ዐቢይ ጾም

ዐቢይ ማለት ታላቅ የከበረ ማለት ሲሆን ዐቢይ ጾም ጌታችን አምላካችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ከተጠመቀ በኋላ በገዳመ ቆሮንቶስ ዐርባ መዓልትና ዐርባ ሌሊት ከቆመ ሳያርፍ ከዘረጋ ሳያጥፍ በትኅርምት የጾመው ታላቅ ጾም ነው፡፡ በተለይም የዲያብሎስን ሦስቱን ፈተናዎች ውድቅ ያደረገበት፤ በፍቅረ ንዋይ የመጣውን በጸሊዐ ንዋይ በትዕቢት የመጣውን በትሕትና በስስት የመጣውን በቸርነት ድል ያደረገበትም ነው፡፡ (ማቴ. ፬፥፩)

‹‹ወደ እኔ ተመለሱ፤ እኔም ወደ እናንተ እመለሳለሁ›› (ሚል ፫፥፯)

የሰው ልጆችን ጥፋት የማይወደው ፈጣሪያችን እግዚአብሔር በንስሓ እንድንመለስ ይሻል፤ ‹‹ወደ እኔ ተመለሱ፤ እኔም ወደ እናንተ እመለሳለሁ›› ብሎም ዘወትር ወደ እርሱ ይጠራናል፡፡ (ሚል ፫፥፯)