳዊት በመዝሙሩ ‹‹… እግዚአብሔር ሕፃናትን ይጠብቃል…›› በማለት እንደተናገረው በእግዚአብሔር ጥበቃ በሰላምና በጤና እንደቆያችሁልን ተስፋችን የታመነ ነው፡፡ (መዝ.፻፲፬፥፮)

የስም ዝርዝር በመራሕያን

ውድ አንባብያን! እንደምን ሰነበታችሁ? ባለፈው ትምህርታችን የግሥ ዝርዝር በዐሥሩ መራሕያን ዓይተን ነበር፡፡ በዚህም ክፍለ ጊዜያችን ለሰጠናችሁ መልመጃ ምላሽና ስሞችን በመራሕያን እንዴት መዘርዘር እንደምችል አዘጋጅተን አቅርበንላችኋል፡፡ መልካም የትምህርት ክፍለ ጊዜ ይሁንላችሁ!

ዕረፍተ አቡነ ሀብተ ማርያም

በተከበረች በኅዳር ፳፮ ቀን ንዑድ ክቡር ንጹሕ መነኰስ ኢትዮጵያዊ ጻድቅ አባታችን አቡነ ሀብተ ማርያም የዕረፍቱ መታሰቢያ ነው። ይህም ቅዱስ አባት የትውልድ ሀገሩ የራውዕይ በምትባል በስተ ምሥራቅ ባለች ሀገር ውስጥ ሲሆን በዚያም ስሙ ፍሬ ቡሩክ የሚባል አንድ ደግ ሰው ነበረ። ይህም ከክቡራን ሰዎች ወገን የሆነ ሰው እጅግ ሀብታምም የነበረ ሲሆን በሕጋዊ ጋብቻ ያጋቡት ቡርክት የሆነች ስሟ ዮስቴና የምትባል ሚስት ነበረችው። እርሷም በበጎ ምግባርና ሥራ የተጌጠች ናት። ይህችውም ደግ እናታችን በሕግ ተወስና ሳለች በጽኑዕ ገድል፣ በጾም በጸሎት በምጽዋትና በስገድትም ትጋደል ነበር።…

ሰማዕቱ ቅዱስ መርቆሬዎስ

የቅዱስ መርቆሬዎስም ወላጆች አስቀድመው አረማውያን ነበሩና የክርስትና ጥምቀትን በጸጋ ተቀበሉ፤ አባቱንኖህ እናቱንም ታቦት ብለው ሰየሟቸው፤ ቀድሞ ፒሉፓዴር የነበረውም ስሙ ተለውጦ መርቆሬዎስ ተባለ፡፡ ‹መርቆሬዎስ› ማለትም የአብ ወዳጅ ማለት ነው፤ ዳግመኛም የኢየሱስ ክርስቶስ አገልጋይ ማለት ነው፡፡ የውሻ መልክ ያላቸው ግን መልአኩ በተገለጠላቸው ጊዜ እንደነገራቸው ለቅዱስ መርቆሬዎስ አባት የሚታዘዙና የሚያገለግሉ ሆኑ፡፡