መንፈሳዊነት
ኦርቶዶክሳዊነት ርትዕት ሃይማኖት፣ ጽኑ እምነት፣ መልካም ምግባርና መንፈሳዊ እውቀት በአንድነት የተዋሐዱበት፤ አርአያ እግዚአብሔርን አጽንቶ በሐዋርያዊ የሕይወት ተጋድሎ እግዚአብሔርን በግብር ወደ መምሰል የሚታደግበት ፍጹም ሰማያዊ ሕይወት በመሆኑ፤ አባላት በየትኛውም ቦታ፣ ጊዜና ሁኔታ በማሰብ፣ በመናገር እና በመሥራት/በተግባር በሚገለጽ ክርስቲያናዊ ሥነ ምግባር ታንጸው፣ ፍኖተ አበውን ተከትለው፣ በታማኝነት እና በፈሪሐ እግዚአብሔር ቤተ ክርስቲያንን በቅንነት ያገለግላሉ::




ጾመ ፍልሰታ ለቤተ ክርስቲያን ሰላም
ኢትዮጵያ የእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም የአሥራት አገር ናት፡፡ ሊቃውንትም ነቢያት የተነበዩትን ትንቢት የቆጠሩትን ሱባዔ መሠረት በማድረግ ቅድስት ድንግል ማርያም በኪደተ እግሯ ኢትዮጵያን መባረኳን ያስተምራሉ፡፡ «ነቢዩ ዕንባቆም የኢትዮጵያ ድኳኖች ሲጨነቁ ዐየሁ፤» ዕንባ. 3፡7 ብሎ የተናገረው ቃለ ትንቢት እመቤታችን የኢትዮጵያን አውራጃዎች ለመባረኳ ማስረጃ መሆኑን ሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያን ይተረጉማሉ፤ ያመሠጥራሉ፡፡
ዘጠነኛው የአውሮ ማዕከል ጉባኤ ተጠናቀቀ
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ሰንበት ትምህርት ቤቶች ማደራጃ መምሪያ ማኅበረ ቅዱሳን የአውሮ ማዕከል ዘጠነኛ ጠቅላላ ጉባኤ ከሐምሌ 3 ቀን እስከ 5 ቀን 2001 ዓ.ም በኦስትሪያ ሽቬካት ከተማ ተካሔደ፡፡
ለቅኔ ትምህርት ትኩረት መስጠት እንደሚገባ ተገለጸ
ዓውደ ርእዩ ኅብረተሰቡ ስለአብነት ትምህርት ቤቶች ግንዛቤ እንዲኖረው ረድቷል
«ቅኔ የአብነት ትምህርቱ ፍልስፍና መሠርተ» በሚል ርዕስ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ሰንበት ትምህርት ቤቶች ማደራጃ መምሪያ ማኅበረ ቅዱሳን በማኅበራዊ አገልገሎት ልማት ዋና ክፍል የተዘጋጀው የግማሸ ቀን ዐውደ ጥናት በስ ድስት ኪሎ ስብሰባ አዳራሽ ተካሄደ፡፡
ለጥምቀት ወጥታ የቆየችው ታቦት ወደ አዲሱ ሕንጻ ቤተክርስቲያን ገባች
የቃሊቲ ቁስቋም ማርያም ታቦተ ሕግ ባለፈው ጥምቀት ወጥታ ተመልሳ መግባት ፈቃዷ ባለመሆኑ የተፈጠረውን የምእመ ናንና የካህናት ጭንቅ፣ ሐዘን፣ ድንጋጤ በብዙ የሚክስ የደስታ ዕለት፡፡ ሐምሌ 25 ቀን 2001 ዓ.ም፡፡
ከብርሃን ይልቅ ጨለማን ስለወደዱ …/ዮሐ.3-19/
ብርሃን ወደ ዓለም ስለመጣ፣ ሰዎችም ሥራቸው ክፉ ነበርና ከብርሃን ይልቅ ጨለማን ስለወደዱ ፍርዱ ይህ ነው፡፡ ክፉ የሚያደርግ ሁሉ ብርሃንን ይጠላልና፡፡ ሥራውም እንዳይገለጥ ወደ ብርሃን አይመጣም፤ እውነትን የሚያደርግ ግን ሥራው በእግዚአብሔር ተደርጐ እንደሆነ ይገለጥ ዘንድ ወደ ብርሃን ይመጣል፡፡ /ዮሐ.3-19/
የቅዱስ ሲኖዶስ ሰማያዊና ሉዓላዊ ሥልጣን ይከበር!
የቅዱስ ሲኖዶስ አስቸኳይ ስብሰባ ተጠናቀቀ
በግንቦቱ የቅዱስ ሲኖዶስ ስብሰባ የቤተክርስቲያኒቱን አስተዳደራዊና የልማት ሥራዎች እንዲያከናውን የተመረጠውንና በአዲስ አበባ ሀገረ ስብ ከት የተነሳውን ችግር ለመፍታት የተጠራው አስቸኳይ የቅዱስ ሲኖዶስ ስብሰባ ተጠናቀቀ፡፡
ማኅበረ ቅዱሳን «ደጀ ሰላም»ብሎግ ልሣኑ አለመሆኑን አስታወቀ
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን በሰንበት ትምህርት ቤቶች ማደራጃ መምሪያ ማኅበረ ቅዱሳን ፣ «ደጀ ሰላም» በሚሰኝ ብሎግ ላይ የሚለቀቀው መግለጫ እንደማይመለከተው አስታወቀ፡፡
intro
intro page
ጾመ ፍልሰታን እንዴት እናክብር?
በሕይወተ ሥጋ ሳለን ካልጾምንና ካልጸለይን ነፍሳችን ልትለመልም አትችልም፡፡ በጾም በጸሎት ዲያብሎስን፣ ዓለምንና ፍትወታት እኩያትን ድል መንሣት ይቻላል፡፡ እንደዚሁም በጾም አማካኝነት መንፈሳዊ ሕይወትን ማሳደግ ይቻላል፡፡
ውድ አንባቢያን ለመግቢያ ያህል ስለጾም ይህን ያህል አልን እንጂ ጾም በራሱ ምንድን ነው? ለምንስ ይጾማል? ምንስ ጥቅም ያስገኛል? ባንጾምስ ምን ጉዳት አለው? የሚሉትን በአጭር በአጭሩ ከገለጽን በኋላ በዋናነት ስለተነሣንበት ዐቢይ ርእስ ስለ ፍልሰታ ጾም በስፋት ለመዳሰስ እንሞክራለን፡፡
የፍልሰታ ጾም ከሰባቱ አጽዋማት አንዷ ነች፡፡ በደመቀና በተለየ ሁኔታ የምትጾምበት ምክንያት ምን እንደሆነና ሌሎች ተያያዥ ጥያቄዎች በማንሳት የቤተ ክርስቲያንን ሊቃውንት መልስ ጭምር ይዘን ቀርበናል መልካም ንባብ፡፡