• እንኳን በደኅና መጡ !

ዜናዎች፣ ወቅታዊ ክንውኖች እና ልዩ ልዩ ይዘቶች

የወልደ ነጎድጓድ ልጆች እንቅስቃሴ

በፈትለወርቅ ደስታ
 ሰኔ 28ቀን 2003ዓ.ም
ጊዜው ትውልዱ በሶሻሊዝም ፍልስፍና እየተሳበ የነበረበት ነበር፡፡ 1960ዓ.ም ማለትም የዛሬ 43 ዓመት ሆነ፡፡ የቤተ ክርስቲያኗ አስተዳደር የነበሩት መምህር መዘምርና መምህር ዘውዴ የቅዱስ ዮሐንስ ወልደ ነጎድጓድ ሰንበት ትምህርት ቤትን እንደመሠረቱት የሚነገረው በዚህ ጊዜ ነው፡፡ ሕፃናትንና ወጣቶችን በመሰብሰብ ምሥረታው አሐዱ የተባለው ሰንበት ትምህርት ቤት አሁን በሕይወት የሌሉት ብፁዕ አቡነ ያዕቆብ የቅርብ ክትትል ይደረግለት ነበር፡፡ ብፁዕነታቸው የደብሩ አስተዳዳሪ በነበሩበት ወቅት አባላትን እንደልጅ እየኮተኮቱና እየተንከባከቡ ያሳድጓቸው ነበር፡፡ ቅዳሜና እሑድ የሚሰጠውን የትምህርት መርሐ ግብር የሚመጡትንም /የሚመደቡትን/ መምህራንና የሚያስተምሩትን ትምህርት በመቆጣጠርና በማረም ሰንበት ትምህርት ቤቱን ጥሩ ደረጃ ላይ አድርሰውታል፡፡

ትምህርተ ጦም በሊቃውንት

ሰኔ 24/2003 ዓ.ም.

 በዲ/ን ሽመልስ መርጊያ
 
በዚህ ጽሑፍ ጦምን አስመልክቶ የቅዱሳን አባቶችን አስተምህሮ እንመለከታለን
 
አንድ የገዳም አበምኔት  አንድ ወቅት አባ ጳይመን የሚባሉትን አባት “እግዚአብሔርን መፍራት እንዴት ገንዘቤ ማድረግ ይቻለኛል” ብለው  ይጠይቋቸዋል፡፡ እሳቸውም ሲመልሱ “እንዴት ሰው በላመና በጣፈጠ መብልና መጠጥ ሆዱን እየሞላ እግዚአብሔርን መፍራት ገንዘቡ ሊያደርግ ይችላል? ስለዚህም ጦም እግዚአብሔርን ወደመፍራት ይመራል፡፡ የጦም የመጨረሻ ግቡ እግዚአብሔርን ወደመፍራት ማምጣት  ነው”  ብለው ይመልሱላቸዋል፡፡
 

“የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ሚና በአየር ንብረት ለውጥ” በሚል መሪ ቃል ጥናታዊ የውይይት መድረክ ተካሄደ

ዲ/ን ቴዎድሮስ ኃይሉ
 
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን በሰንበት ትምህርት ቤቶች ማደራጃ መምሪያ ማኅበረ ቅዱሳን ጥናትና ምርምር ማዕከል “የኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን ሚና በአየር ንብረት ለውጥ“ በሚል መሪ ቃል ሰኔ 18 ቀን 2003 ዓ.ም በኢትዮጵያ ብሔራዊ ሙዝየም መሰብሰቢያ አዳራሽ ጥናታዊ የውይይት መድረክ ተካሄደ፡፡
 
ቀሲስ ለማ በሱፍቃድ

ማኅበረ ቅዱሳን 20ኛውን ሐዋርያዊ ጉዞ በሰሜን ምሥራቅ ኢትዮጵያ በተሳካ ሁኔታ አደረገ

በዲ/ን ቴዎድሮስ ኃይሉ

ሰኔ 20 ቀን 2003ዓ.ም

ማኅበረ ቅዱሳን በትምህርትና ሐዋርያዊ አገልግሎት ዋና ክፍል ከግንቦት 19 – ሰኔ 1 ቀን 2003 ዓ.ም ድረስ በሰሜን ወሎ እና ደቡብ ትግራይ አህጉረ ስብከቶች ሃያ ሰባት ልዑካንን በመያዝ ሐዋርያዊ ጉዞ ማድረጉን በትምህርትና ሐዋርያዊ አገልግሎት ዋና ክፍል መደበኛ መምህርና የሐዋርያዊው ጉዞ አስተባባሪ ቀሲስ ለማ በሱ ፍቃድ አስታወቁ፡፡

በክለሳ ላይ ያለው የግቢ ጉባኤያት ሥርዓተ ትምህርት ትግበራው በ2004 ዓ.ም ይጀመራል ተባለ፡፡

 ዲ/ን ቴዎድሮስ ኃይሉ
 
ከ2000 ዓ.ም ጀምሮ እየተከናወነ ያለውን የግቢ ጉባኤያት የሥርዓተ ትምህርት ክለሳ በተመለከተ ከማዕከላትና ግቢ ጉባኤያት ተወካዮች ጋር ውይይት ተደረገ፡፡ ሥርዓተ ትምህርቱም ከ2004 ዓ.ም ጀምሮ ተግባራዊ እንደሚደረግ በማኅበረ ቅዱሳን የትምህርትና ሐዋረያዊ አገልግሎት ዋና ክፍል አስታወቀ፡፡

የእግዚአብሔር ኃይል(ለሕፃናት)

ሰኔ15 ፣2003 ዓ.ም

ከእመቤት ፈለገ
 
በእስራኤል ሀገር ውስጥ አክዓብ የሚባል ንጉሥ ነበር፡፡ ንጉሡም በዓል የሚባል ጣዖት አምልኮ እግዚአብሔርን አሳዘነው፡፡ በዚሁ ሀገር ውስጥ የሚገኝ የእግዚአብሔርን ትዕዛዝ የሚፈጽም ኤልያስ የሚባል ነቢይ ነበር፡፡ ንጉሡና ሕዝቦቹ እግዚአብሔርን እንዳስቀየሙት ባየ ጊዜ ዝናብ እንዳይዘንብ ጸለየ፡፡ ከብዙ ቀንም በኋላ በምድር ላይ ዝናብ አልነበረም፡፡ ከብዙ ቀንም በኋላ በሦስተኛው ዓመት “አክዓብ ጋር ሂድ በምድር ላይም ዝናብ እሰጣለሁ” ብሎ እግዚአብሔር ለኤልያስ ነገረው፡፡ በአገሪቱም ውስጥ ከፍተኛ ረሃብ ሆኖ ነበር፡፡
የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊ ብፁዕ አቡነ ሕዝቅኤል

ምዕዳነ አበው

በዲ/ን ኅሩይ ባየ እና በደረጀ ትዕዛዙ
 ሰኔ 17 ቀን 2003 ዓ.ም
/ምንጭ፦ ስምዐ ጽድቅ ጋዜጣ ከግንቦት1-15፣ 2003 ዓ.ም/ 
 
የቅዱስ ሲኖዶስ የርክበ ካህናት ጉባኤ ከግንቦት 10-16 ቀን 2003 ዓ.ም ሲካሔድ ቆይቶ ውሳኔዎችን በማሳለፍ ተጠናቋል፡፡ ስለ ጉባኤው ሒደት አስተያየታቸውን እንዲሰጡን፤ ተሳታፊ ከነበሩት የቅዱስ ሲኖዶስ አባላት በተለያዩ ጉዳዮች ላይ ይመለከታቸዋል ብለን ያሰብናቸውን ብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳት አነጋግረን የዚህ ዕትም የአብርሃም ቤት እንግዳ አድርገናቸዋል፡፡
«ያሳለፍናቸው ውሳኔዎች በሥራ ላይ መዋል አለባቸው፡፡»

  የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊ ብፁዕ አቡነ ሕዝቅኤል

ስምዐ ጽድቅ፡- የግንቦቱ ቅዱስ ሲኖዶስ ጉባኤ የርክበ ካህናት ጉባኤ ስለተወያየባቸው አጀንዳዎች ቢገልጹልን? 

ብፁዕ አቡነ ሕዝቅኤል፡- ተወያይተን ውሳኔ ያሳለፍንባቸው አጀንዳዎች ወደ ዐሥራ ሦስት ይሆናሉ፡፡ የብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርኩ የጉባኤ መክፈቻ ንግግር፣ የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊ ዓመታዊ የሥራ ክንውን፣ በቅርቡ ለጠቅላይ ቤተ ክህነት ሠራተኞች ስለተደረገው የደመወዝ ጭማሪ፣ የኢትዮጵያ ታላቁ የሕዳሴ ግድብ ግንባታ፣ የሲዳማ ሀገረ ስብከት ችግር፣ መንፈሳዊ ተቋማትን በተመለከተ፣ የልማት እና ክርስቲያናዊ ተራድኦ ኮሚሽን ኤች አይ ቪ/ ኤድስ መከላከያና መቆጣጠሪያ መምሪያ ሥራ አፈጻጸም፣ ልማትን በተመለከተ፣ የስብከተ ወንጌል ጉዳይ፣ የሊቃነ ጳጳሳት ዝውውር፣ በሰንበት ት/ቤቶች ማደራጃ መምሪያ ሓላፊ እና በማኅበረ ቅዱሳን የተፈጠረውን አለመግባባት በተመለከተ፣ የቀጣዩ ቋሚ ሲኖዶስ አባላት ምርጫና ልዩ ልዩ የሚሉ ናቸው፡፡
 
hawire_Hiwot2.jpg

ከ 3000 በላይ ምዕመናን ይሳተፉበታል ተብሎ የሚጠበቅ መንፈሳዊ ጉዞ ተዘጋጀ

በተ/ሥላሴ ፀጋ ኪሮስ

ሰኔ 15 ቀን 2003 ዓ.ም

ከ6 ወራት በፊት ተዘጋጅቶ እንደነበረው በርካታ ምእመናን የሚሳተፉበት መንፈሳዊ ጉዞ ተዘጋጀ፡፡ ሐዊረ ሕይወት ቁጥር 2 የሚል ስያሜ ያለው ይህ ጉዞ ሰኔ 19 ቀን 2003 ዓ.ም ይከናወናል፡፡

አጭሩ ዘኪዮስ(ለሕፃናት)

ሰኔ11 ፣2003 ዓ.ም

አዜብ ገብሩ

ዘኪዮስ የሚባል አጭር ሀብታም ሰው ነበረ፡፡ ኢየሱሱ ክርስቶስን ለማየት በጣም ይፈልግ ነበር፡፡ ምክንያቱም ስለ እርሱ ብዙ ነገር ሲነገር ይሰማ ስለነበረ ነው፡፡ ጌታችን በዛሬው ዕለት ኢያሪኮ ወደምትባለው ከተማ ይገባል ብለው ሰዎች ሲያወሩ ዘኪዮስ ሰማ፡፡

የግቢ ጉባኤያትን ተማሪዎች መንፈሳዊ ሕይወት ለማሳደግ የሚያስችል የንሰሐ አባቶች ሴሚናር ተካሔደ

በእንዳለ ደጀኔ

ሰኔ 10 ቀን 2003 ዓ.ም 

በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን በሰንበት ት/ቤቶች ማ/መምሪያ ማኅበረ ቅዱሳን የግቢ ጉባኤያት ተማሪዎችን መንፈሳዊ ህይወት ለማሳደግ የሚያስችል የግቢ ጉባኤያት ተማሪዎች የንስሐ አባቶች ሴሚናር ተካሔደ፡፡

በፌስቡክ የትስስር ገጽ ያግኙን

ስለ ማኅበረ ቅዱሳን መሰረታዊ መረጃዎች

ስያሜ

ማኅበረ ቅዱሳን እግዚአብሔር ያከበራቸው የነቢያት፣ የሐዋርያት፣ የጻድቃንና የሰማዕታት በአጠቃላይ የቅዱሳን ገድል፣ ትሩፋትና አማላጅነት የሚዘከርበት በመሆኑ ‹‹ማኅበረ ቅዱሳን›› የሚል ስያሜውን አግኝቷል፡፡

የማኅበሩ ርእይ

ቤተ ክርስቲያን ሁለንተናዊ የመሪነት ሚናዋን ስትወጣ ማየት

ተልእኮ

ለቤተ ክርስቲያን ተልእኮ መሳካት እና ለሕልውናዋ የሚተጋ፣ የተደራጀ ፣ ምሉዕ ኦርቶዶክሳዊ፤ ርቱዕ ዘመናዊ፤ ሁለገብ መሪ ትውልድ ማፍራት እና ማሰማራት

እሴቶች

  • መንፈሳዊነት

    ኦርቶዶክሳዊነት ርትዕት ሃይማኖት፣ ጽኑ እምነት፣ መልካም ምግባርና መንፈሳዊ እውቀት በአንድነት የተዋሐዱበት፤ አርአያ እግዚአብሔርን አጽንቶ በሐዋርያዊ የሕይወት ተጋድሎ እግዚአብሔርን በግብር ወደ መምሰል የሚታደግበት ፍጹም ሰማያዊ ሕይወት በመሆኑ፤ አባላት በየትኛውም ቦታ፣ ጊዜና ሁኔታ በማሰብ፣ በመናገር እና በመሥራት/በተግባር በሚገለጽ ክርስቲያናዊ ሥነ ምግባር ታንጸው፣ ፍኖተ አበውን ተከትለው፣ በታማኝነት እና በፈሪሐ እግዚአብሔር ቤተ ክርስቲያንን በቅንነት ያገለግላሉ::
  • አገልጋይነት

    የማኅበሩ አባላት አገልግሎትን የክርስቲያናዊ ሕይወታቸው መገለጫ አድርገው በመቀበል በበጎ ፈቃድ ሰማያዊውን ክብርና ጸጋ በመሻት፣ ምድራዊ ክብርና ውዳሴ ከንቱን ሳይፈልጉ፣ በትሕትና እና በክርስቲያናዊ ፍቅር በታማኝነት ያገለግላሉ::
  • የሐሳብ መሪነት

    ማኅበሩ ለቤተ ክርስቲያን ዘላቂ አገልግሎት የሚያስፈልጉ፣ ኦርቶዶክሳዊ እሳቤን የተከተሉና ዘመኑን የዋጁ የመሪነት ሐሳቦችን በማፍለቅ ከሚመለከታቸው የቤተ ክርስቲያን መሪዎች ጋር በመመካከር ይሠራል::
  • ተባባሪነት

    ማኅበሩ የቤተ ክርስቲያን አገልግሎት የሁሉም የቤተ ክርስትያን አካላት የወል ተግባር ነው ብሎ ያምናል:: በመሆኑም እንደየጉዳዩ አግባብነት ካላቸው ባለ ድርሻ እና አጋር አካላት ጋር በመግባባት፣ በመመካከር እና በቅንነት ለተልእኮ አንድነት ብዝኃ ጸጋን በማክበር አብሮ ይሠራል::
  • ሙያ አክባሪነት

    የማኅበሩ አባላት ባላቸው ልዩ ልዩ ሙያ /ዕውቀት/ ቤተ ክርስቲያንን ለማገልገል የተሰባሰቡ በመሆናቸው፣ በማኅበሩ አሠራሮች ሁሉ ከኦርቶዶክሳዊው ትምህርተ ሃይማኖት ጋር በማይጋጩ በእውነተኛ መረጃ ለሚደገፉ ሙያዊ ምክረ ሐሳቦች ተገቢውን ክብርና ቅድሚያ ይሰጣል:: በቤተ ክርስቲያንም ለመንፈሳዊ እና ለዘመናዊው (አስኳላ) ሙያ ተገቢው ክብር እንዲሰጥ ይሠራል::
  • ምክንያታዊ ሞጋችነት

    ማኅበሩ በእውነተኛ መረጃ ላይ ተመሥርቶ ቤተ ክርስቲያንን ከውስጥም ሆነ ከውጭ የሚፈትኑ አስተሳሰቦችን፣ አሠራሮችን፣ ልማዶችን እና ትርክቶችን በግልጽና በመንፈሳዊ ጥብዓት እና በእውነት እንዲሞገቱና መፍትሔ ላይ እንዲደረስ ይሠራል::
  • ተጠያቂነት

    የማኅበሩ አገልግሎት ግብ ሰማያዊ ዋጋ ማግኘት ስለሆነ ኀላፊነትን በአግባቡ አለመወጣት በእግዚአብሔር እና በሰዎች ዘንድ የሚያስጠይቅ በመሆኑ በየትኛውም እርከን ላይ ያለ አባል እና አመራር በማኅበሩ አሠራር መሠረት በተሰጠው ኀላፊነት ተጠያቂ ይሆናል፡፡

ዓላማዎች

  • የቤተ ክርስቲያን ተቋማዊ አስተዳደር፣ የአሠራር ሥርዐትና አስተሳሰብ፣ በቴክኖሎጂ እና በልዩ ልዩ መንገዶች በመደገፍ ዘመኑን ለዋጀ ጠንካራ አገልግሎት ማብቃት፤
  • የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ተማሪዎችን ሙሉ ሰብእናን የሚገነባ ሥርዐተ ትምህርት በማስተማር ዘመኑን የዋጁ ምሉዕ ኦርቶዶክሳዊ የሆኑ በቤተ ክርስቲያን አስተዳደራዊ መዋቅር የሚያገለግሉ እንዲሁም በማኅበራዊ፣ በኢኮኖሚያዊ በፖለቲካዊ እና በሀገር አስተዳደር ጉዳዮች መሪ/ንቁ ተሳታፊ አገልጋዮችን ማፍራት እና ማሠማራት፤
  • የተተኪውን ትውልድ ምንጭ ለማጎልበት የሰ/ት/ቤቶችን አቅም በማጠናከር የሕጻናት እና የወጣቶችን የተተኪነት ሚና ማሳደግ፤
  • ኦርቶዶክሳዊ መንፈሳዊነትን በተግባር የሚገልጽ ቤተሰብ እና አንድነቱን የጠበቀ ኦርቶዶክሳዊ ማኅበረሰብ በመገንባት የተደራጀ እና የተናበበ አገልግሎት መስጠት፤
  • በተደራጀ እና ተደራሹን ማእከል ባደረገ መንገድ ስብከተ ወንጌልንና ሐዋርያዊ ተልእኮን ዘርፈ ብዙ በሆኑ መንገዶች በመላው ዓለም ማስፋፋት፤
  • በቤተ ክርስቲያን ላይ የሚነዙትን የርእዮተ ዓለም፣ የሐሰት ትርክቶች እና የአጽራረ ቤተ ክርስቲያንን እንቅስቃሴ ጥናት እና ምርምር ላይ ተመርኩዞ መሞገት እና የተሳሳቱትን በማረም፣ በጠንካራ የዕቅበተ እምነት አገልግሎት የቤተ ክርስቲያንን ሕልውና ማስጠበቅ፤
  • በተመረጡ ገዳማት እና አብነት ትምህርት ቤቶች የልኅቀት ማእከል እና የተለየ ክርስቲያናዊ ተልእኮ የሚፈጽሙ እንዲሆኑ የሚያስችል ሁለገብ የአእምሮ ልማት ድጋፍ ማድረግ፤
  • ማኅበሩ ዘመኑን የዋጀ ተቋማዊ የአሠራር ሥርዓት በመዘርጋት ተልእኮውን ማሳካት የሚችልበት አቅም መፍጥር ( በአመራር፣ በሰው ኃይል፣ በመንፈሳዊነት፣ በግንኙነት፣ በዕውቀት፣በልማት፣ በፋይናንስ፣ በቴክኖሎጂ)፤
  • ዓለም አቀፍ ግንኙነትና የትብብር አገልግሎትን መርሕ ያደረገ የኦርቶዶክሳውያን ኢኮኖሚያዊ፣ ማኅበራዊና ፖለቲካዊ ተሳትፎ ማሳደግ፣

አቡነ ጎርጎርዮስ ካልዕ
የሸዋ ሊቀ ጳጳስ ፲፱፻፴፪-፲፱፻፹፪ዓ.ም.

የማኅበሩ ህንጻ