ake 4

ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማቲያስ ፓትሪያሪክ ዘኢትዮጵያ በሐዋሳ ደማቅ አቀባባል ተደረገላቸው

 የካቲት 12 ቀን 2006 ዓ.ም.

ዲ/ን ያለው ታምራት ከሐዋሳ

ake 4
ጥር 29 ቀን 2006 ዓ.ም በእምነት ተቋማት ኀብረት በተዘጋጀው የሰላም ጉባኤ ላይ ለመሳተፍ ሐዋሳ ለተገኙት ለብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማቲያስ ፓትሪያሪክ ርዕሰ ሊቃለ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ እና ለሌሎች ሊቃነ ጳጳሳት በሐዋሳ ከተማ ምዕመናን ደማቅ አቀባበል ተደረገላቸው፡፡

ake 1ከፍተኛ ቁጥር ያለው የከተማው ነዋሪ በሞተር፣በመኪና እንዲሁም በእግር ከከተማ ውጪ በኦሮሚያ ክልል በቶጋ አከባቢ እስከ ሐዋሳ ደብረ ምሕረት ቅዱስ ገብርኤል ገዳም ድረስ በማጀብ ለቅዱስ ፓትርያርኩ ደማቅ አቀባበል አድረገዋል፡፡ የአባቶችን ቡራኬ ለመቀበል በደብረ ምህረት ቅዱስ ገብርኤል ገዳም ለረዥም ሰዓት ሲጠባበቁ የነበሩት ምዕመናን በዝማሬ፣በእልልታ ተቀብለዋል፡፡ ቅዱስ ፓትሪያሪኩና ብፁዓን አባቶች ልክ ወደ ሐዋሳ ከተማ ሲገቡ ያልተጠበቀ ዝናብ ጥላሏል፡፡ ይህ ሁኔታ በዝናብ እጦት ሲቸገሩ ለነበሩት ለከተማው ነዋሪዎች ልዩ ስሜትን ፈጥሯል፡፡የአባቶቹንም በረከት አድንቋል፡፡

የአቀባበል መርሐግብሩ በዓውደ ምሕረት ቀጥሎ በሲዳማ፣ጌዲኦ፣አማሮና ቡርጂ እንዲሁም የጉጂ ቦረናና ሊበን ሀገረ ስብከቶች ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ ገብርኤል ለቅዱስ ፓትሪያሪኩና ለብፁዓን አባቶች የእንኳን ደህና መጣችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል፡፡በመቀጠልም ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማቲያስ ምዕመናኑን ባርከው ወደ ሐዋሳ የመጡበትን ምክንያት ገልጸው በከተማዋ ለሦስት ቀናት እንደሚቆዩና እሁድ 2/06/2006 ዓ.ም ከምዕመናን ጋር ሰፊ መሐርግብር እንደሚኖራቸው ቃል ገብተዋል፡፡ በመጨረሻም የመዝጊያ ጸሎት ተደርጎ የዕለቱ የመርሐ ግብሩ ፍጻሜ ሆኗል፡፡

እሑድ የካቲት 2/2006 ዓ.ም የአቀባበል መርሐግብሩ ቀጥሏል፡፡ በዕለቱ ሥርዓተ ቅዳሴው የተከናወነው በብፁዓትን ሊቃነ ጳጳሳት ሲሆን ሥርዓተ ቅዳሴውም ከተፈጸመ በኋላ የዓውደ ምሕረት መርሐ ግብሩ በደማቅ ሁኔታ ተጀምሯል፡፡ ብፁዕ አቡነ ኤልሳ የሰሜን ጎንደረ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ የዕለቱን ትምህርተ ወንጌል አስተምረዋል፡፡ በመቀጠልም የቅዱስ ፓትሪያሪኩ የአንደኛ ዓመት በዓለ ሲመት አስመልክቶ በቅዱስ ገብርኤል ገዳም ካህናት ቅኔ መወድስ የቀረበ ሲሆን የገዳሙ አስተዳደርም ለብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማቲያስ ያዘጋጀውን ልዩ ልዩ ስጦታዎችን አበርክቷል፡፡

ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማቲያስ ፓትሪያሪክ ርዕሰ ሊቃለ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ በሐዋሳ ከተማ ከብፁዓን ሊቃ ጳጳሳት ጋር በመገኘታቸው መደሰታቸውንና የተለያዩ የእምነት ተቋማት ባዘጋጁት የሰላም ጉባኤ ላይ ለመሳተፍ በሐዋሳ በነበራቸው የሦስት ቀን ቀይታake 3 ስለ ሰላም አስፈላጊነት በሰፊው ውይይት መደረጉን ገልጸዋል፡፡”ከሁሉ በፊት ሰላም፣ፍቅርና አንድነት ያስፈልጋል፡፡ ሰላም ከሌለ ምንም ነገረ የለም ሰላም ካለ ግን ሁሉ ነገረ አለ፡፡ስለዚህ ሁላችንም ስለ ሰላም ማስተማር መጸለይ አለብን” ብለዋል፡፡
በመጨረሻም ቅዱሳ አባታችን ሕዝቡን ባርከው ከፊት ያሉትን ሱባኤና ጾም ፀሎት ሁላችንም በርትተን መፈጸም አለብን ብለው ስለተደረገላቸው መልካም አቀባበልና ስጦታ በእርሳቸውና በብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳት ስም አመስግነዋል፡፡