google play news 4

«ተዋሕዶ ለአንድሮይድ» የተሰኘ የስልክ ላይ አገልግሎት ተጀመረ

 የካቲት 17 ቀን 2006 ዓ.ም.

በዝግጅት ክፍሉ ሪፖርተር

 google play news 4

google play news 2በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ማኅበረ ቅዱሳን የሰሜን አሜሪካ ማእከል ሚድያና ቴክኖሎጂ ክፍል «ተዋሕዶ ለአንድሮይድ» የተሰኘ የቴሌፎን አገልግሎት መስመር ዘረጋ፡፡ አገልግሎቱ በተለይ የእጅ ስልካቸው ወይም የኪስ ኮምፒዩተራቸው /ታብሌት/ አንድሮይድ በተሰኘው ግብረ ቴክኖሎጂ /ኦፕሬቲንግ ሲስተም/ አማካይነት የሚሠራ ምእመናን በያሉበት ኾነው በቀላሉ ልዩ ልዩ ትምህርቶችን፣ መዝሙራትን፣ የዕለትና የበዓላት ንባባትን /ግጻዌን/፣ በድምጽና በምስል የቀረቡ መንፈሳዊ ትረካዎችንና ጭውውቶችን፣ ልዩ ልዩ የጸሎት መጻሕፍትን እንዲሁም በሰሜን አሜሪካ በልዩ ልዩ ግዛቶች ስለሚገኙ አብያተ ክርስቲያናት መረጃዎችን በቀላሉ እንዲያደርስ ኾኖ የተዘጋጀ ነው፡፡ 

 

 

ክፍሉ ለዝግጅት ክፍላችን በላከው መግለጫ እንዳሳወቀው ቀደም ሲል ተመሳሳይ አገልግሎት አይ ፎንን መሠረት በማድረግ ሲጀምር ለምእመናን ቃል በገባው መሠረት፤ አገልግሎቱ በአንድሮይድ ግብረ ቴክኖሎጂም ይሰፋ ዘንድ የጀመረው መኾኑንgoogle play news 3 ገልጿል፡፡

ይህንን አገልግሎት ለማግኘት የሚሹና አንድሮይድ የተሰኘውን ግብረ ቴክኖሎጂ የሚጠቀሙ የእጅ ስልክ ወይም የኪስ ኮምፒዩተር ያላቸው ሁሉ አገልግሎት ማግኛ መንገዱን /አፕሊኬሽኑን/ ከጎግል ፕሌይ ስጥ ተዋሕዶ ከሚለውን የአገልግሎት ማዕቀፍ በመጫን መጠቀም እንዲችሉ ክፍሉ በአክብሮት ጋብዟል፡፡ ምእመናን ይህንን ጠቃሚ አገልግሎት ላልሰማ በማሰማት እንዲተባበሩም ጠይቋል፡፡

 

ሐዊረ ሕይወት ወደ አዲስ ዓለም ማርያም ቤተ ክርስቲያን ሊካሄድ ነው

 

የካቲት 14 ቀን 2006 ዓ.ም.

ዲ/ን ቴዎድሮስ ኃይሉ

በዚህ ዓመት ለሁለተኛ ጊዜ የታሰበው ሐዊረ ሕይወት ወደ ርእሰ አድባራት ወገዳማት አዲስ ዓለም ደብረ ጽዮን ማርያም ቤተ ክርስቲያን መጋቢት 21 ቀን 2006 ዓ.ም ሊካሄድ መሆኑን፤ የማኅበረ ቅዱሳን ምክትል ዋና ጸሐፊና የጉዞው ኮሚቴ ሰብሳቢ አቶ ግርማ ተሾመ ገለጹ፡፡

ስብከተ ወንጌልን ማስፋፋት የጉዞው ተቀዳሚው ዓላማ መሆኑን አቶ ግርማ ተናግረው፤ በዕለቱ በብፁዐን አበው ሊቃነ ጳጳሳት ቃለ ምዕዳንና ቡራኬ፤ ስብከተ ወንጌል በሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያን የሚሰጥ ከመሆኑ በተጨማሪ የቅኔ መምህራን ቅኔ የሚቀኙበት፤ ዘማርያንም ወረብና መዝሙር የሚያቀርቡበት መሆኑ ተገልጠዋል፡፡ በመሆኑም በወርኃ ጾም በሚከናወነው ጉዞ በመሳተፍ ምእመናን ነፍሳቸውን በወንጌል ያለመልሙ ዘንድ አቶ ግርማ አሳስበዋል፡፡

በመርሐ ግብሩ በማኅበረ ቅዱሳን አገልግሎት ላይ የግንዛቤ ማስጨበጫ ገለጻ ይሰጣል ያሉት ሰብሳቢው፤ የማኅበረ ቅዱሳንን አገልግሎት ያልተረዱ ሰዎች ካሉም በመርሐ ግብሩ በመገኘት ማኅበሩ ለቤተ ክርስቲያን፣ ለሀገር ብሎም ለዓለም እያበረከተ ያለውን መንፈሳዊ ዕሴቶችን መገንዘብ እንደሚችሉ አስታውቀዋል፡፡

የማኅበረ ቅዱሳን አገልግሎት ዘርፈ ብዙና የምእመናንን ተሳትፎ የሚጠይቅ በመሆኑ ምእመናን የድርሻቸውን እንዲወጡ ማስቻል የጉዞው ተጨማሪ ዓላማ መሆኑን ያስታወሱት ሰብሳቢው፤ በገንዘብ፣ በጉልበት እንዲሁም በአሳብ የቤተ ክርስቲያንን አገልግሎት እንዲደግፉ መርሐ ግብሩ ያግዛል ብለዋል፡፡ አያይዘውም ተጓዦች የጉዞውን ትኬት ከማኅበሩ ጽ/ቤትና ሱቆች ማግኘት እንደሚችሉ ጠቁመዋል፡፡

ርዕሰ አድባራት ወገዳማት አዲስ ዓለም ደብረ ጽዮን ማርያም ቤተ ክርስቲያን በምዕራብ ሸዋ ሀገረ ስብከት ከአዲስ አበባ 55 ኪ.ሜ ርቀት ላይ ትገኛለች፡፡ ታቦተ ማርያም ከዐፄ ዘርዐ ያዕቆብ ዘመን ጀምሮ በቤተ መንግሥት አካባቢ እንደቆየችና በዐፄ በዕደ ማርያም ዘመነ መንግሥት መንዝ ውስጥ ቤተ ክርስቲያን ታንፆላት ምስሐለ ማርያም ተብላ በታልቅ ክብር ነበረች፤ በግራኝ መሐመድ ጊዜ ንጉሡ ሲሰደዱ ታቦቷን ከመቅደስ አውጥተው በአካባቢው በሚገኝ ዋሻ በባህታውያን ሲጠብቋት ኖረዋል፡፡ በተለይ ከዐፄ ምኒልክ ዘመን ጀምሮ የቤተ ምንግሥትና የቤተ ክርስቲያንን ታሪክ የሚያሳዩ ቅርሶች የሚገኙባት ደብር መሆኗን የታሪክ ድርሳናት ያስረዳሉ፡፡

 

ged te 2006

ለአብነት መምህራኑ የህክምና ምርመራ ተደረገ፡፡ ክብካቤና ክትትል ካልተደረገ ለዐይነ ስውርነት ሊዳረጉ ይችላሉ፡፡

 የካቲት 13 ቀን 2006 ዓ.ም.

 
መ/ር ሳሙኤል ተስፋዬ

በቅርቡ ለሦስተኛ ጊዜ በማኅበረ ቅዱሳን አዘጋጅነት ሊካሄድ የነበረውን የአብነት መምህራን ሀገር አቀፍ ጉባኤ ላይ ለመሳተፍ  ከመጡት 202 ሊቃውንት ከ70 በላይ የአብነት መምህራን ካታራክት እና ትራኮማ ችግር እንዳለባቸው ተገለጸ፡፡ክብካቤና ክትትል ካልተደረገ ለዐይነ ስውርነት ሊዳረጉ እንደሚችሉ  የማኅበሩ የሞያ አገልግሎት ዋና ክፍል የሕክምና  ቡድን ገለጸ፡፡

ged te 2006

ማኅበሩ ባቋቋመው ጊዜያዊ ክሊኒክ ለ170ዎቹ ለምስክር መምህራኑ የውስጥ ደዌ፣ የዐይን፣ የነርቭ፣ የአጥንትና ሌሎችም የበሽታ ዐይነቶች ላይ በስፔሻሊስቶች ባካሔደው ምርመራ ከ70 በላይ የአብነት መምህራን ካታራክት እና ትራኮማ ችግር እንዳለባቸው ተረጋግጧል፡፡

ምርመራውን ከምኒልክ ሆስፒታልና ሌሎች የግል የሕክምና ማእከላት ጋራ በመተባበር ማከናወኑን የገለጸው የማኅበሩ የሞያ አገልግሎት ዋና ክፍል የሕክምና  ቡድኑ አባላት ፤የሊቃውንቱ ዐይን ህመም ሊከሰት የቻለው የአብነት መምህራኑ የሚጠቀሙባቸው ጧፎች ቀለም ተቀላቅሎባቸው የሚመረቱ በመሆናቸው ጢሱ እየጎዳቸው በመሆኑ፣ በድንግዝግዝ ብርሃን ማንበባቸው፣ የግል ንጽሕና አጠባበቅና ዕድሜ ከዐይን ጋራ ተያይዞ እንደሆነ ተገለጾ ፤ክብካቤና ክትትል ካልተደረገ ለዐይነ ስውርነት ሊዳረጉ እንደሚችሉ ተገልጿል፡፡

የህክምና ቡድኑ ለ50ዎቹ የንባብና የፀሐይ መነጽሮች የታደለ ሲሆን፤ ከዐሥር ሺሕ ብር በላይ ግምት ያላቸው መድኃኒቶች እንዲያገኙ ያደረገ ሲሆን መነጽር ላላገኙትም ድጋፍ እየጠየቀ መሆኑ ተገልጿል፡፡

ቡድኑ መምህራኑና ተማሪዎቻቸው ከሚጠቀሙባቸው ያልታከመ የወንዝና የምንጭ ውኃ ጋራ የተያያዙ ውኃ ወለድ የሆድ ሕመሞች፣ የቆዳ በሽታዎች በዚሁ አጋጣሚ በተደረገ የጤና ምርመራ ታውቀው ጊዜያዊ መድኃኒት መሰጠቱን ተነግሯል፡፡ በመጪው ዐብይ ጾምም በየአህጉረ ስብከቱ በግል ጤና አጠባበቅና በመከላከል ላይ ያተኮረ የጤና አጠባበቅ ሥልጠና ለመስጠት ዝግጅቱን ማጠናቀቁንም አመልክቷል፡፡
   

 

 

megelecha 2006

ቅዱስ ፓትርያርኩ ዐብይ ጾምን አስመልክቶ ቃለ ምዕዳን አስተላለፉ

 የካቲት 13 ቀን 2006 ዓ.ም.

ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማቲያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት የ2006 ዓ.ም. ዐቢይ ጾም አስመልክቶ እንኳን በሰላም አደረሳችሁ ባሉበት ወቅት “ጾም ለመንፈሳዊ ሕይወት መጎልበት፣ ራስን ለመግዛት፣ ከእግዚአብሔር ጋር ልዩ ግንኙነትና አንድነት ለመፍጠር እጅግ አስፈላጊ ነው” ሲሉ ተናግረዋል፡፡

ቅዱስነታቸው ዐብይ ጾሙን አስመልክቶ ያስተላለፉትን ሙሉ ቃል ከዚህ በታች ይመልከቱ፡፡

 megelecha 2006

 

ዐቢይ ጾም

 የካቲት 13 ቀን 2006 ዓ.ም.

ሊቀ ጉባኤ ቀለመ ወርቅ ውብነህ

ጾም ማለት መተው መከልከል ማለት ነው፡፡ ቤተ ክርስቲያናችን ሥርዓት ሠርታ ጾመን ከአምላካችን ጋር ህብረት እንዲኖረን ፤መንፈሳዊ ኃይል እንድናገኝ አድርጋለች፡፡ ጾም በእግዚአብሐር የተቀደሰ ስለሆነ ወደ ቅድስና ጎዳና የሚመራ ነው፡፡

በጾም ወራት ከመባልዕት መከልከል ብቻ ሳይሆን ዐይን ክፉ ከማየት አንደበት ክፉ ከመናገር ጆሮ ክፉ ከመስማት መቆጠብ እንደሚገባ ተጽፎአል፡፡ “ይጹም ዐይን፣ ይጹም ልሳን፣ እዝንኒ ይጹም እምሰሚዓ ኀሡም በተፋቆሮ” /ቅዱስ ያሬድ ጾመ ድጓ/፡፡ በጾም ወራት፣ ላምሮት፣ ለቅንጦት፣ የሚበሉ ወይም ለመንፈሳዊ ኃይል ተቃራኒ የሆኑ ሥጋዊ ፍትወትን የሚያበረታቱ፣ ሥጋንና የሚያሰክሩ መጠጦችን /ዳን.10፥2-3/ ቅቤና ወተትን ማራቅ ታዟል፡፡ /መዝ.108፥24፣ 1ቆሮ.7፥5፣ 2ቆሮ.6፥6/

በብሉይ ኪዳን ጾም ከፍተኛ ቦታ አለው፡፡ የብሉይ ኪዳን ነቢያት ከእግዚአብሔር በሚገናኙበት ወራት እህልና ውኃ በአፋቸው አይገባም ነበር፡፡ /ዘፀ.34፥28/አስቴር አስቀድማ ሦስት ቀን ጾማ ጸልያ በእስራኤል ላይ የመጣውን መቅሰፍት እንዲመለስ አድርጋለች፡፡አስ4፡15-16 በኃጢአት ብዛት የታዘዘው የእግዚአብሔር መዓት የሚመለሰው ሕዝቡ በጾም ሲለምኑትና ሲማልዱት ነበር፡፡ /ዮና.2፥7-10/

በሐዲስ ኪዳንም ጾም ሰው ሠራሽ ሕግ ሳይሆን እራሱ ክርስቶስ የሥራ መጀመሪያ አድርጎ የሠራው ሕግ ነው፡፡ /ማቴ.4፥2፣ ሉቃ.4፥2/ ይህም ብቻ ሳይሆን በቁራኝነት ተቆራኝቶ አብሮ የሚኖር መንፈሰ ርኩስ ሰይጣን እንኳን በጾም የሚወገድ መሆኑን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ተናግሮአል፡፡ ማቴ.17፥21፣ ማር.9፥2

ቤተ ክርስቲያንን እንዲያገለግሉ የታዘዙ ሐዋርያትም በየጊዜው ከመንፈስ ቅዱስ ትእዛዝ የሚቀበሉት በጾም በጸሎት ላይ እንዳሉ ነበር፡፡ /የሐዋ.ሥራ.13፥2/ ለስብከተ ወንጌል የሚያገለግሉ ዲያቆናትና ቀሳውስትም የሚሾሙት በጾምና በጸሎት ነበር፡፡ /የሐ. ሥራ.13፥3፣ 14፥23/ እነቆርኔሌዎስ ያላሰቡትን ያዩና ያገኙ የነበረው በጾምና በጸሎት ፈጣሪያቸውን ማልደው ነው፡፡ /የሐ. ሥራ.10፥30/

ዐቢይ ጾምም ቤተክርስቲያናችን እንድንጾም ካወጀችልን ጾም አንዱ ነው፡፡ዐቢይ ጾምየተለያዩ ስሞች አሉት፡፡ አንደኛ ጌታችን መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ከተጠመቀ በኋላ የጾመው የአርባ ቀን ጾም በመሆኑ እንዲሁም ዐቢይ እግዚአብሔር ወዓቢይ ኀይሉ ዓቢይ እግዚአብሔር ወብዙኃ አኰቴቱ የተባለ ጌታ የጾመው ስለሆነ፣ /መዝ.47፥1፣ መዝ.146፥5/፡፡ ሁለተኛ ሁዳዴ ጾም ይባላል፡፡ ይህም የመንግሥት እርሻ ወይም ማንኛውም የሕዝብ ብዛት ያለበት ሥራ ሁዳድ ስለሚባል ሲሆን ከአጽዋማት ሁሉ ብዙ ቀናት ስለሚጾምና ኃያሉ አምላካችን ስለጾመው ነው፡፡፣ /አሞ.7፥1/፡፡ ሦስተኛ በዓተ ጾም ይባላል፡፡የጾም መግቢያ፣ መባቻ ወይም ጾሙ የሚሰፍርበት በዓት ማለት ነው፡፡ አራተኛ ጾመ አርባ ይባላል፡፡ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የጾመው 40 /ዓርባ/ ቀን ስለሆነ፣ /ማቴ.4፥1/ አምስተኛ ጾመ ኢየሱስይባላል፡፡ ጾሞ፣ ጹሙ ብሎ ስላዘዘን፣ ስድስተኛ ጾመ ሙሴ ይባላል፡፡ ቅዱስ ያሬድ በዘወረደ ሰኞ ዕዝል ከመዝ ይቤ ሙሴ እስመ ለዓለም፣ ሙሴኒ ይቤ በውስተ ኦሪት እያለ በጾመ ድጓ ስለ ዘመረ ነው፡፡

ዐቢይ ጾምጌታ ከተጠመቀ በኋላ የጾመው የአርባ ቀን ጾም ነው፡፡ ማቴ.4፥1 ምእመናን ጌታቸው ያደረገውን ምሳሌ ተከትለው ይጾሙታል፡፡ ዐቢይ ጾም ስምንት ሳምንታት /55 ቀኖች/ አሉት፡፡ ሰባት ቅዳሜ ስምንት እሑድ ይገኛሉ፡፡ አሥራ አምስት ቀን ማለት ነው፡፡ ከጥሉላት እንጂ ከእህል ውኃ ስለማይጦሙ የጦሙ ወራት አርባ ቀን ብቻ ይሆናል፡፡

ዘወረደ /ዘመነ አዳም/

የዐቢይ ጾም የመጀመሪያ ሳምንት ዘወረደ ይባላል፡፡ ዘወረደ ማለት፣ ከላይ የመጣ፣ የወረደ ማለት ነው፡፡ ይህም የአምላካችን ሰው መሆን ያመለክታል፡፡ ከሰማይ ከወረደው በቀር ወደሰማይ የወጣ የለም ካለው ከጌታችን ከመድኃኒታችን ከኢየሱስ ክርስቶስ ቃል በመነሳት ሊቁ ቅዱስ ያሬድ በዚህ ዕለት ምስባክ “ዘወረደ እምላዕሉ አይሁድ ሰቀሉ ወሚመ ኢያእመሩ እግዚአ ኩሉ ዘየሐዩ በቃሉ” በማለት በጾመ ድጓው መጀመሪያ ላይ ገልጾት ይገኛል፡፡

አዳምን ለማዳን ከሰማይ የወረደውን አይሁድ ሰቀሉት፣ የሰማይን ሥልጣን ያለው የሁሉ ጌታ እንደሆነም ምንም አላወቁም ብሎ ተናግሮ ነበር፡፡ ይህም ድርሰት በቤተ ክርስቲያናችን የጾም መጀመሪያ የሆነው ዕለተ ሰንበት ዋዜማ፣ መግቢያ፣ /መሐትው/ ሆኖ ከዋዜማ በፊት ምንጊዜም በየዓመቱ ይቆማል፡፡ ይዘመራል፡፡ ይመሰገናል ማለት ነው፡፡

ስለዚህ የሳምንቱ ስያሜ ከዚህ የተወሰደ ነው፡፡ እንዲሁም ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የማዳን ሥራውን የጀመረው፤ ከሰማየ ሰማያት ወርዶ ሰው በመሆን ፣ በዮርዳኖስ ተጠምቆ በማስተማር እንደሆነ ሁሉ የመጀሪያው ሳምንት ዘወረደ ይባላል፡፡
በዚህ ሳምንት በተለይም እሑድና ሰኞ የሚነገሩት ውዳሴያት ከመጻሕፍተ ኦሪትና ነቢያት የተወሰዱ ናቸው፡፡ ሁለተኛም ሙሴኒ በመባል ይታወቃል፡፡ እግዚአብሔር አምላክ አዳምን ለማዳን ከሰማይ መውረዱንና በመስቀል መሰቀሉን ስለሚያወሳ ነው፡፡

በተጨማሪም ይህ የመጀመሪያው ሳምንት ጾመ ሕርቃል ይባላል፡፡ በ714 ዓ.ም.ሕርቃል /ኤራቅሊየስ/ የቤዛንታይን ንጉሥ ነበረ፡፡ይህ ሳምንት በስሙ የተጠራበት ምክንያት በዘመኑ ፋርሶች ኢየሩሳሌምን ወርረው የጌታችን መስቀል ማርከው ወስደው ነበር፡፡ እርሱ ወደፋርስ ዘመቶ መስቀሉን ከእነርሱ ነጥቆ ይዞ ወደ ኢየሩሳሌም ተመልሷል፡፡

ሕርቃል ከፋርሶች ጋር ከመዋጋቱ በፊት ሐዋርያት በሲኖዶሳቸው ነፍስ የገደለ ሰው እስከ እድሜ ልኩ ይጹም ብለው ሥርዓት ሠርተዋልና ጾሙን ፈርቶ ስለነበር በኢየሩሳሌም የነበሩ ምእመናን አሳቡን ደግፈው “አንተ ጠላታችንን አጥፋልን ፣መስቀሉን አስመልስልን እንጂ የአንድ ሰው እድሜ ቢበዛ ሰባ ሰማንያ ነው ፡፡ጾሙንአምስት አምስት ቀን ተከፋፍለን እኛ ተከፋፍለን እንጾምልሃለን፡፡”ብለው ጾመውለታል፡፡

ይህንን መሠረት በማድረግ ያላወቁት አንድ ጊዜ ጾመው ትተውታል፡፡ ያወቁት ግን ቀድሞም ሐዋርያት ጾመውታል ብለው ሥርዓት አድርገው በዓመት በዐቢይ ጾም መጀመሪያ ላይ ጾመ ሕርቃል እያሉ የሚጾሙት ሆነዋል፡፡ስለዚህ ቤተክርስቲያናችን ይህንን መሠረት በማድረግ በጌታችን ከመድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ጾም የመጀመሪያውን ሳምንት ጾመ ሕርቃል በሚል ስያሜ ሰማይ እንዲጾም አድርጋለች፡፡ /መጋቢት 10 ስንክሳር ይመልከቱ፡፡/

የቤተ ክርስቲያናችን ታሉቁ ሊቅ ቅዱስ ያሬድ፣ በዘወረደ ጾመ ድጓው ሰንበት ለሰው ልጆች ብቻ ሳይሆን፣ ሕይወት ላለው ነገር ሁሉ ጸጥታና ሰላም የሰፈነባት የዕረፍት ቀን ስለመሆኗ “አዘዞ እግዚአብሔር ለሙሴ ወይቤሎ ሰብዕከ ወላህምከ ወኲሉ ቤትከ ያዕርፍ በሰንበት” ዘፀ.20፥10፣23፣12፣ ጾመ ድጓ፣ እግዚአብሔር ሙሴን ሕዝብህ የከብትህ መንጋህ ቤተሰብህ ሀሉ በሰንበት ቀን ከድካማቸው ይረፉ በማለት አዘዘው ይላል፡፡ በዚህም ዘመነ ጾም፣ ወይም ጾመ ሙሴ ይባላል፡፡

በጾመ ድጓው ዘወረደ እየተባለ የሚታወቀው፣ በጾመ አርባው ወቅት በተለይም በመጀመሪያው ሳምንት የሚገኘው ያሬዳዊ ድርሰት በነግህ በሠለስት፣ በቀትርና በሠርክ እንዲሁም ቅዳሜና እዡድ በሌሊት የሚዘመር ነው፡፡ በውስጡም የያዘው ፍሬ አሳብ፣ የጾምን፣ የጸሎትን፣ የምጽዋትንና የፍቅርን ጠቃሚነት አጉልቶ የሚያስተምር ነው፡፡

በዚህ በጾም ወቅት በቤተ ክርስቲያናችን ሥርዓት በአብዛኛው ከቅዱስ ያሬድ ድርሰቶች ውስጥ የሚዘመረው ምዕራፍ የተባለው ነው፡፡ ምዕራፍ የተባለበት ምክንያትም በየመዝሙራቱ መሀል ሃሌታና ድጓ እያስገባ ለመዝሙሩ ማረፊያ ስላበጀለት በዚህ ምክንያት ምዕራፍ የሚል ስያሜ ሊያገኝ ችሏል፡፡ ይህ የዜማ መጽሐፍ በሁለት ታላላቅ ክፍሎች ይከፈላል፡፡ ይኸውም የዘወትር ምዕራፍና የጾም ምዕራፍ በመባል ይታወቃል፡፡የዘውትር ምዕራፍ የሚባለው በዓመቱ ውስጥ ባሉት ቀናት ውስጥ ሳምንታትና በዓላት ሁልጊዜ በአገልግሎት ላይ የሚውል ሲሆን፣ የጾም ምዕራፍ የሚባለው ደግሞ በጾመ አርባ ብቻ ለአገልግሎት የሚውል ነው፡፡

ከዚህም በተጨማሪ በዐሥሩ ምህላት አርዕስተ ምህላ በዚሁ ክፍል ይካተታል፡፡ የምዕራፍ ቅንብር ከመዝሙረ ዳዊት፣ ከድጓና ከጾመ ድጓ ጋር የተቀናጀ ነው፡፡ የትምህርት አሰጣጡም እንደ ድጓው ወይም እንደ ዝማሬ መዋሥዕቱ መጽሐፍ ተዘርግቶ ሳይሆን በቃል የሚጠናና የሚወሰን ነው፡፡ ስለሆነም ምዕራፍን ለመማር 150 መዝሙረ ዳዊትን፣ ከነቢያት 15 ምዕራፎችንና 5 መኃልያተ ሰሎሞንን በቃል ሸምድዶ መያዝ ይጠበቅበታል፡፡ ወይም ግድ ነው፡፡

ጾምን መጾም የፈቃድ ብቻ ሳይሆን የትእዛዝም ነው፡፡ በዘመነ ብሉይ ነቢዩ ኢዩኤል “ቀድሱ ጾመ ወስብኩ ምህላ” ጾምን ያዙ አጽኑ ምሕላንም ዐውጁ ሸማግሌዎቹን ከፈጣሪያችን ቤት ሰብስባችሁ በአንድነት ሁናችሁ ወደ እግዚአብሔር ጩሁ /ለምኑ/ ብሏል፡፡ ኢዮ.ምዕ.1፥11፣ 2፣12፣15-16 ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስም ወኲኑ ላዕካነ፣ ለእግዚአብሔር በጾም ወበንጽሕ፡፡ በጾም፣ በንጽሐና ተወስናችሁ እግዚአብሔርን አገልግሉ ብሏል 2ቆሮ.6፥4-6፡፡

ጾም ከሌለ ወይም ተገቢ ካልሆነ ጌታችን በምትጾሙበት ጊዜ እንደ ግብዞች አትሁኑ ስለ ጽድቅ የሚራቡ የሚጠሙ ንዑዳን ክብራን ናቸው ለምን አለ? ማቴ.5፥፣6፣16፡፡ ነቢዩ ዳዊትም ሰውነቴን በጾም አሳመምኳት በቀጠና፣ በሰልት አደከምኳት ለምን አለ መዝ.34፥68፣ ት.ዳን. 9፥3-4፣ 14፥5

ነብዩ ሚኪያስ ሐዋርያት ሙሸራውን ከነሱ ለይተው የሚወስዱበት ጊዜ ይመጣል ያን ጊዜ ይጾማሉ ያለውን የጌታን ቃል መሠረት በማድረግ ክርስቶስ በሞት ከተለያቸው በኋላ ጾመዋል፡፡ ጾምንም ሠርተዋል የሐዋ.ሥራ 13፥3፡፡ ሠለስቱ ምዕትም ሐዋርያት የጾሙትንና እንዲጾም የወሰኑትን መጾም ይገባል ብለው ቤተ ክርስቲያን የተቀበለቻቸውን አጽዋማት እንዲጾሙ መወሰናቸው ይህን የጌታ ቃል መሠረት በማድረግ ስለሆነ፣ የትእዛዝ መሆኑን ተገንዝበን መጾም አለብን፡፡ ጌታችን መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስም ሠራዔ ሕግ እንደመሆኑ አርባ ቀን አርቦ ሌሊት ጾመ እንጂ እርሱ ሳይጾም ጾሙ አላለንም ማቴ.4፥2፡፡ ጾመን ለማበርከት ያብቃን፡፡

ይቆየን

 

ten 2006 02

የማኅበረ ቅዱሳን ጥናትና ምርምር ማእከልን ወደ ተቋምነት ለማሳደግ ምክክር ተካሄደ

 የካቲት 13 ቀን 2006 ዓ.ም.

በመ/ር ሳሙኤል ተስፋዬ

ten 2006 02ከ1998 ዓ.ም. ጀምሮ በማእከልነት ደረጃ ተቋቁሞ በጥናትና ምርምር፣ በቤተመጻሕፍት፣ በቤተ መዛግብትና ቋሚ ኤግዚቢሽን አገልግሎት እየሰጠ የሚገኘው የማኅበረ ቅዱሳን ጥናትና ምርምር ማእከል ወደ ተቋምነት እንዲያድግ የምክክር ጉባኤ በማኅበሩ የስብሰባ አዳራሽ በ11/06/06 ተካሄደ፡፡

በተካሄደው የምክክር ጉባኤ ብፁዕ አቡነ ሉቃስ የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊ፣ የሴቲት ሁመራ ሊቀ ጳጳስና የማኅበረ ቅዱሳን ጥናትና ምርምር አማካሪ ቦርድ ሰብሳቢ፣ የማኅበሩ የሥራ አመራርና ሥራ አስፈጻሚ አባላት፣ የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ምሁራን ተሳታፊ ሆነዋል፡፡ የምክክር ጉባኤው በጸሎት የተከፈተው በብፁዕ አቡነ ሉቃስ ሲሆን፤ የምክክር ጉባኤው የመነሻ ጥናት ይዘው የቀረቡት ደግሞ የጥናትና ምርምሩ አማካሪ ቦርድ አባልና የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የታሪክ ምሁሩ ፕሮፌሰር ሽፈራው በቀለ ናቸው፡፡

ten 2006 01ፕሮፌሰር ሽፈራው በቀለ ባቀረቡት የመነሻ ሐሳብ የማኅበሩ ጥናትና ምርምር ማእከል እያበረከተ ያለውን አስተዋጽኦ፣ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ሐዋርያዊ አገልግሎትና የጥናት ተቋም ባለመኖሩ እያስከተለ ያለውን ተግዳሮት፣ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን እምነት ተከታዮች ቁጥር በየጊዜው እያሽቆለቆለ መሄዱ ያለውን አሳሳቢነት፣ የማኅበረ ቅዱሳን ጥናትና ምርምር ማእከልን ወደ ተቋምነት ማሳደግ ያለውን ጠቀሜታና ትኩረት ሊሰጣቸው የሚገቡ ጉዳዮችን አስረጅ በማቅረብ አስረድተዋል፡፡

ከጥናት አቅራቢው በመቀጠል ንግግር ያደረጉት ብፁዕ አቡነ ሉቃስ ጥናትና ምርምር ለቤተ ክርስቲያን በጣም አስፈላጊ መሆኑንና ትኩረት ሊሰጠው እንደሚገባ ጠቅሰው ማእከሉን ወደ ተቋምነት ለማሳደግ በሚደረገው ጥረት ፕሮፌሰር ሽፈራው በቀለ ከፍተኛ ሚና እንዲጫወቱ አባታዊ አደራ ጥለውባቸዋል፡፡

ጉባኤውን በአወያይነት ሲመሩ የነበሩት በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የፊሎሎጂ ትምህርት ክፍል ሓላፊና መምህር የሆኑት ዶ/ር አምሳሉ ተፈራ፤ ጥናትና ምርምር ለቤተ ክርስቲያን ሊያበረከት የሚችለውን ከፍተኛ አስተዋጽኦ በመግለጽ ማኅበሩ የጀመረውን አገልግሎት ለመደገፍ በተሰማሩበት መስክ ድጋፍ እንደሚያደርጉ ገልጸዋል፡፡ በምክክር ጉባኤው የተገኙት የማኅበሩ አመራር አባላት ለጥናት አቅራቢው የተለያዩ ጥያቄዎች አቅርበው ሰፊ ገለጻ ተደርጎላቸዋል፡፡

 

dasa 2006

የደሴ ማእከል ቅዱሳት መካናትና ማኅበራዊ አገልግሎት ክፍል ስለቤተ ክርስቲያን ዘላቂ ልማት ከበጎ አድራጊዎች ጋር ውይይት አካሄደ፡፡

 የካቲት 13 ቀን 2006 ዓ.ም.

ወርቁ በላይሁን ከደሴ ማእከል

የደሴ ማእከል ቅዱሳት መካናትና ማኅበራዊ አገልግሎት ክፍል “ለቤተ ክርስቲያን ሁለንተናዊ እድገት በጋራ እንሥራ” በሚል መርህ ከደሴ ከተማ በጎ አድራጊዎች ጋር ቤተ ክርስቲያን በዘላቂነት ራሷን ለማስቻል እንዲረዳ ጥር 25 ቀን 2006 ዓ.ምdasa 2006 የግማሽ ቀን ውይይት አደረገ፡፡

መርሐ ግብሩ በጸሎት ተከፍቶ የበገና መዝሙር ከቀረበ በኋላ ስለቦሩ ደብረ ብርሃን ቅድስት ሥላሴ፤ የመምህር አካለወልድ አዳሪ ት/ቤት እና ስለ አቡነ አኖሬዎስ ገዳም የጓሮ አትክልትና ፍራፍሬ ልማትና የእደ ጥበብ ፕሮጀክት ዶክመንተሪ ፊልም ቀርቧል፡፡ በዶክመንተሪ ፊልሙም ገዳማትንና የገጠር አብያተ ክርስቲያናትን ለመርዳት በተናጠል የሚደርገው ሩጫ ለችግሮቹ ዘላቂ መፍትሄ የሚያስገኝ ባለመሆኑ በተጠና መልኩ የተቀናጀ እንቅስቃሴ ማድረጉ የተሻለ እንደሚሆን አስገንዝቧል፡፡

የቀረበውን ዶክመንተሪ ፊልም መነሻ በማድረግ በተደረገው ውይይት በውይይቱ ተጋባዥ የነበሩት ሊቀ ትጉሐን አባ መፍቀሬ ሰብዕ እንደገለጡት “ብንተባበር የቤተ ክርስቲያንን ችግር መፍታት እንችላለን፣ ለዚህም ደግሞ ለኅብረተሰቡ እንደዛሬው ያለ ጥልቅ ትምህርት በመስጠት ግንዛቤውን መለወጥ አስተዋጽኦ የጎላ እንደሆነ” ገልጸዋል፡፡ አክለውም “የቤተ ክርስቲያን ልጆች እኛ እያለን ቤተ ክርስቲያን አትዘጋም፣ ጉባኤው አይታጠፍም ልንል ይገባል” ብለዋል፡፡

በደቡብ ወሎ ሀገረ ስብከት ያሉ አብያተ ክርስቲያናት ወቅታዊ ሁኔታ የሚያሳይ የፎቶ ኤግዚቢሽን በመርሐ ግብሩ ለዕይታ ቀርቧል፡፡ በዕለቱ በመሪጌታ ይቻለዋል ጎሽሜ ‘ዕለት ዕለት የሚያሳስበኝ የአብያተ ክርስቲያናት ጉዳይ ነው’ በሚል ርዕስ ሰፋ ያለና ጥልቅ ትምህርት ተሰጥቷል፡፡ በትምህርቱም “ቤተ ክርስቲያን ጥላ ዘቅዝቃ የምትለምነው እኛ ልጆቿ ግዴታችንን ስለማንወጣ፤ አስራት በኩራት ስለማንከፍል እንደሆነና አባቶቻችን ድር ቢያብር … እንደሚሉት ከተናጠል ይልቅ በኅብረት ሆነን ቤተ ክርስቲያናችንን በዘላቂነት ማልማት እንዳለብን ተገልጿል፡፡

አቶ አለማየሁ የተባሉ የውይይቱ ተሳታፊ እንደገለጹት “በደሴ ከተማ ያሉ በጎ አድራጊዎችን በማስተባበርና ሁሉንም በመያዝ የተቀረጹ ፕሮጀክቶችን በመደገፍ ለቤተ ክርስቲያን ዘላቂ ልማት አስተዋጽኦ እንዲያበረክቱ ማድረግ ይገባል” በማለት ገልጸዋል፡፡በመርሐ ግብሩ ላይ ስለታቀዱት ፕሮጀክቶች መረጃ የሚሰጥ በራሪ ወረቀትና ተሳታፊዎች ፕሮጀክቶቹን ለመደገፍ የሚያበረክቱትን አስተዋጽኦ የሚሞሉበት ቅጽ ተዘጋጅቶ የተሰጠ ሲሆን በስራ ቦታና በመኖሪያ አካባቢያቸው ለሚያገኟቸው በጎ አድራጊዎች መልእክቱን እንደሚያስተላልፉና እነሱም የበኩላቸውን አስተዋጽኦ እንደሚያበረክቱ ገልጸዋል፡፡

በመጨረሻም በመርሐ ግብሩ የተገኙ፣ ተጠርተው ያልተገኙና ሌሎች በጎ አድራጊዎችንም በማካተት በተጠናከረ መልኩ በጋራ ለመንቀሳቀስና የቤተ ክርስቲያንን ልማት ለመደገፍ ይቻል ዘንድ ለየካቲት 23/2006 ዓ.ም ሌላ መርሐ ግብር ተይዞ የዕለቱ ውይይት ተፈጽሟል፡፡

 

abh 1

ለአብነት መምህራን የአቅም ማጎልበቻ ስልጠና ተሰጠ

የካቲት 12 ቀን 2006 ዓ.ም.

ህሊና ሲሳይ ከሐዋሳ

 

በማኅበረ ቅዱሳን ሐዋሳ ማዕከል የቅዱሳት መካናት ልማት እና ማኅበራዊ አገልግሎት ክፍል ለግቢ ጉባኤያት የአብነት መምህራን ከጥር 21-23 2006 ዓ.ም የአቅም ማጎልበቻ ሥልጠና ተሰጠ፡፡

abh 1በሐዋሳ ማዕከል መሰብሰቢያ አዳራሽ ሥልጠናው የተሰጣቸው የአብነት መምህራን ከሲዳማ፣ጌዲኦ፣አማሮና ቡርጂ ሀገረ ስብከት ከበንሳ፣ ዲላ፣ ይርጋጨፌ፣ ወንዶገነት፣ አርቤ ጎና፣ ሀገረ ሰላም፣ አማሮ፣ አለታ ወንዶ፣ እና ሐዋሳ ወረዳ ቤተ ክህነት የተመረጡ 13 የአብነት መምህራን ሲሆኑ የአቅም ማጎልበቻ ስልጠናው ትምህርተ ኖሎት፣የአብነት ትምህርትን የማስተማር ዘዴ፣የቤተ ክርስቲያን ታሪክ፣ ወቅታዊ የቤተ ክርስቲያን ጉዳይ እና የባለ ድርሻ አካላት ሚና በሚሉ ርእሰ ጉዳዮች በውይይት፣ በገለጻ፣ እና በልምድ ልውውጥ መልክ በአሠልጣኝነት የተጋበዙት የአብነት መምህራንና የዩኒቨርስቲ መምህራን ሥልጠናው ሰጥተዋል፡፡

በሥልጠናው ወቅት የአብነት መምህራኑ በሀገረ ስብከቱ በካህናት እጥረት የተነሳ የገጠረ አብያተ ክርስቲያናት እየተዘጉና አብዛኛዎቹ የተሟላ አገልግሎት እንደማይሰጥባቸው ገልጸው በሀገረ ስብከቱ አዳዲስ የአብነት ትምህርት ቤቶች እንዲከፈቱና ያሉትን ጥቂት ትምህርት ቤቶች ማጠናከር የተሻለ አማራጭ እንደሆነ አስረድተዋል፡፡

በተጨማሪም የአብነት ትምህርት መምህራኑ የመማር ማስተማር ሂደት ላይ በርካታ ችግሮች እንዳሉባቸው ገልጸዋል፡፡ የአብነት ትምህርት ቤቶችና ተማሪዎች ትምህርታቸውን እንዳይከታተሉ ዋና ዋና ፈተናዎች ናቸው ተብለው ከተነሱት መካከል፡-

  1.  የተማሪዎች ቤተሰብ ተጽእኖ፣

  2.  በገጠር አብያተ ክርስትያናት ብቁ እና በቂ መምህራን አለመኖር፣

  3. በተለያየ ምክንያት መምህራን ለማስተማር ያላቸው ተነሳሽነት ዝቅተኛ መሆን፣

  4. የአብነት መምህራን ከከተማ ወደ ገጠር እየተመላለሱ ማስተማር፣

  5. የተማሪዎች የግንዛቤ ችግር እና ፍላጎት ማነስ እንዲሁም ርዕይ አለመኖር፣

  6.  የሰበካ ጉባኤ ለአብነት ትምህርት ትኩረት አለመስጠት፣

  7. ለሚያስተምሩ መምህራን ከሀገረ ስብከቱ ምንም አይነት ማበረታታት አለመኖር፣

  8. ለአብነት መምህራን በቂ ክፍያና ትኩረት አለመኖር 

  9. የአብነት መምህራን ከገጠር ወደ ከተማ መፍለስ የሚሉና ሌሎችም ምክንያቶች ተጠቅሷል፣

 

abh 2የአብነት መምህራኑ አክለው እነዚህን ችግሮች ለመቅረፍ የአብነት ትምህርት ባለድርሻ አካላት ማለትም ሀገረ ስብከቱ፣ወረዳው ቤተ ክህነት፣ ሰበካ ጉባኤ፣ማኅበረ ቅዱሳን፣ የአብነት መምህራንና ተማሪዎች፣ የተማሪ ወላጆች እንዲሁም መላ ህዝበ ክርስቲያን ይህንን ችግር ለዘለቄታው ለመፍታት መረባረብ እንደሚገባ የተነሳ ሲሆን ይህ ሳይሆን ቢቀር ግብ ችግሩ የከፋ ደረጃ እንደሚደርስ የአብነት መምህራኑ አስረድተዋል፡፡

በመጨረሻም እንደዚህ አይነት የአቅም ማጎልበቻ ሥልጠና ተጠናክሮ ቀጥሎ ሌሎች የአብነት መምህራንም እንዲሳተፍ ማድረግ እንደሚገባና መቋረጥ እንደሌለበት የአብነት መምህራኑ አስተያየታቸውን ሰጥተዋል፡፡

 

ake 4

ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማቲያስ ፓትሪያሪክ ዘኢትዮጵያ በሐዋሳ ደማቅ አቀባባል ተደረገላቸው

 የካቲት 12 ቀን 2006 ዓ.ም.

ዲ/ን ያለው ታምራት ከሐዋሳ

ake 4
ጥር 29 ቀን 2006 ዓ.ም በእምነት ተቋማት ኀብረት በተዘጋጀው የሰላም ጉባኤ ላይ ለመሳተፍ ሐዋሳ ለተገኙት ለብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማቲያስ ፓትሪያሪክ ርዕሰ ሊቃለ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ እና ለሌሎች ሊቃነ ጳጳሳት በሐዋሳ ከተማ ምዕመናን ደማቅ አቀባበል ተደረገላቸው፡፡

ake 1ከፍተኛ ቁጥር ያለው የከተማው ነዋሪ በሞተር፣በመኪና እንዲሁም በእግር ከከተማ ውጪ በኦሮሚያ ክልል በቶጋ አከባቢ እስከ ሐዋሳ ደብረ ምሕረት ቅዱስ ገብርኤል ገዳም ድረስ በማጀብ ለቅዱስ ፓትርያርኩ ደማቅ አቀባበል አድረገዋል፡፡ የአባቶችን ቡራኬ ለመቀበል በደብረ ምህረት ቅዱስ ገብርኤል ገዳም ለረዥም ሰዓት ሲጠባበቁ የነበሩት ምዕመናን በዝማሬ፣በእልልታ ተቀብለዋል፡፡ ቅዱስ ፓትሪያሪኩና ብፁዓን አባቶች ልክ ወደ ሐዋሳ ከተማ ሲገቡ ያልተጠበቀ ዝናብ ጥላሏል፡፡ ይህ ሁኔታ በዝናብ እጦት ሲቸገሩ ለነበሩት ለከተማው ነዋሪዎች ልዩ ስሜትን ፈጥሯል፡፡የአባቶቹንም በረከት አድንቋል፡፡

የአቀባበል መርሐግብሩ በዓውደ ምሕረት ቀጥሎ በሲዳማ፣ጌዲኦ፣አማሮና ቡርጂ እንዲሁም የጉጂ ቦረናና ሊበን ሀገረ ስብከቶች ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ ገብርኤል ለቅዱስ ፓትሪያሪኩና ለብፁዓን አባቶች የእንኳን ደህና መጣችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል፡፡በመቀጠልም ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማቲያስ ምዕመናኑን ባርከው ወደ ሐዋሳ የመጡበትን ምክንያት ገልጸው በከተማዋ ለሦስት ቀናት እንደሚቆዩና እሁድ 2/06/2006 ዓ.ም ከምዕመናን ጋር ሰፊ መሐርግብር እንደሚኖራቸው ቃል ገብተዋል፡፡ በመጨረሻም የመዝጊያ ጸሎት ተደርጎ የዕለቱ የመርሐ ግብሩ ፍጻሜ ሆኗል፡፡

እሑድ የካቲት 2/2006 ዓ.ም የአቀባበል መርሐግብሩ ቀጥሏል፡፡ በዕለቱ ሥርዓተ ቅዳሴው የተከናወነው በብፁዓትን ሊቃነ ጳጳሳት ሲሆን ሥርዓተ ቅዳሴውም ከተፈጸመ በኋላ የዓውደ ምሕረት መርሐ ግብሩ በደማቅ ሁኔታ ተጀምሯል፡፡ ብፁዕ አቡነ ኤልሳ የሰሜን ጎንደረ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ የዕለቱን ትምህርተ ወንጌል አስተምረዋል፡፡ በመቀጠልም የቅዱስ ፓትሪያሪኩ የአንደኛ ዓመት በዓለ ሲመት አስመልክቶ በቅዱስ ገብርኤል ገዳም ካህናት ቅኔ መወድስ የቀረበ ሲሆን የገዳሙ አስተዳደርም ለብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማቲያስ ያዘጋጀውን ልዩ ልዩ ስጦታዎችን አበርክቷል፡፡

ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማቲያስ ፓትሪያሪክ ርዕሰ ሊቃለ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ በሐዋሳ ከተማ ከብፁዓን ሊቃ ጳጳሳት ጋር በመገኘታቸው መደሰታቸውንና የተለያዩ የእምነት ተቋማት ባዘጋጁት የሰላም ጉባኤ ላይ ለመሳተፍ በሐዋሳ በነበራቸው የሦስት ቀን ቀይታake 3 ስለ ሰላም አስፈላጊነት በሰፊው ውይይት መደረጉን ገልጸዋል፡፡”ከሁሉ በፊት ሰላም፣ፍቅርና አንድነት ያስፈልጋል፡፡ ሰላም ከሌለ ምንም ነገረ የለም ሰላም ካለ ግን ሁሉ ነገረ አለ፡፡ስለዚህ ሁላችንም ስለ ሰላም ማስተማር መጸለይ አለብን” ብለዋል፡፡
በመጨረሻም ቅዱሳ አባታችን ሕዝቡን ባርከው ከፊት ያሉትን ሱባኤና ጾም ፀሎት ሁላችንም በርትተን መፈጸም አለብን ብለው ስለተደረገላቸው መልካም አቀባበልና ስጦታ በእርሳቸውና በብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳት ስም አመስግነዋል፡፡

 

በግዮን ሆቴል ሊካሔድ የነበረው የአብነት መምህራን የምክክር ጉባኤ እንዳይካሔድ ተከለከለ

የካቲት 7 ቀን 2006 ዓ.ም.

መ/ር ሳሙኤል ተስፋዬ

በማኅበረ ቅዱሳን አስተባባሪነት በየሦስት ዓመቱ የሚካሔደው የአብነት መምህራን የምክክር ጉባኤ ከቅዱስ ፓትርያርኩ በተሰጠ መመሪያ መሠረት እንዳይካሔድ ተደርጓል፡፡

የጉባኤውን መከልከል አስመልክቶ መግለጫ የሰጡት የማኅበሩ ዋና ጸሐፊ አቶ ተስፋዬ ቢሆነኝ እና የማኅበሩ ቅዱሳት መካናት ልማትና ማኅበራዊ አገልግሎት ምክትል ዳይሬክተር ወ/ሮ ዓለምፀሐይ መሠረት በጋራ እንደገለጹት “ማኅበሩ በየሦስት ዓመቱ ይህንን ጉባኤ ያካሒዳል፤ ይህ ለሦስተኛ ጊዜ ነው፡፡ ዓላማውም የአብነት መምህራንን የቀለብ፣ የአልባሳት፣ የፍልሰት ችግሮችን ለመቅረፍ እንዲሁም መምህራኑ በቂ ደመወዝ ስለማይከፈላቸው ድጋፍ ለማድረግና የአቅም ማጐልበቻ ውይይትና ሥልጠና ለማድረግ  የታቀደ ነበር፡፡

ሆኖም ግን ደብዳቤው ደርሶን የጉባኤውን መታገድ ምክንያት ለጊዜው ባንረዳም በቅዱስነታቸው መመሪያ መሠረት ጉባኤው መካሔድ እንደሌለበት ብፁዕ ሥራ አስኪያጁ ደብዳቤ እንደደረሳቸውና መቋረጥ እንዳለበት በቃል ነግረውናል” በማለት ገልጸው የዘንድሮው ጉባኤ ካለፉት ጉባኤያት የሚለየው በምንድን ነው? ተብለው ለተጠየቁት ጥያቄ ሲመልሱ:-

 

“የዘንድሮው ጉባኤ ባለፉት ጉባኤያት ከተነሡት አጀንዳዎች ልዩነት የለውም፡፡ ቀጣይና የሞኒተሪንግ አካል ነው፡፡ ትልልቅ ግንባታዎች የአብነት ት/ቤቶች ይሠራሉ፡፡ በእነዚህ ሥራዎች ላይ ጥያቄ አልቀረበም፡፡ በግዮን ሆቴልም ሆነ በሌሎቹ ማእከላዊ ቦታዎች ምክክር ስናደርግ ቆይተናል፡፡ ስለዚህ አሁን የተከለከለውን ጉባኤ እንደገና ለማካሔድ ከቅዱስ ፓትርያርኩ ጋርና ከብፁዓን አባቶች ጋር የጀመርነውን ውይይት እንቀጥላለን፡፡ ተመካክረን የምንሠራበትን ሁኔታ እናመቻቻለን፤ ለዚህም ተስፋ አለን” በማለት ገለጻቸውን አጠቃለዋል፡፡