ለአብነት መምህራንና ተማሪዎች ለስብከተ ወንጌል አገልግሎት የሚያግዝ ስልጠና ተሰጠ

ግንቦት 3 ቀን 2007 ዓ.ም.

ከደሴ ማእከል

በማኅበረ ቅዱሳን ደሴ ማእከልና ደሴ ወረዳ ማእከል አስተባባሪነት ከሚያዚያ 18 – 24 ቀን 2007 ዓ.ም. ከዘጠኝ ወረዳዎች ለተውጣጡ ዐሥራ ስምንት የአብነት መምህራንና ተማሪዎች ለሐዋርያዊ አገልግሎት የሚያበቃ ስልጠና ተሰጠ፡፡

ለተከታታይ ለሰባት ቀናት በተሰጠው ስልጠናም ትምህርተ ሃይማኖት፤ ሐዋርያዊ ተልእኮ፤ ትምህርተ ኖሎት እና የቤተ ክርስቲያን ታሪክ ስልጠናው ተሰጥቷል፡፡

በስልጠናው ላይ የተሳተፉት መምህራንና ተማሪዎቹ ከፍተኛ ተሳትፎ ያደረጉ ሲሆን፤ የተሰጣቸው ስልጠና ለስብከተ ወንጌል አገልግሎት በንቃት እንድንሳተፍ ያደርገናል ሲሉ አስተያየታቸውን ሰጥተዋል፡፡

በሥልጠናው ማብቂያ ላይ በማእከሉ የሕክምና ቡድን ለሁሉም ሠልጣኖች የተሟላ የጤና ምርመራ በማድረግ የመድኃኒት ድጋፍ ተደርጎላቸዋል፡፡