መንፈሳዊነት
ኦርቶዶክሳዊነት ርትዕት ሃይማኖት፣ ጽኑ እምነት፣ መልካም ምግባርና መንፈሳዊ እውቀት በአንድነት የተዋሐዱበት፤ አርአያ እግዚአብሔርን አጽንቶ በሐዋርያዊ የሕይወት ተጋድሎ እግዚአብሔርን በግብር ወደ መምሰል የሚታደግበት ፍጹም ሰማያዊ ሕይወት በመሆኑ፤ አባላት በየትኛውም ቦታ፣ ጊዜና ሁኔታ በማሰብ፣ በመናገር እና በመሥራት/በተግባር በሚገለጽ ክርስቲያናዊ ሥነ ምግባር ታንጸው፣ ፍኖተ አበውን ተከትለው፣ በታማኝነት እና በፈሪሐ እግዚአብሔር ቤተ ክርስቲያንን በቅንነት ያገለግላሉ::
33ኛው አጠቃላይ ሰበካ መንፈሳዊ ጉባኤ በጠቅላይ ቤተ ክህነት ስብከተ ወንጌል አዳራሽ ተጀመረ
ጥቅምት 5 ቀን 2007 ዓ.ም.
መ/ር ሳሙኤል ተስፋዬ
“ቄስ” ገዳሙ ደምሳሽ በቋሚ ሲኖዶስ ውሳኔ ከቤተ ክርስቲያን አንድነት ተለዩ
ጥቅምት 5 ቀን 2007 ዓ.ም
በዲ/ን ፍቃዱ ዓለሙ
በኑፋቄ ትምህርታቸው ምእመናንን ሲቀስጡና የማኅበረ ካህናቱንና ምእመናኑን አንድነት ሲጎዱ የቆዩት “ቄስ” ገዳሙ ደምሳሽ በቋሚ ሲኖዶስ ውሳኔ ከቅስናና ከቤተ ክርስቲያን ሓላፊነት እንዲሁም ከማንኛውም ክህነታዊ አገልግሎትና ትምህርተ ወንጌል ከመስጠት ታገዱ፡፡
33ኛው የመንበረ ፓትርያርክ አጠቃላይ ሰበካ መንፈሳዊ ጉባኤ ሊካሄድ ነው፡፡
ጥቅምት 4 ቀን 2007 ዓ.ም. በመ/ር ሳሙኤል ተስፋዬ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን የመንበረ ፓትርያርክ አጠቃላይ ሰበካ መንፈሳዊ ጉባኤ 33ኛው መደበኛ ስብሰባ ከጥቅምት 5-8 ቀን 2007 ዓም. በመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ስብከተ ወንጌል አዳራሽ ይካሄዳል፡፡ በመንፈሳዊ ጉባኤው ላይ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ፓትርያርክ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት፤በሀገር ውስጥና […]
ማኅበረ ቅዱሳን ለሰዋስወ ብርሃን ቅዱስ ጳውሎስ መንፈሳዊ ኮሌጅ 90 ሺሕ ብር የሚገመት የቁሳቁስ ድጋፍ አደረገ
ጥቅምት 3 ቀን 2006 ዓ.ም.
በእንዳለ ደምስስ
ማኅበረ ቅዱሳን ለአንጋፋውና የሊቃውንት መፍለቂያ ለሆነው የሰዋስወ ብርሃን ቅዱስ ጳውሎስ መንፈሳዊ ኮሌጅ 90 ሺሕ ብር የሚያወጡ ኮምፒዩተሮች፤ ፕሪንተሮችና መጻሕፍት ጥቅምት 1 ቀን 2007 ዓ.ም. ለኮሌጁ ደቀመዛሙርት አገልግሎት እንዲውል ድጋፍ አደረገ፡፡
የጅማ ሀገረ ስብከት ሁለገብ ዘመናዊ ሕንፃ ተመረቀ
መስከረም 27 ቀን 2007 ዓ.ም.
እንዳለ ደምስስ
በመስቀል በዓል መጨመር ወይም መቀነስ የሌለበት የትኛው ነው?
መስከረም 20 ቀን 2006 ዓ.ም.
በዲ/ን ፍቃዱ ዓለሙ
መጽሐፈ ጤፉት ለኅትመት በቃች
መስከረም 12 ቀን 2007 ዓ.ም.
መምህር ሳሙኤል ተስፋዬ
የግቢ ጉባኤያት ተተኪ ሰባኪያነ ወንጌል ተመረቁ
መስከረም 12 ቀን 2007 ዓ.ም.
በእንዳለ ደምስስ
በአምስት የማኅበረ ቅዱሳን ማስተባበሪያ ማእከላት አስተባባሪነት በስድስት የሥልጠና ቦታዎች ለአንድ ወር ሲሰጣቸው የነበረውን የደረጃ ሁለት ሥልጠና በማጠናቀቅ 357 የግቢ ጉባኤያት ተተኪ ሰባክያነ ወንጌል ተመረቁ፡፡
በአማርኛ ቋንቋ በዝዋይ ሐመረ ብርሃን ቅዱስ ገብርኤል ገዳምና የካህናት ማሠልጠኛ 70፤ በሐዋሳ ደብረ ታቦር ቅዱስ ሩፋኤል ቤተ ክርስቲያን 45፤ በጅማ ፍኖተ ብርሃን የካህናት ማሠልጠኛ 42፤ በማይጨው የካህናት ማሠልጠኛ 34፤ በባሕር ዳር ሰላም አርጊው ቅድስት ማርያም 83 ሠልጣኞች የሠለጠኑ ሲሆን፤ በኦሮምኛ ቋንቋ በአሰላ ደብር ቅዱስ ደብረ መዓዛ አቡነ ተክለ ሃይማኖት ገዳም የካህናት ማሠልጠኛ 83 የግቢ ጉባኤያት ተተኪ ሰባክያነ ወንጌል ሥልጠና ወስደው ተመርቀዋል፡፡
ጼዴንያ ማርያም
መስከረም 9 ቀን 2007 ዓ.ም.
ማኅበረ ቅዱሳን በገዳማትና በአብነት ትምህርት ቤቶች ዙሪያ እያከናወናቸው የሚገኙ ውጤታማ ተግባራት
መስከረም 8 ቀን 2007 ዓ.ም.
እንዳለ ደምስስ