መንፈሳዊነት
ኦርቶዶክሳዊነት ርትዕት ሃይማኖት፣ ጽኑ እምነት፣ መልካም ምግባርና መንፈሳዊ እውቀት በአንድነት የተዋሐዱበት፤ አርአያ እግዚአብሔርን አጽንቶ በሐዋርያዊ የሕይወት ተጋድሎ እግዚአብሔርን በግብር ወደ መምሰል የሚታደግበት ፍጹም ሰማያዊ ሕይወት በመሆኑ፤ አባላት በየትኛውም ቦታ፣ ጊዜና ሁኔታ በማሰብ፣ በመናገር እና በመሥራት/በተግባር በሚገለጽ ክርስቲያናዊ ሥነ ምግባር ታንጸው፣ ፍኖተ አበውን ተከትለው፣ በታማኝነት እና በፈሪሐ እግዚአብሔር ቤተ ክርስቲያንን በቅንነት ያገለግላሉ::
ማኅበረ ቅዱሳን የጠራው ሰልፍ እንደሌለ አስታወቀ
ጥቅምት 7 ቀን 2007 ዓ.ም.
በተለያዩና ባልታወቁ አካላት ለማኅበሩ አጋርነት ለማሳየት በመጪው እሑድ በቅድስት ሥላሴ ካቴድራል ሰልፍ ለማድረግ በማኅበራዊ ሚዲያው የሚሽከረከረውን አስመልክቶ ከአባላቱ ለቀረበለት ጥያቄ የሚያውቀው ነገር እንደሌለና ማኅበሩም ምንም ዓይነት ጥሪም እንዳላካሔደ የማኅበረ ቅዱሳን የሕዝብ ግንኙነት ክፍል አስታወቀ፡፡
33ኛው አጠቃላይ ሰበካ መንፈሳዊ ጉባኤ የሦስተኛ ቀን ውሎ
ጥቅምት 7 ቀን 2007 ዓ.ም. መ/ር ሳሙኤል ተስፋዬ የ33ኛው የሰበካ መንፈሳዊ ጉባኤ በሀገር ውስጥና በውጭ የሚገኙ ሀገረ ስብከቶችን የ2006 ዓ.ም. የሥራ ክንውን ሪፖርት አደመጠ፡፡ ሦስተኛ ቀኑን የያዘው ይህ ጉባኤ በሀገረ ስብከቶች አማካኝነት የቀረበውን ሪፖርቶች ያደመጠ ሲሆን በአብዛኛው የሀገረ ስብከቶች ሪፖርት ማኅበረ ቅዱሳን ለቤተ ክርስቲያን የሚያደርገውን ሁለገብ ድጋፍ ከፍተኛ መሆኑን በሪፖርቶቹ የቀረቡ ሲሆን የጉባኤው ታዳሚም አድናቆቱን […]
33ኛው አጠቃላይ የሰበካ መንፈሳዊ ጉባኤው እንደቀጠለ ነው፡፡
ጥቅምት 6 ቀን 2007 ዓ.ም.
መ/ር ሳሙኤል ተስፋዬ
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ጥቅምት 5 ቀን 2ዐዐ7 ዓ.ም የተጀመረው የሰበካ መንፈሳዊ ጉባኤ ቀጥሏል፡፡ በጥቅምት 5 ቀን የከሰዓት ውሎና ጥቅምት 6 ቀን ጠዋት 24 አህጉረ ስብከቶች ሪፓርቶቻቸውን አቅርበዋል፡፡
ማኅበረ ቅዱሳን በ2006 ዓ.ም ከ13,948,984.71 በላይ ወጪ በማድረግ የቤተ ክርስቲያንን አገልግሎት ደገፈ
ጥቅምት 5 ቀን 2007 ዓ.ም.
መ/ር ሳሙኤል ተስፋዬ
በ33ኛው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን መንበረ ፓትርያርክ ሰበካ መንፈሳዊ ጉባኤ ላይ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ጠቅላይ ሥራ አስኪያጅ ባቀረቡት ሪፖርትና በዐዋጅ ነጋሪ መጽሔት 6ኛ ዓመት ቁጥር 10 ጥቅምት 2007 ዓ.ም ላይ በተገለጸው ሪፖርት ውስጥ የማኅበረ ቅዱሳን የ2006 ዓ.ም የሥራ አፈጻጸም ሪፖርት ከነጻ ሞያ አገልግሎት ውጭ ከ13,948.984.7 /አሥራ ሦስት ሚሊዮን ዘጠኝ መቶ ዐርባ ስምንት ሺሕ ዘጠኝ መቶ ሰማንያ ዐራት ብር/ በላይ ወጪ በማድረግ የቤተ ክርስቲያንን አገልግሎት መደገፉ ተገልጿል፡፡
33ኛው አጠቃላይ ሰበካ መንፈሳዊ ጉባኤ በጠቅላይ ቤተ ክህነት ስብከተ ወንጌል አዳራሽ ተጀመረ
ጥቅምት 5 ቀን 2007 ዓ.ም.
መ/ር ሳሙኤል ተስፋዬ
“ቄስ” ገዳሙ ደምሳሽ በቋሚ ሲኖዶስ ውሳኔ ከቤተ ክርስቲያን አንድነት ተለዩ
ጥቅምት 5 ቀን 2007 ዓ.ም
በዲ/ን ፍቃዱ ዓለሙ
በኑፋቄ ትምህርታቸው ምእመናንን ሲቀስጡና የማኅበረ ካህናቱንና ምእመናኑን አንድነት ሲጎዱ የቆዩት “ቄስ” ገዳሙ ደምሳሽ በቋሚ ሲኖዶስ ውሳኔ ከቅስናና ከቤተ ክርስቲያን ሓላፊነት እንዲሁም ከማንኛውም ክህነታዊ አገልግሎትና ትምህርተ ወንጌል ከመስጠት ታገዱ፡፡
33ኛው የመንበረ ፓትርያርክ አጠቃላይ ሰበካ መንፈሳዊ ጉባኤ ሊካሄድ ነው፡፡
ጥቅምት 4 ቀን 2007 ዓ.ም. በመ/ር ሳሙኤል ተስፋዬ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን የመንበረ ፓትርያርክ አጠቃላይ ሰበካ መንፈሳዊ ጉባኤ 33ኛው መደበኛ ስብሰባ ከጥቅምት 5-8 ቀን 2007 ዓም. በመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ስብከተ ወንጌል አዳራሽ ይካሄዳል፡፡ በመንፈሳዊ ጉባኤው ላይ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ፓትርያርክ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት፤በሀገር ውስጥና […]
ማኅበረ ቅዱሳን ለሰዋስወ ብርሃን ቅዱስ ጳውሎስ መንፈሳዊ ኮሌጅ 90 ሺሕ ብር የሚገመት የቁሳቁስ ድጋፍ አደረገ
ጥቅምት 3 ቀን 2006 ዓ.ም.
በእንዳለ ደምስስ
ማኅበረ ቅዱሳን ለአንጋፋውና የሊቃውንት መፍለቂያ ለሆነው የሰዋስወ ብርሃን ቅዱስ ጳውሎስ መንፈሳዊ ኮሌጅ 90 ሺሕ ብር የሚያወጡ ኮምፒዩተሮች፤ ፕሪንተሮችና መጻሕፍት ጥቅምት 1 ቀን 2007 ዓ.ም. ለኮሌጁ ደቀመዛሙርት አገልግሎት እንዲውል ድጋፍ አደረገ፡፡
የጅማ ሀገረ ስብከት ሁለገብ ዘመናዊ ሕንፃ ተመረቀ
መስከረም 27 ቀን 2007 ዓ.ም.
እንዳለ ደምስስ
በመስቀል በዓል መጨመር ወይም መቀነስ የሌለበት የትኛው ነው?
መስከረም 20 ቀን 2006 ዓ.ም.
በዲ/ን ፍቃዱ ዓለሙ