በእንተ ልደቱ ለአቡነ ተክለ ሃይማኖት

የዳሞት አውራጃ ገዚ ሞተለሚ በነበረበት ቡልጋ ደብረ ጽላልሽ በኢቲሳ መንደር ካህኑ ጸጋዘአብና እግዚኀረያ በትዳር ተወስነው ይኖሩ ነበር። ጸጋ ዘአብ በክህነቱ እግዚኀረያ በደግነቷና በምጽዋት ጸንተው በመኖራቸው በሕጉና በሥርዓቱ ለሚኖሩት ቀናዒ በመሆኑ እግዚአብሔር አምላክ ጎበኛቸው። ሃይማኖታቸውን የሚረከብ፣ እንዳባቱ ጸጋዘአብ የሚባርክ የአብራካቸውን ክፋይ ሊሰጣቸው ወደደ።

ብሥራተ ገብርኤል

ብሥራታዊው መልአክ ቅዱስ ገብርኤል ለእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ተገልጦ ስለ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ከእርሷ መወለድ ያበሠራት ዕለት ታኅሣሥ ፳፪ ‹‹ብሥራተ ገብርኤል›› ታላቅ በዓል ነው፡፡

‹‹እኔ በእግዚአብሔር ፊት የምቆመው ገብርኤል ነኝ›› (ሉቃ.፩፥፲፱)

የእግዚአብሔር መልአክ ቅዱስ ገብርኤል የስሙ ትርጓሜ ‹‹እግዚእ ወገብር፤ አምላክ ሰው ሆነ ሰው አምላክ ሆነ›› ማለት ነው፤ ‹‹ሰላም ለዝክረ ስምከ ዘኢይተረጐም ምሥጢር ባሕቱ ይመስል ብሂለ እግዚእ ወገብር፤ ገብርኤል ሆይ ተመራምሮ ለማይደረስበት ስም አጠራርህ ሰላም እላለሁ፤ ነገር ግን አምላክ ሰው ሆነ ሰው አምላክ ሆነ ማለት ይመስላል›› እንዲል፡፡ (መልክዐ ቅዱስ ገብርኤል)

‹‹ሁል ጊዜ በጌታ ደስ ይበላችሁ›› (ፊልጵ.፬፥፬)

ከመከራው በላይ የእግዚአብሔርን ቸርነት እያሰበ የሚያመሰግን ሰው፥ ዘወትር ደግሞ ከመንፈስ ቅዱስ የተነሣ ደስተኛ ነው። ቅዱስ ጳውሎስ እስር ቤት ሁኖ በደቀ መዝሙሩ በአፍሮዲጡ አማካኝነት በወንጌል ለተከላቸው ተክሎች ምእመናን በላከላቸው መልእክት እንዲህ ይላቸዋል፦ ‹‹ሁል ጊዜ በጌታ ደስ ይበላችሁ፥ ደግሜ እላለሁ ደስ ይበላችሁ!›› (ፊልጵ.፬፥፬)

የቤተ ክርስቲያን አስፈላጊነት

ውድ የእግዚአብሔር ልጆች! ለከበረው ጤንነታችሁ እንደምን አላችሁ? ነቢየ እግዚአብሔር ንገሥ ክቡር ዳዊት በመዝሙሩ ‹‹…ከማኅፀን ጀምሮ በአንተ ላይ ተጣልሁ፤ ከእናቴ ሆድ ጀምረህ አንተ አምላኬ ነህ….›› (መዝ.፳፪፥፲) በማለት እንደገለጸው ከእናታችን ሆድ ጀምሮ የጠበቀን አሁንም በቸርነቱ የሚጠብቀን እግዚአብሔር ይመስገን፤ አሜን!

ባለቤትና ተሳቢ

ውድ አንባብያን! እንደምን ሰነበታችሁ? ባለፈው የትምህርታችን ክፍለ ጊዜ ስሞች በዐሥሩ መራሕያን እንዴት እንደሚዘርዘሩ ዓይተን ነበር፡፡ በዚህም ሳምንት ደግሞ ለሰጠናችሁ መልመጃ ምላሽና ‹‹ባለቤትና ተሳቢ›› በሚል ርእስ እናስተምራችኋለን፡፡ መልካም ትምህርት ይሁንላችሁ!

ዕረፍቱ ለአባ ሳሙኤል ዘዋልድባ

የከበረ ገድለኛ አባት የዋልድባው አባ ሳሙኤል የአባቱ ስም እስጢፋኖስ የእናቱ ስም ደግሞ ዓመተ ማርያም ነው። እነርሱም በዘመድ የከበሩ ደጋግ ናቸው፤ እነርሱም በአክሱም ሀገር ሲኖሩ ሁለት ልጆችን ወለዱ። አንደኛው ስሙ ገብረ ክርስቶስ ሲሆን ይህ ሁለተኛው ደግሞ የእግዚአብሔር ሰው አባ ሳሙኤል ነው።

ሰማዕቷ ቅድስት አርሴማ

ቅድስት አርሴማ ከሃያ ሰባቱ ደናግል ጋራ ሰማዕትነት ከተቀበለች በኋላ የቅዱሳን ሰማዕታቱን ዕፅም ፍልሠታቸው በዚህ በቅዱስ ጎርጎርዮስ እንዲደረግ ሆነ፤ ይህም ታኅሣሥ ስድስት ቀን ነው፡፡ እንዲሁ ደግሞ የእርሷ ማኅበርተኞች የሚባሉ የመቶ ዐሥራ ዘጠኝ ሰማዕታት ዝክራቸው ነው። ከዚያም በስሟ ያማረ ቤተ ክርስቲያን ሠርተው እንዲሁ አከበሩበት።

ዘመነ ስብከት

ዘመነ ስብከት ከጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የልደት በዓል በፊት ከታኅሣሥ ፯ ጀምሮ እስከ ፳፱ ያለው ወቅት ነው፡፡ ሳምንታቱም ስብከት፣ ብርሃንና ኖላዊ ይባላሉ፡፡ በዚህም ወቅት ስለ ጌታችን ኢየሱስ  መወለድ ነቢያት የተናገሩት ትንቢት ይሰበክበታል፡፡

በዓታ ለማርያም

ንጽሕተ ንጹሐን፣ ቅድስተ ቅዱሳን፣ ከተመረጡ የተመረጠች፣ ከተለዩ የተለየች፣ ከተከበሩ የተከበረች እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ቤተ መቅደስ የገባችበት ታኅሣሥ ፫ ቀን ‹‹በዓታ ለማርያም›› በቅድስት ቤተ ክርስቲያናችን በድምቀት ይከበራል፡፡