መንፈሳዊነት
ኦርቶዶክሳዊነት ርትዕት ሃይማኖት፣ ጽኑ እምነት፣ መልካም ምግባርና መንፈሳዊ እውቀት በአንድነት የተዋሐዱበት፤ አርአያ እግዚአብሔርን አጽንቶ በሐዋርያዊ የሕይወት ተጋድሎ እግዚአብሔርን በግብር ወደ መምሰል የሚታደግበት ፍጹም ሰማያዊ ሕይወት በመሆኑ፤ አባላት በየትኛውም ቦታ፣ ጊዜና ሁኔታ በማሰብ፣ በመናገር እና በመሥራት/በተግባር በሚገለጽ ክርስቲያናዊ ሥነ ምግባር ታንጸው፣ ፍኖተ አበውን ተከትለው፣ በታማኝነት እና በፈሪሐ እግዚአብሔር ቤተ ክርስቲያንን በቅንነት ያገለግላሉ::
መጽሐፈ ጤፉት ለኅትመት በቃች
መስከረም 12 ቀን 2007 ዓ.ም.
መምህር ሳሙኤል ተስፋዬ
የግቢ ጉባኤያት ተተኪ ሰባኪያነ ወንጌል ተመረቁ
መስከረም 12 ቀን 2007 ዓ.ም.
በእንዳለ ደምስስ
በአምስት የማኅበረ ቅዱሳን ማስተባበሪያ ማእከላት አስተባባሪነት በስድስት የሥልጠና ቦታዎች ለአንድ ወር ሲሰጣቸው የነበረውን የደረጃ ሁለት ሥልጠና በማጠናቀቅ 357 የግቢ ጉባኤያት ተተኪ ሰባክያነ ወንጌል ተመረቁ፡፡
በአማርኛ ቋንቋ በዝዋይ ሐመረ ብርሃን ቅዱስ ገብርኤል ገዳምና የካህናት ማሠልጠኛ 70፤ በሐዋሳ ደብረ ታቦር ቅዱስ ሩፋኤል ቤተ ክርስቲያን 45፤ በጅማ ፍኖተ ብርሃን የካህናት ማሠልጠኛ 42፤ በማይጨው የካህናት ማሠልጠኛ 34፤ በባሕር ዳር ሰላም አርጊው ቅድስት ማርያም 83 ሠልጣኞች የሠለጠኑ ሲሆን፤ በኦሮምኛ ቋንቋ በአሰላ ደብር ቅዱስ ደብረ መዓዛ አቡነ ተክለ ሃይማኖት ገዳም የካህናት ማሠልጠኛ 83 የግቢ ጉባኤያት ተተኪ ሰባክያነ ወንጌል ሥልጠና ወስደው ተመርቀዋል፡፡
ጼዴንያ ማርያም
መስከረም 9 ቀን 2007 ዓ.ም.
ማኅበረ ቅዱሳን በገዳማትና በአብነት ትምህርት ቤቶች ዙሪያ እያከናወናቸው የሚገኙ ውጤታማ ተግባራት
መስከረም 8 ቀን 2007 ዓ.ም.
እንዳለ ደምስስ
በጂንካ ማእከል አበረታች ሐዋርያዊ አገልግሎት እየተከናወነ ነው
መስከረም 6 ቀን 2007 ዓ.ም.
ከነሐሴ 29 ቀን እስከ ጳጉሜን 4 ቀን2006 ዓ.ም ዐሥር አባላት ያሉት የማኅበረ ቅዱሳን የስብከተ ወንጌል ማስፋፊያ መርሐ ግብር የልኡካን ቡድን በጂንካ ማእከል በመገኘት በሐዋርያዊ አገልግሎት ላይ ተወያይቷል፡፡ ልኡካን ቡድኑ በጂንካ ማእከል ድጋፍ የሚደረግላቸውን በሣልማ ኪዳነ ምሕረት ቤተ ክርስቲያን የሚገኙ የአብነት ተማሪዎችንና በሸጲ ገይላ የሚገኘውን የ“ስብከት ኬላ” ጎብኝቷል፡፡
የሰሜን አሜሪካ ሰንበት ት/ቤቶች አንድነት ጉባኤ 14ኛ ዓመት ጠቅላላ ጉባኤውን አካሄደ
መስከረም 2 ቀን 2006 ዓ.ም.
ከሰሜን አሜሪካ ማእከል
የ2007 አጽዋማትና በዓላት
ጳጉሜን 5 ቀን 2006 ዓ.ም. መስከረም 1 ሐሙስ፣ ነነዌ ጥር 25፣ ዓብይ ጾም የካቲት 9፣ ደብረ ዘይት መጋቢት 6፣ ሆሣዕና መጋቢት 27፣ ስቅለት ሚያዚያ 2፣ ትንሣኤ ሚያዚያ 4፣ ርክበ ካህናት ሚያዚያ 28፣ ዕርገት ግንቦት 13፣ ጰራቅሊጦስ ግንቦት 23፣ ጾመ ሐዋርያት ግንቦት 24፣ ምሕላ ድኅነት ግንቦት 26፣
ቅዱስ ፓትርያርኩ የአዲስ ዓመት የእንኳን አደረሳችሁ መልእክት አስተላለፉ
ጳጉሜን 4 ቀን 2006 ዓ.ም.
የመግለጫውን ሙሉ ቃል አቅርበነዋል፡፡
ሀገር ዓቀፍ ዐውደ ጥናት ተካሔደ
ጳጉሜን 3 ቀን 2006 ዓ.ም.
እንዳለ ደምስስ
በማኅበረ ቅዱሳን ጥናትና ምርምር ማእከል የተዘጋጀው 6ኛው ሀገር ዓቀፍ ዐውደ ጥናት ጳጉሜን 1 ቀን 2006 ዓ.ም. በማኅበሩ ሕንፃ መሰብሰቢያ አዳራሽ ተካሔደ፡፡
የንባብ ምልክቶች
ነሐሴ 30 ቀን 2006 ዓ.ም.
መ/ር ደሴ ቀለብ
በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የፊሎሎጂ መምህር
የማንሳት ምልክት
የመጣል ምልክት
የማጥበቅ ምልክት
አንዳንድ የግእዝ ግሶች የሚጠብቅ ድምፅ ሲኖራቸው ግማሾቹ የላቸውም፡፡
ምሳሌ፣ ቀተለ — ገደለ፣ ቀደሰ — አመሰገነ