“ሊከተለኝ የሚወድ… መስቀሉን ተሸክሞ ይከተለኝ”

ቀሲስ ፋሲል ታደሰ
ቀን፡ መስከረም 13 / 2003 ዓ.ም.

መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የሰው ልጆችን ፍቅር ስለገለጠበት ሕማምና ሞቱ ለደቀመዛሙርቱ ባስተማረበት ወቅት ለእነርሱም “እኔን ሊከተል የሚወድ ራሱን ይካድ ጨክኖም መስቀሌን ተሸክሞ ይከተለኝ” ብሏቸዋል፡፡ አስቀድሞ “የሰው ልጅ ይሰቀል ዘንድ ይገባዋል” በማለት ነገረ ድኅነትን የሚፈጽምልን በዕፀ መስቀሉ እንደሆነ ተናግሯል፡፡ ጊዜው ሲደርስም በቀራንዮ መስቀል ላይ ዋለ በገዛ ፈቃዱ ስለ ሰው ልጆች መዳን ቅድስት ነፍሱን ከቅዱስ ሥጋው ለየ፡፡ በአካለ ነፍስ ወደ ሲዖል ወርዶ ነፍሳትን ወደ ገነት አሸጋገረ፤ የዲያብሎስንም ሥራ በመስቀሉ ድል ነሣ ሰላምን አደረገ፡፡ “በእኛ የነበረውን የሚቃወመንንም በትእዛዛት የተጻፈውን የዕዳ ጽሕፈት ደመሰሰው እርሱንም /ዲያብሎስ/ በመስቀሉ ጠርቆ ከመንገድ አስወግደታል እንደሚል /ቆላ. 2÷20/

ቅዱስ ዮሐንስ “ወበዝንቱ ተዐውቀ ፍቅሩ ለእግዚአብሔር የእግዚአብሔር ፍቅሩ በዚህ ታወቀ” በማለት እንደገለጸው አምላካዊ ፍቅሩን በሕማማተ መስቀሉ አሳይቶናል  /1ኛ ዮሐ.4÷10/፡፡ ሕግን የጣስን ቅጣትም የሚገባን የሰው ልጆች ሆነን ሳለ ነገር ግን ከቸርነቱ ብዛት “የሟቹን ሞት አልወድም” በማለት በዘለዓለም ሞት ተቀጥተን እንድንኖር አልወደደምና በሕማማተ መስቀሉ “ደዌያችንን ተቀበለ ሕማማችንን ተሸከመ ስለ እኛም ታመመ… በእርሱ ቁስል እኛ ተፈወስን” /ሕዝ.18÷32፣ ኢሳ.53÷4/፡፡

የእግዚአብሔር ፍቅር በመስቀል እንደተገለጠ ሁሉ የሰው ልጆችም እርሱን የመውደዳችን መገለጫ መስቀሉን በመሸከም መከተል እንደሆነ በአምላካዊ ቃሉ አስተምሮናል፡፡ ይህም ማለት እንደ ጌታችን ረጅምና ክብደት ያለው ዕፀ መስቀልን በትከሻችን ተሸክመን ቀራንዮ እንድንጓዝ ሳይሆን መከራ መስቀሉ ስለ እኛ ሲል የፈጸመልን መሆኑን በማመን እና ተከታዮቹ በመሆናችን የሚመጣብንን መከራ በመታገሥ መኖር እንደሚገባን ሲያመለክተን ነው፡፡ በዚህም መሠረት “መስቀል መሸከም” የተባለው በዓለም ስንኖር በክርስትና ምክንያት የሚገጥመንን መከራ ነው፡፡ “በዓለም ግን መከራ ትቀበላላችሁ ነገር ግን ጽኑ እኔ ዓለሙን ድል ነስቼዋለሁና” እንዲል /ዮሐ.16÷33/፡፡ በወቅቱ ይህ ቃል የተነገራቸው ቅዱሳን ሐዋርያት መስቀሉን በመሸከም ማለትም ስለ ክርስትና ኑሮ የመጣባቸውን መከራ በመታገሥ እና ድል በመንሳት ኑረዋል ለዚህም ነው፡፡ “መንግሥተ ሰማያት በብዙ መከራ እንገባ ዘንድ ያስፈልገናል” በማለት በቃልም በተግባርም የገለጹት /ሐዋ.14÷22/፡፡ የክርስትና ጉዞ እንደ ቀራንዮ ጉዞ መከራ የበዛበት ነው፡፡ ፈቃደ ሥጋን እየታገሱ ለፈቃደ ነፍስ እየኖሩ ዓለምን፣ ዲያብሎስን እየተዋጉ እስከ ሞት በመጽናት ተጉዘው የክብር አክሊል የሚቀዳጁበት ሕይወት ነውና “እስከ ሞት ድረስም የታመንህ ሁን የሕይወት አክሊልንም እሰጥሀለሁ” ተብሎ እንደተጻፈ /ራእ.2÷10/፡፡

መከራ ከየት ይመጣል?

1. ከዲያብሎስ ጥንተ ጠላታችን ዲያብሎስ የሰው ልጅን በኃጢአት መጣል ቋሚ ሥራው ነው፡፡ ይልቁንም የመስቀሉን ዓላማ የያዙ ክርስቲያኖችን ይከታተላል፡፡ በተለያዩ ወጥመዶችም ለመያዝ እና መከራ ለማጽናት ይሞክራል፡፡ ቅዱስ ጴጥሮስ “ጠላታችሁ ጋኔን የሚውጠውን ፈልጐ እንደሚያገሳ አንበሳ ይዞራልና” ሲል ቅዱስ ጳውሎስም “ሰልፋችሁ ከጨለማ ገዦች…. ከክፋዎች አጋንንት ጋር ነው” በማለት ውግያውን ገልጾታል፡፡ ቅዱስ ዮሐንስ በራእይ መጽሐፉም በሰይጣን አማካኝነት የተለያዩ መከራዎች እንደሚመጡ ሲያስረዳ እንዲህ ብሏል “ትቀበለውም ዘንድ ስላለህ መከራ አትፍራ እነሆ እንድትፈተኑ ሰይጣን ከእናንተ አንዳንዶችን ወደ እስር ቤት እንዲገቡ ያደርጋል….”/ራእ.2÷10/ ቅዱሳን ከዲያብሎስ የመጣባቸውን መከራ በመታገሥ ለክብር እንደበቁ ገድላት ምስክሮች ናቸው፡፡ “ክርስቶስን በመከራ ትመስሉት ዘንድ ደስ ይበላችሁ” እንደ ተባለው ቅዱስን የመጣባቸውን መከራ በጸጋ በመቀበል ጌታቸውን መስለዋል /1ኛ ጴጥ. 4÷13/፡፡

ጠላታችን ዲያብሎስ ፈቃደ ሥጋን በማስወደድ፣ በደካማ ጐናችን በመፈታተን፣ በሥጋዊ ምኞት ለመጣል መከራ ያመጣብናል፡፡ ለእኛ አብነት እንዲሆነን በተፈጸመው የገዳመ ቆሮንቶስ የዲያብሎስ ፈተና እንደምንገነዘበው “ዛሬም ለእኔ ብትሰግድ፣ ብትገዛ…” በማለት በምኞት ዓለም በማስጐምጀት ከእግዚአብሔር ሊያርቀን ይታገለናል፡፡ ስለሆነም ጌታችንን በክብር የምንመስለው መስቀሉን በመሸከም ከመሰልነው እንደሆነ በማስተዋል ከዲያብሎስ በተለያዩ መንገዶች የሚመጡብንን መከራዎች በመታገሥ እና ድል በመንሣት ለመኖር መዘጋጀት ይጠበቅብናል፡፡ መስቀሉን የመሸከም መገለጫም የሚደርስብንን የተለያየ መከራ መታገሥ እንደሆነም በማስታወስ፤ ክብሩን በማሰብ፤ ክርስቲያናዊ ፈተናን ለመቋቋም እንበርታ፡፡ “ካለው ክብር ጋር ሲመዛዘን መከራው ምንም እንዳይደለ እናውቃለን” እንደሚል /ሮሜ. 8÷18/፡፡


2.    በራሳችን ክፉ ምኞት
– አንዳንድ ጊዜ ከመንፈሳልነት ርቀን የምናውጠነጥነው ክፉ ምኞት በራሳችን ሕይወት ላይ መከራ ሲያመጣብን ይስተዋላል፡፡ ቅዱስ ያዕቆብ “በእናንተ ዘንድ ጥልና መጋደል ከወዴት ይመጣሉ? በሰውነታችሁ ውስጥ የሚሠራውን ዝሙት ከመውደድ የተነሣ ከዚህ አይደለምን….” በማለት ከራስ ክፉ ምኞት መከራ እንደሚመጣ ያስገነዝበናል፡፡ በመንፈስ ስንዝል ኃጢአት መጓዝ እንጀምራለን፡፡ አምኖን በገዛ ምኞቱ ተፈትኖ በዝሙት እንደወደቀ ሁሉ ዛሬም በራሳችን ክፉ ምኞት በመገፋፋት በኃጢአት በመውደቅ ዳግማዊ አምኖን እንዳንሆን ያስፈልጋል /2ኛ ሳሙ.13÷1/፡፡  በአብዛኛው ያለፈቃዳችን የምንሠራው ኃጢአት እንደሌለ ልናጤን ይገባናል፡፡ ይህንንም “ነገር ግን እያንዳንዱ በራሱ ምኞት ሲሳብና ሲታለል ይፈተናል” እንዲል /ያዕ 1÷14/፡፡

በመሆኑም ለክፉ ምኞት ተጋላጭ የሆነውን ኅሊናችንን በመግዛት፤ ለመልካም ሥራ መነሣሣት መታገል በራሱ መስቀል መሸከም መሆኑን ዘወትር ልንዘነጋ አይገባንም፡፡ በፈቃደ ሥጋ ለተዘፈቅንም ከዚህ ለመውጣት የሚደረገው ትግል ተገቢ መሆኑን በመረዳት መንፈሳዊ ተጋድሎውን ልናፀና ይገባልና፡፡ “ሰውነቱን በመከራ የሚያሰቃያትን አመስግኑት” /ኢሳ. 49÷7/ ተብሎ እንደተጻፈ የፈቃደ ሥጋ ምኞት የሆኑትን ዝሙት፣ ሱሰኝነትን፣ መዳራት… የመሳሰሉትን ድል ለመንሣት መታገል የሚያስመሰግን ተግባር ነው፡፡ ስለዚህም የሥጋን ሥራ በመንፈሳዊ ሥራ በመተካት ከራሳችን ምኞት ፈተና እንዳይጸናብን መንገዱን ለመዝጋት እየጣርን በጾም በጸሎት ረድኤተ እግዚአብሔርን አጋዥ እናድርግ፡፡ “እንደ እግዚአብሔር ፈቃደ መከራን የሚቀበሉ ሰዎችም መልካም ሥራን በመሥራት ለታመነ ፈጣሪ ነፍሳቸውን አደራ ይስጡ” ተብሏልና /1ጴጥ.4÷19/፡፡

3.    ካላመኑ ወገኖች- በክርስትና ኑሮ ላይ መከራ ከሚመጣበት አንድ ካለመኑ ወገኖች ነው፡፡ ከዘመነ አበው ጀምሮ በአምልኮተ እግዚአብሔር የዳኑ ሰዎች እግዚአብሔርን ከማያምኑ ወገኖች መከራ ሲመጣባቸው ኖሯል፡፡ የግብጹ ፈርዖን እሥራኤል ላይ መከራ ማጽናቱ እና ከዐሥሩ የቅስፈት ዓይነቶች አለመማሩ ያለማመኑ ውጤት ነው፡፡ በመሆኑም እሥራኤል ባሕረ ኤርትራን ሲሻገሩ ፍጻሜው ስጥመት ሆኗል፡፡ ቅዱሳን ሐዋርያትን አይሁድ ጣዖት አምላኪዎች እና ጠንቋዮች መከራ ያጸኑባቸው እንደነበር በሐዋርያት ሥራ ተመዝግቧል፡፡ ለምሳሌ ኤልማስ የተባለ ጠንቋይ ወንጌልን እንዳይሰብኩ ሲፈታተናቸው፤ ሌሎች ደግሞ መጽሐፎቻቸውን በማቃጠል የአገልግሎት እንቅፋት ሆነውባቸዋል፡፡ እንደዚሁም በማሳደድ እና በመግረፍም ሄሮድስና ሌሎችም ዐላውያን ነገሥታት መከራ ያመጡባቸው ነበር፡፡ /ሐዋ.13÷8፤19÷19/ ለዚህም ነው፡፡ “መከራ ተቀብለን ተንገላተን ወንጌልን ተናገርን” በማለት ቅዱስ ጳውሎስ መከራቸውን የገለጸው /1ኛ ተሰ.2÷2/ በተጨማሪም ስደት መራብ መጠማት ነቀፋ.. እና የመሳሰሉት በአገልግሎታቸው ጊዜ የተለመደ መከራ ስለመሆኑ እና ነገር ግን የቅዱሳን አበው ጭንቀት ከሌሎች ስለሚመጣው መከራ ሳይሆን የአብያተ ክርስቲያናት ሐሳብ ስለመሆኑ ለቆሮንቶስ ክርስቲያኖች በጻፈው መልእክቱ አስገንዝቧል/ 2ኛ ቆሮ.11÷28/፡፡ የዘመነ ሰማዕታት ቅዱሳን ሰዎች ኑሮም እንደሚያስረዳው በየዋሻው እምነታቸውን የገለጡበት እና ደማቸውን ስለ ክርስትና ያፈሰሱት እንደእነ ዲዮቅልጥያኖስ እና መሰሎቹ ካመጡባቸው መከራ የተነሣ መሆኑን የቤተ ክርስቲያን ታሪክ ማስረጃ ነው፡፡ በዘመናችንም በተለያዩ መንገዶች በኢየሱስ ክርስቶስ የባሕርይ አምላክነት ካላመኑ ወገኖች መከራ ሊመጣ ይችላል፡፡ አይሁድ የክርስቶስን መስቀል እንደቀበሩ፤ የቤተ ክርስቲያንን ትውፊትና ሥርዓተ ትምህርት ለመቅበር በመሯሯጥ በተዋሕዶ እምነታቸው የዳኑትን ምእመናን እና አገልጋዮችን የሚፈታተኑ ተረፈ አይሁድ በየዘመኑ ይነሣሉና፡፡ “በመጣባችሁ መከራ አትደነቁ” እንደተባለ፤ ስለ ሃይማኖት ከማያምኑ /ከተጠራጣሪዎች/ በሚመጣው ፈተና ሳንታወክ በመንፈሳዊ ሕይወት እና በተዋሕዶ ትምህርት ልንጸና ይገባናል፡፡

ከላይ የጠቀስናቸውን የመከራ ምንጮች መሠረት አድርገን በዘመናችን ስላለው መከራም ልናተኩር ይገባናል፡፡ በክርስትና ኑሮ ላይ እየተፈታተኑን የሚገኙትን የመከራ ዓይነቶች ከራሳችን እና ከውጪ ብለን ብንጠቁም ለመረዳት ግልጽ ይሆናል፡፡ ለአብነት ያህልም ከራሳችን ከሚመጡብን የወቅቱ ችግሮት ሁለቱን እንመልከት፡፡

1.    ዓለማዊነት- “ወንድሞች ሆይ ይህን ዓለም አትውደዱ፤ ዓለምን መውደድ ከእግዚአብሔር ጋር ጥል ነው፡፡” ይላል ነገር ግን ከሰይጣን ግፊት ወይም ከራሳችን ከደካማ ጐን የተነሣ በመውደቅ ለዓለም ምርኮኛ መሆን የተለመደ ሆኗል፡፡ ዓለማዊነት ስንልም በዓለም ውስጥ የሚገኝ የኃጢአት ተግባራት መፈጸምን ነው በዘመናዊነት እና በሥልጣኔ ሰበብ ብዙዎች ለዕውቀትና ለልማት የሚሆነውን በጐ ነገር ከመቀስም ይልቅ ኃጢአታዊ ተግባራት ላይ ሲያተኩሩ ይታያል፡፡ ለምሳሌ ከመጾም መብላትን፣ ከማስቀደስ መተኛትን፣ ከመዝሙር ዘፈንን፣ በሥርዐት ከመልበስ ፋሽን መከተልን… የመሳሰሉትን ማዘውተሩ በዓለማዊ ምኞት የመጠመድ መገለጫ ነው፡፡ በአንድ ወቅት እሥራኤል ከሞዓብ መንደርና ተግባር በመተባበራቸው በጣዖት አምልኮ በዘፈን እና በዝሙት ሲወድቁ ለቅስፈት ተዳርገዋል፡፡ ዛሬም ቢሆን በክርስትና ኑሮ የሚጓዙ ኦርቶዶክሳዊያን ዕውቀት፣ ገንዘብ እና ሀገር መለወጥ ሲገጥማቸው በጐውን ከመጠቀም ይልቅ የሥልጣኔ ትርጓሜ ባለመረዳት የክርስትና ሕይወትን በዓለማዊነት ሲለውጡ በአነጋገር፣ በአለባበስ በውሎ…. በመሳሰሉት ምዓባዊ ሥራ መሥራት እየተብራከተ መጥቷል /ዘኁ.21/፡፡ ስንቶቻችን ነን ከዓለማዊነት ሸክም ርቀን ስለ እግዚአብሔር ፍቅር መስቀሉን ተሸክመን ለመኖር የተዘጋጀን? ዛሬ ዛሬ ከዓለማዊነት የተነሣ ቤተ ክርስቲያንን መከተል ሳይሆን ቤተ ክርስቲያን እንደ እነርሱ ፍላጐት እንድትከተላቸው የሚፈልጉ አይጠፋም፡፡ ለሥርዐት ከመገዛት ይልቅ “ምን አለበት፣ ምን ችግር? አለው” በሚል ቃላት ተደልለው ለቀኖና ቤተ ክርስቲያን ቸልተኛ ከመሆን እስከ ኑፋቄ መድረስ እየተለመደ ነው፡፡ ስለዚህም ለሥጋ ሥራ የሚያተጋውን ዓለማዊነትን አርቀን ለመንፈስ ፍሬዎች የሚያበቃውን ነገረ መስቀሉን እየሰብን ጌታችንን በእውነት ልንከተለው ይገባናል፡፡

2.  ፍቅረ ንዋይ– ባለንበት ወቅት በፍቅረ እግዚአብሔር እንዳንጸና ከሚፈታተነን አንዱ ገንዘብ ወዳድ መሆን ነው፡፡ ይሁዳ እንደ ሌሎቹ ደቀመዛሙርት መስቀሉን ተሸክሞ እንዳይከተል ጠልፎ የጣለው ኃጢአት ፍቅረ ንዋይ መሆኑ የታወቀ ነው፡፡ ዛሬስ ለምን በዐሥራት አልታመንም? ሰንበትና በዓላትን አላከበርንም…? ብለን ራሳችንን ብንመረምር ያለኝ ይበቃኛል የሚለውን ምክር ወደ ጐን ትተን በፍቅረ ንዋይ መጠመዳችንን የሚያሳይ ነው፡፡ የሙስና መብዛት፤ አጭበርባሪነት መበራከት፤ በንግድና በተለያዩ ዘርፎች አታላይነት ከመጠን ማለፉ ፍቅረ ንዋይ ሲጸናወተን እንጂ ሌላ ምን ሊሆን ይችላል? ቅዱስ ጳውሎስ “ገንዘብ መውደድ የክፋት ሁሉ ሥር ነው” በማለት እንደ ገለጸው ለገንዘብ ሲባል በየቤቱ፣ በየቢሮው፣ እና በተለያዩ ቦታዎች የክፉ ሥራ መበራከት የሰላም መጥፋት የአደባባይ ምስጢር አይደለምን? /1ኛ ጢሞ.6÷10/

ከውጪያዊ አካላት የሚመጡብንን የክርስትና ሕይወት እንቅፋቶች ለመዘርዘር ይህ አጭር ጽሑፍ በቂ አይሆንም፡፡ ነገር ግን ለአብነት ያህል አንዱን እንመልከት-

ሀ.   የሐሰት ክስ /ስም ማጥፋት/– ዲያብሎስ የታወቀው እና ሥራውን የጀመረው በሐሰት ንግግር መሆኑ ይታወቃል፡፡ በዓለመ መላእክት “እኔ ነኝ ፈጣሪ” ማለቱ እና አዳምና ሔዋንን በሐሰት ትምህርት ማጥመድ የሐሰት አባትነቱን አረጋግጦለታል፡፡ ጥንትም ሆነ ዛሬ በሐሰት አባትነቱን አረጋግጦለታል፡፡ ጥንትም ሆነ ዛሬ በሐሰት አንደበት የግብር ልጆቹ የሆኑ ሐሳዋውያን እውነተኞች በሐሰት ሲከስሱ እና ስማቸውን ሲያጠፉ ይገኛሉ፡፡ በእግዚአብሔር ቃል ጸንተው እውነትን ይዘው የሚታገሉትን ከሚገጥማቸው ፈተና አንዱ ከሐሰተኞች የሚሰነዘር ስም ማጥፋት ዘመቻ መሆኑ እየተለመደ መጥቷል፡፡ በመሠረቱ አይሁድ መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስን በሐሰት መክሰሳቸውን ያስተዋለ ክርስቲያን በዚህ ሊደነቅ አይገባውም፡፡ በዘመነ ብሉይ ሶስናን ብናስታውስ ያልፈጸመችውን እንደ ፈጸመችው አድርገው በሐሰት ከሰዋት ለፍርድ ያበቋት ረበናት ለጊዜው ስም ማጥፋቱ ቢሳካላቸውም እውነቱ ሲገለጥ ግን ውርደቱ እና ቅጣቱ በእነርሱ ላይ ሆኗል፡፡ ዛሬም በቤተ ክርስቲያን አገልግሎት የተጠመዱትን ከአባቶች እስከ ምእመናን በሚገኙ አገልጋዮች ላይ ስም ለማጥፋት የሚሯሯጡ ውሉደ ሐሰት ተበራክተዋል፡፡ ንስሐ ካልገቡ ፍጻሜያቸው እንደ ረበናቱ ይሆናል፡፡ ቅዱስ ጳውሎስ “በሌላ ትፈርድ ዘንድ ማነህ? … እርሱን እግዚአብሔር ሊያቆመው ይችላልና” /ሮሜ.14÷4/ በማለት እንዳስተማረው ሐሰተኞች የፈረዱባቸው ወገኖች አጥፍተው እንኳን ቢሆን ንስሐ ገብተው እንደሆነ ምን እናውቃለን? በውኑ የአገልግሎት ማኅበራትን አባቶችን የቤተ ክርስቲያን ሓላፊዎችን… ለማዋረድ በመሞከርስ የሚገኘው ጥቅም ምን ይሆን?

አንዳንድ ጊዜ የምንታማበት ነገር እውነት ከሆነም የታማው /የተተቸው/ አካል ልቡ ያውቃልና ራሱን ሊመረምር ይገባል፡፡ ሆኖም ግን ሐሰተኞች /ሰዳቢዎች/ ሊገነዘቡ የሚገባው ለሃይማኖት በመቅናት ከሆነ አገላለጹ ይህ እንዳልሆነ ተረድተው ይልቁንም ክርስቲያን ከባቴ አበሳ መሆን በፍቅር እና በቅርበት ስሕተተኞችን በምክርና በጸሎት በማገዝ ቢሆን የዓመፃ ሳይሆን የእውነት መሆኑ ግልጽ ይሆናል፡፡

ማጠቃለያ

የክርስትና ኑሮ አልጋ በአልጋ እንዳልሆነ ከልብ ከተረዳን እውነትን የያዘ ሁሉ ፈተና ሲገጥመው “መስቀሉን ይሸከም” የሚለውን ቃል ሊያስተውል ይገባል፡፡ የሚገጥመንንም መከራ በሚከተሉት ነጥቦች ድል መንሣት እንችላለን፡፡

1.   ትዕግሥት “ኢዮብ ታገሠ እግዚአብሔርም ሰማው” /ያዕ.5÷11/ ተብሎ እንደተጻፈ ትዕግሥት ይኑረን፡፡ የማይፈተን የተባረከ ነው አልተባለም፤ በፈተና የሚጸና እንጂ፡፡ በመሆኑም ከጌታችን እና እርሱን መስለው ከተገኙ ከቅዱሳን በመማር መስቀሉን በትዕግሥት ተሸክመን ልንጓዝ ይገባል፡፡ ቅዱሳን ሐዋርያትን መከራ አጽንተውባቸው በሸንጐ ሲያቆሟቸው በትዕግሥት ተቀበሉት፡፡ “በሸንጐ ፊት ስለተናቁ ደስ ብሏቸው ወጡ” እንደሚል መከራን በጸጋ ተቀበሉ /ሐዋ. 5÷41/፡፡

2.  ፍቅር– “ከክርስቶስ ፍቅር ማን ይለየናል? መከራ ወይስ ጭንቀት” /ሮሜ 8÷35/ እንደተባለ ፍቅር ያለው መከራን ይታገሣል /1ኛ ቆሮ.13÷7/፡፡ ሊያስፈራን የሚገባ ከእግዚአብሔር መለየት እንጂ፤ በእግዚአብሔር መንገድ ሆነን የሚገጥመን መከራ መሆን የለበትም፡፡ የክርስትና ሕይወትም ሆነ ፍቅረ እግዚአብሔር ዋና መገለጫው መከራ መቀበል መስቀሉን ተሸክሞ በፍቅር መኖር ነውና፡፡ በመሆኑም በትክክለኛ መንገድ ዓላማውን ተረድቶ የመጣ አገልጋይ አስፈሪ ነገሮች እንኳን ቢገጥሙት ወደኋላ አይሸሽም፤ ቅዱሳን ሁሉን ትተው እንደተከተሉት ፍቅረ እግዚአብሔር ራስን እስከ መስጠት ያደርሳልና /ማቴ.19÷19/፡፡

3.    ጽናት- እያንዳንዱ አገልግሎት የራሱ የሆነ ችግር አለው፡፡ ውጤቱም ጽናቱ ላይ ነው “እያንዳንዱ በራሱ ድካም መጠን የራሱን ደመወዝ ይቀበላል” የተባለው እንዲፈጸምልን ጽናት ወሳኝ ነው፡፡ “በሁሉ እንገፋለን እንጂ አንጨነቅም፤… እንሰደዳለን እንጂ አንጣልም…” ብሎ ቅዱስ ጳውሎስ እንደተናገረው ለአገልግሎት ያለንን ቁርጠኝነት በጽናት ልንገልጽ ይገባናል፡፡

በአጠቀላይ የክርስትና ሕይወት መከራው ብዙ ዋጋውም እጅግ ብዙ ነውና በትዕግስት፣ በፍቅር፣ በጽናት ሆነን እንትጋ በመከራ ጽናት መስለነው መስቀሉን ተሸክመን እስከሞት ከተጓዝን ክብርን ያቀዳጀናልና፡፡ በሁሉም ስለ ስሜ የተጠላችሁ ትሆናላችሁ እስከ መጨረሻ የሚጸና ግን እርሱ ይድናል እንደሚል /ማቴ.10÷22/፡፡

ምንጭ፡- ሐመር 18ኛ ዓመት ቁጥር 6 መስከረም 2003

ወስብሐት ለእግዚአብሔር
adye abeba 2006

“በዚህች ዓመት ደግሞ ተዋት” ሉቃ.13÷6-9

ዲ/ን ተስፋሁን ነጋሽ

ጳጉሜ 3/2006 ዓ.ም.

adye abeba 2006

 

ጌታችንና መድኃኒታችን ፈጣሪያችንና አምላካችን እግዚአብሔር ወልድ /ኢየሱስ ክርስቶስ/ በመዋዕለ ሥጋዌው በምሳሌ አድርጐ ወንጌልን አስተምሯል፡፡ በምሳሌ ማስተማር ሊተላለፍ የተፈለገውን መልእክት ሲያስተላልፉት ምግብን በጣፈጠ መረቅ ፈትፍቶ እንደማጉረስ ያህል ይሆናልና፤ እንዲሁም አንድ መልእከት በምሳሌ ጣፍጦ በቋንቋ ዘይቤ ተውቦ ሲቀርብ ምሥጢሩ ልብን ይማርካል፡፡ ስለዚህ የሰው አእምሮ በሃይማኖት ልጓም ተስቦ ለምግባረ ጽድቅ እንዲዘጋጅ ጌታችን ለነጋዴው በወርቅ በዕንቁ፣ ለገበሬው በእርሻ በዘር፣ ለባልትና ባለሙያዎች በእርሾ በቡሆ፣….. ወዘተ እየመሰለ ያስተምር ነበር፡፡ ማቴ.4÷30፡፡

እኛም ጌታ በምሳሌ ካስተማራቸው ትምህርቶች መካከል ለወቅቱ የሚስማማውን መርጠን እንመለከታለን በሉቃ.13÷6-9 ላይ ይህንንም ምሳሌ መሰለ “ለአንድ ሰው በወይኑ አትክልት አጠገብ የተተከለች በለስ ነበረች ግን ፍሬ ሊፈልግባት ቢመጣ ምንም አላገኘም፡፡ ስለዚህ የወይን አትክልት ጠባቂዋን እነሆ ከዚህች በለስ ፍሬ ልፈልግ ሦስት ዓመት እየመጣሁ ምንም አላገኘሁምና ቁረጣት፤ ስለምን ደግሞ መሬቱን ታጐሳሉቁላለች? አለው፡፡” እርሱ ግን መልሶ ጌታ ሆይ ዙሪያዋን እስክኮተኩትላትና ፋንድያ እስካፈስላት ድረስ በዚህች ዓመት ደግሞ ተዋት፡፡ ወደ ፊት ግን ብታፈራ ደህና ነው፤ ያለዚያ ግን ትቆርጣታለህ አለው፡፡” ተብሎ ተጽፏል፡፡

ይህ ከላይ የተገለጸው ምሳሌ በሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያን ሲተረጐም /ሲመሰጠር/ እንዲህ ነው፤ የወይን አትክልት የተባለች ኢየሩሳሌም ናት፣ አንድ ሰው የተባለ እግዚአብሔር ነው፣ በለስ የተባሉ ደግሞ ቤተ እስራኤል ናቸው፡፡ ነቢዩ ኢሳይያስ “እግዚአብሔር ለዘለዓለም አይራብም” ይላል ኢሳ.46÷25፡፡ ራሱ ጌታችንም “የእኔስ መብል የላከኝን ፈቃድ አደርግ ዘንድ ሥራውንም እፈጽም ዘንድ ነው፡፡” ብሏል ዮሐ.4÷35 ፡፡ ስለዚህ ሰማያዊያን መላእክትን እንዳይራቡ ያደረገ አምላክ እስራኤል ዘሥጋን ገበሬ በማያርስበት ዘር በሌለበት ዝናብ በማይጥልበት ምድረ በዳ መና ከሰማይ አውርዶ የመገበ ጌታ ተራበ ሲባል ያስገርማል! ግን ፍጹም አምላክ እንደመሆኑ ፍጹም ሰው ሆኗልና አልተራበም አንልም፤ በሥጋ ተርቧልና የዕፀ በለስ ፍሬን ፈለገ፡፡

ይኸውም የበለስ ውክልና ከተሰጣቸው ቤተ እስራኤል የሃይማኖትና የምግባር ፍሬን እንደፈለገ ያመለክታል፡፡ “በለስ ዘይቤ ቤተ እስራኤል እሙንቱ” ተብሏልና እግዚአብሔር አምላክ በብሉይ ኪዳን በቅዱሳን ነቢያት አድሮ የሃይማኖት /የምግባር/ ፍሬ ባገኝባቸው ብሎ ወደ እስራኤል ሔደ፤ ግን ምንም አላገኘም፡፡ እንዲያውም ሕዝቡ ቅዱሳን ነቢያትን በመጋዝ እየሰነጠቁ፣ በምሳር እየፈለጡ በማጥፋት ከዘመን ዘመን ወደተለያየ አዳዲስ ባዕድ አምልኮአቸው ሲገቡ አየ፡፡ ስለዚህ የበለስዋን ጠባቂ “ሦስት ዓመት እየመጣሁ ምንም ፍሬ አላገኘሁባትምና ቁረጣት” አለው፡፡ ሦስት ዓመት ያለው ዘመነ መሳፍንት፣ ዘመነ ነገሥታትና ዘመነ ካህናትን ነው፡፡ በዚህን ጊዜ የወይን ጠባቂዋ የተባለ መጋቤ ብሉይ ቅዱስ ሚካኤል “ተራድቼ ሥራ እስካሠራቸው ድረስ የዘንድሮን ይቅር በላቸው” እያለ መለመኑን ያጠይቃል፡፡

አንድም ሰው የተባለ አብ ቢሉ በልጁ ህልው ሆኖ፣ ወልድ ቢሉ ሰው ሆኖ ሃይማኖት፣ ምግባር ፍለጋ ወደ እስራኤል ሄደ፡፡ ሦስት ዓመት በመዋዕለ ስብከቱ እየተመላለሰ ሲያስተምራቸውም ምንም ፍሬ አላፈሩምና “ይህችን ዕፀ በለስ ቁረጣት” አለው፡፡ መጋቤ ሐዲስ ቅዱስ ገብርኤል ግን “ተራድቼ ሥራ እስካሠራቸው ድረስ ይቅር በላቸው፡፡” ብሎ ለመነ የጌታን ትምህርት ያልተቀበሉ አይሁድ ግን የንስሐን ፍሬ ለማፍራት በጄ የሚሉ አልሆኑም፡፡ በአንደበታቸው የአብርሃም ልጆች ነን ይላሉ፤ ነገር ግን የአብርሃምን ሥራ ሊሠሩ አልቻሉም፡፡ “ይህ ሕዝብ በከንፈሩ ያከብረኛል ልቡ ግን ከእኔ የራቀ ነው” እንዲል፡፡

ስለዚህ ጌታ ከዕፀ በለሷ ዛፍ ምንም የሚበላ ፍሬ ስላላገኘ ረገማት፡፡ አንድም ጌታችን የፈለገውን ባለማግኘቱ ጉባኤ አይሁድን ረገመ፡፡ “በአንጻረ በለስ ረገማ ለኃጢአት” እንዲል፡፡ ሊቁ ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ ስለዚህ ጉዳይ እስራኤል ከበረከት ይልቅ እርግማን እንዳገኛቸው አሕዛብ ደግሞ የእግዚአብሔርን ጸጋ እንዳገኙ ሲገልጽ “አሕዛብ በእግዚአብሔር ቸርነት አበባ ሰበሰቡ፤ በአይሁድ ዘንድ ግን እሾህ ተረፈ፡፡ ይኸውም የሃይማኖት ጉድለት ነው፡፡” ብሏል፡፡

ዛሬም ገበሬ ዘርን ዘርቶ አርሞና ኮትኩቶ ከአሳደገ በኋላ የድካሙን ፍሬ እንደሚጠብቅ ሁሉ፤ እግዚአብሔር አምላካችንም በድንቅ መግቦቱ ከአሳደገን ልጆቹ የምግባርና የሃይማኖት ፍሬን ይፈልግብናል፡፡ ግን ጌታ ወደ በለስ ሕይወታችን ቢመጣ ምን ያገኝ ይሆን? ፍሬ ወይስ ቅጠል? የእግዚአብሔር ቃል ግን ለንስሐ የሚገባውን ፍሬ እንድናፈራ ያዘናልና መንፈሳዊ ሕይወታችን እንዳይደክም፣ እንዳይጠወልግ፣ እንዳይደርቅና አላስፈላጊ ሆኖ ሲገኝ ደግሞ ወደ እሳት እንዳይጣል የንስሐን ፍሬ ልናፈራ ይገባናል፡፡ ሕይወት ያለ ንስሓ ክንፍ እንደሌላት ወፍ ናትና፡፡

በንስሓ ወደ እግዚአብሔር የሚመለሱ ሰዎች ግን ይቅርታን /ምሕረትን/ ያገኛሉ፡፡ እግዚአብሔር የሚመለከተው ያለፈ ማንነታችንን ሳይሆን የዛሬውንና የወደፊቱን ሕይወታችንን ነውና፡፡ ቅዱስ ያሬድ “ኢተዘኪሮ አበሳ ዚአነ ኢኃደገነ ፍጹመ ንማስን ኄር እግዚአብሔር ኃጢአታችንን በማሰብ እንጠፋ ዘንድ ከቶ አልተወንም ቸር አምላክ ነውና” እንዲል፡፡ አዎ! እኛ በንስሓ ከተመለስን አምላካችን በኃጢአታችን ላይ አያስኬደንም፤ እርሱ የኃጢአታችንን አድራሻ ክረምት በፈለቀው ባሕር ውስጥ ይጥለዋልና፡፡ ሚክ.7÷18፡፡

እኛ ሰዎች ልብ ካልን በአዲሱ የዘመን መለወጫ ከተፈጥሮ እንኳ ብዙ ነገር መማር እንችላለን፡፡ አዝርእት፣ እፅዋት፣ ታድሰው፣ ቅጠላቸው ለምልሞ በአበባ ተንቆጥቁጠው እናያለን፡፡ ጋራ ሸንተረሩ አረንጓዴ ለብሶ፣ አፍላጋት በየቦታው እየተንፎለፎሉ፤ አዕዋፍ በዝማሬ፣ እንስሳት በቡረቃ ሰማይ ምድሩን ልዩ ያደርጉታል፡፡ ታዲያ ግዑዛኑ ፍጥረታት ጽጌ መዓዛቸውን የአዲስ ዓመት መሥዋዕት አድርገው ሲያቀርቡ እኛስ ምን ይዘናል?

ሰው ሠራሽ ሆኖ መዓዛ የሌለውን፣ ፍሬ የማያፈራውንና አበባ መሰሉን ሳይሆን፣ እግዚአብሔር የፈጠረውን፣ ያለመለመውንና አብቦ መልካም መዓዛ የሚሰጠውን የተፈጥሮ አበባን እንሁን፡፡ ያን ጊዜ ዝንቦች ሳይሆኑ ንቦች ማርን ለማዘጋጀት ይቀስሙናል፡፡ ስለዚህ በሃይማኖት ብቻ ያይደለ በምግባርም እናብብ፡፡ ያን ጊዜ ከዘማሪው ክቡር ዳዊት ጋር “በቸርነትህ ዓመታትን ታቀዳጃለህ ምድረ በዳውም ስብን ይጠግባል የምድረ በዳ ተራራሮችም ይረካሉ” ብለን ለመዘመር እንበቃለን፡፡ መዝ.64÷11-13፡፡

በአጠቃላይ አዲስ ዘመን የአምላክ ስጦታ /በረከት/ ነው፡፡ ስለዚህ በምድር ላይ የሚኖር ማንኛውም ሰው ዘመኑ በፈጣሪ ምልጣን የተያዘና የተገደበ ነው፡፡ ቅዱስ ዳዊት “አቤቱ እኛ አፈር እንደሆንን አስብ፤ ሰው ዘመኑ እንደ ሣር ነው፡፡ እንደ ዱር አበባም ያብባል ነፋስ በነፈሰበት ጊዜ ግን ያልፋል” በማለት ሰው ካደገ በኋላ በሕመም ፀሐይነት ይደርቅና በሞት ነፋስነት ይወለዳል፡፡ ባለፈው ዓመት ብዙዎች ወደሞት መንደር ደርሰዋል፤ እኛም እንደነርሱ መንገደኞች መሆናችንን እንርሳ፡፡

ባለቅኔው፡-
“በሉ እናንተም ሒዱ የእኛም ወደዚያው ነው ወትሮም መንገደኛ ፊትና ኋላ ነው” እንዲል፡፡

ነቢየ እግዚአብሔር ኢሳይያስም በበኩሉ “ሣሩ ይደርቃል፤ አበባውም ይረግፋል፤ የአምላካችን የእግዚአብሔር ቃል ግን ለዘለዓለም ጸንቶ ይኖራል” በማለት የሰው ሁሉ ክብሩ ሥጋዊ ሕይወቱና ተድላ ደስታው አንድ ጊዜ፣ አንድ ወቅት ለምልሞና አምሮ የሚታይ ሆኖ ሳለ ያው ደግሞ ሳይቆይ የሚጠፋ መሆኑን ያመለክታል፡፡ ኢሳ.40÷8፡፡ ስለዚህ በአዲሱ ዘመን ራሳቸውን ለከፍተኛ ግብ የሚያዘጋጁ ሁሉ ወደ ተቀደሰ መንፈሳዊ ሕይወት ሊሸጋገሩ ይገባል፡፡ ከእግዚአብሔር የተሰጠን እድሜም የአጭር ጊዜ እንግዳ መሆናችንን ስለሚያስገነዝበን የምንሸኘውም እንዲሁ ባልታወቀ ጊዜ ውስጥ መሆኑን በመረዳት እውነተኛ ሃሳባችንና ሥራችንን ለተተኪው ትውልድ የማይረሳ አስመስጋኝ ቅርስ መሆን አለበት፡፡

እንዲህ ዓይነቱ መልካምነት ደግሞ ለክርስቲያን በአዲሱ ዘመን እንደሎተሪ ዕጣ የሚደርሰው ሳይሆን ራሱ ፈልጐ የሚሆነው ነው፡፡ ስለዚህ ይልቁንም በአሁኑ ዘመን በመጽሐፍ ቅዱስ የተጻፈው ሁሉ ፍጻሜ እያገኘ ባለበት ዘመን ፍቅር በጠፋበት ዘመን አብዛኛው ሕዝብ ለማይረባ ነገር ብሎ ደገኛ ሃይማኖቱን እየለቀቀ ወደ አልባሌ ቦታ ሲገባ የሕይወት ለውጥ ማምጣት ያስፈልጋል፡፡ እኛ በአዲሱ ዓመት የሕይወት ለውጥን ካሳየን የእግዚአብሔር ጸጋ በውስጣችን ሥራውን በመጀመር በአንድ ሰንሰለት ላይ በርካታ የሕይወት ለውጥን ያመጣልናል፡፡ ይህ የሕይወት ለውጥ በአዲሱ ዘመን ውስጥ ለመኖሩ ተግባራዊ መለኪያው ደግሞ ቀጣይነቱ፣ ፍጹም ተጋድሎውና ግልጽ መሆኑ ነውና ራሳችንን እንመርምር፡፡ 1ጢሞ.4÷7፡፡

ባለቅኔው፡-

“አዲስ ሰው ስትሆን ጽድቅን ሳታፈራ እንዲያው እንደታጠርክ በክፋት ወጋግራ አሮጌውን ሳትጥል አዲስ መደረቱ የዘመን ቅበላ ይቅር ምናባቱ!” እንዲል፡፡

የዚያች የወይን ጠባቂ “ወደፊት ብታፈራ ደህና ነው ያለበለዚያ ግን ትቆርጣታለህ” እንዳለ ለነፍሳችን አንድ ነገር ሳንይዝ፣ ዘመናችን እንዳያረጅና እንዳይቆረጥ ዛሬ ለበጐ ሥራ እነነሣ፡፡ መጥመቀ መለኮት ቅዱስ ዮሐንስ አሁንም “ምሳር በዛፎች ሥር ተቀምጧል፤ እንግዲህ መልካም ፍሬ የማያደርግ ዛፍ ሁሉ ይቆረጣል፤ ወደ እሳትም ይጣላል” ይላልና፡፡ ማቴ.3÷10 እነሆ ! ዛሬ ግን እንደ እግዚአብሔር ቸርነት አሮጌውን ዓመት አሳልፈን ለአዲሱ ዓመት በቅተናል፡፡ ስለዚህ አዲሱን ዓመት በመንፈሳዊ ሕይወታችን ጐልምሰን፣ ሁላችንም ለተቀደሰ ዓላማ ተሰልፈን፣ ከክፉ ምግባራችንም ተመልሰን የምንቀደስበት የምንባረክበት የሰላም፣ የጤናና የደስታ ዘመን ያድርግልን አሜን!!

Emebetachin-Eriget

«ሞትሰ ለመዋቲ ይደሉ ሞታ ለማርያም የዐጽብ ለኲሉ»

መ/ር ሳሙኤል ተስፋዬ

ነሐሴ 15/2003 ዓ.ም

Emebetachin-Erigetፆመ ፍልሰታ የእመቤታችን ዕረፍት፣ ትንሣኤና ዕርገቷ የሚታሰብበት ወቅት ነው፡፡ በዚህ ወቅት ምእመናንን ከአካባቢያቸው ራቅ ብለው በተለያዩ ገዳማትና አድባራት በመሄድ አሊያም በአጥቢያቸው በመሰባሰብ እመቤታችን ለሐዋርያት በተለያዩ ጊዜያት ተገልጻ ሞትና ትንሣኤዋን የገለጸችበትን ሁኔታ ያስባሉ፡፡ ጌታም እናቱን መንበር አድርጎ ቀድሶ ማቁረቡን ይዘክራሉ በዚህ ወቅት በፆም በጸሎት ተወስነው የልጇን ቸርነት የድንግልን አማላጅነት ይማጸናሉ፡፡ ሁሉም እንደሚደረግላቸው ያምናሉ፡፡ የሱባኤው ወቅት ሲፈጸም «በእውነት ተነሥታለች» ብለው በደስታ የፆሙን ወቅት ይፈጽማሉ፡፡

 

 

ሞትና ትንሣኤዋ እንዴት ነው ቢሉ፡-
የእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያምን ሞትና ትንሣኤ ነገረ ማርያም፣ ስንክሳር እና ተኣምረ ማርያም እንደሚያስረዱት፤ ጥር 21 ቀን ዐርፋለች፡፡ ሞቷ የሚያስደንቅ መሆኑን ታላቁ የቤተክርስቲያናችን አባት ቅዱስ ያሬድ  «ሞትሰ ለመዋቲ ይደሉ ሞታ ለማርያም የሐጽብ ለኲሉ፤ ሞት ለማናቸውም ሰው ሁሉ የተገባ ነው የማርያም ሞት ግን ሁሉን ያስደንቃል» በማለት ገልጾታል፡፡

ቅዱሳን ሐዋርያት የእመቤታችንን የከበረ ሥጋዋን ገንዘውና ከፍነው ለማሳረፍ ወደ ጌቴሴማኒ መካነ ዕረፍት (የመቃብር ቦታ) ይዘው ሲሄዱ አይሁድ በቅንአት መንፈስ ተነሣሥተው «ቀድሞ ልጇን በሦስተኛው ቀን ከሙታን ተነሣ፤ በዐርባኛው ቀን ወደ ሰማይ ዐረገ እንደገናም ተመልሶ ይህን ዓለም ለማሳለፍ ይመጣል  እያሉ ሲያውኩን ይኖራሉ፡፡ አሁን ደግሞ እርሷንም እንደ ልጇ ተነሣች፣ ዐረገች እያሉ ሲያውኩን ሊኖሩ አይደለምን) ኑ ተሰብሰቡና ሥጋዋን በእሳት እናቃጥላት» ብለው ተማክረው መጡ፡፡

ታውፋንያ የሚባል አይሁዳዊ የከበረ ሥጋዋን የተሸከሙበትን አጎበር (የአልጋ ሸንኮር) በድፍረት ያዘ፡፡ የእግዚአብሔር መልአክ በእሳት ሰይፍ ሁለት እጆቹን ቆረጣቸው፡፡ እጆቹ ተንጠልጥለው ከቆዩ በኋላ በእውነት የአምላክ እናት ናት በማለት ስለ አመነ እጆቹ ተመልሰው እንደነበሩ ሆነውለታል፡፡ ከዚህ በኋላ መልአከ እግዚአብሔር የእመቤታችንን የከበረ ሥጋ  ከሐዋርያው ዮሐንስ ጋር ነጥቆ ወስዶ በገነት ከዕፀ ሕይወት ሥር አስቀመጠው፡፡ ቅዱስ ዮሐንስም ከጥቂት ጊዜ በኋላ ወደ ሐዋርያት ሲመጣ የእመቤታችንን የከበረ ሥጋ በገነት መኖሩን ነገራቸው፡፡  ሐዋርያትም የእመቤታችንን የከበረ ሥጋ አግኝተው  ለመቅበር በነበራቸው ምኞትና ጉጉት  ዮሐንስ አይቶ እኛ እንዴት ሳናይ እንቀራለን ብንጠየቅስ ምን እንመልሳለን በማለት በነሐሴ አንድ ቀን ሱባኤ ጀምረው ሲጾሙና ሲጸልዩ ከሰነበቱ በኋላ በ14 (በሁለተኛው ሱባኤ መጨረሻ) ጌታችን የእመቤታችንን ትኩስ የከበረ ሥጋ አምጥቶ ስለሰጣቸው በታላቅ ዝማሬ፣ በውዳሴ ወስደው ቀድሞ በተዘጋጀው መካነ ዕረፍት  በጌቴሴማኒ ቀበሯት፡፡

የእመቤታችን የቀብር ሥነ ሥርዐት በተፈጸመ ጊዜ ከ12ቱ ሐዋርያት አንዱ የሆነው ቅዱስ ቶማስ አልነበረም፡፡ ከሀገረ ስብከቱ በደመና ተጭኖ ወደ ኢየሩሳሌም ሲመጣ፣ እመቤታችን በተቀበረች በሦስተኛው ቀን  እንደ ልጇ ትንሣኤ ተነሥታ ስታርግ ያገኛታል፡፡ ቀድሞ የልጅሽን አሁን ደግሞ የአንቺን ትንሣኤ ሳላይ ቀረሁ ብሎ ቢያዝን እመቤታችን ከእርሱ በቀር ሌሎች ሐዋርያት ትንሣኤዋን እንዳላዩ ነግራው ቅዱስ ቶማስን አጽናናችው፡፡ ሄዶም ለሐዋርያት የሆነውን ሁሉ እንዲነግራቸው አዝዛው ለምልክት ይሆነው ዘንድ የተገነዘችበትን ሰበኗን ሰጥታው ወደ ሰማይ ዐርጋለች፡፡

ልበ አምላክ ቅዱስ ዳዊት የእመቤታችን ትንሣኤ አስቀድሞ በትንቢት መስታወትነት ታይቶት «ተንሥእ እግዚኦ ውስተ ዕረፍትከ አንተ ወታቦተ መቅድስከ፤ አቤቱ ወደ ዕረፍትህ ተነሥ አንተና የመቅደስህ ታቦት» (መዝ.131፥8)፡፡  ነቢዩ ዳዊት ይህን ቃለ ትንቢት  አስቀድሞ ክርስቶስ እንደሚነሣ ከገለጸ በኋላ ቀጥሎ የመቅደሱ ታቦት እናቱ ቅድስት ድንግል ማርያም እንደምትነሣ ይናገራል (ማቴ5፥35፤ ገላ 4፥ 26፤ ዕብ 12፥22፤ ራዕ 3፥12)፡፡

ወደ ቀደመ ነገራችን እንመለስና ቅዱስ ቶማስም ሐዋርያት ወደ አሉበት ኢየሩሳሌም በደረሰ ጊዜ «የእመቤታችን ነገር እነዴት ሆነ?»  ብሎ ቢጠይቃቸው፤ «እመቤታችንን እኮ ቀበርናት» ብለው ነገሩት፡፡ እርሱም ዐውቆ ምስጢሩን ደብቆ «አይደረግም ሞት በጥር በነሐሴ መቃብር  እንደምን ይሆናል?» አላቸው፡፡ ቅዱስ ጴጥሮስ አንተ መጠራጠር ልማድህ ነው፡፡ ቀድሞ የጌታን ትንሣኤ ተጠራጠርክ አሁንም አታምንም ብሎ  የእመቤታችን መካነ መቃብር ሊያሳዩት ይዘውት ሔዱ፡፡ መቃብሩን ቢከፍቱ የእመቤታችንን የከበረ ሥጋ አጡት፤ ደነገጡም፡፡ በዚህ ጊዜ ቅዱስ ቶማስ «አታምኑኝም ብዬ ነው እንጂ እመቤታችንስ ተነሥታ ዐርጋለች» ብሎ  የሆነውን ሁሉ ተረከላቸው፡፡ ከዚያም ምልክት እንዲሆን የሰጠችውን ሰበኗን አሳያቸው፡፡ እነርሱም ማረጓን አምነው ሰበኗን ለበረከት ከተከፋፈሉ በኋላ ወደየአህጉረ ስብከታቸው ሄዱ፡፡ በየሀገረ ስበከታቸውም ሕሙማንን ሲፈውሱበትና ገቢረ ተአምር ሲያደርጉበት ኖረዋል፡፡

በዓመቱ ትንሣኤሽን ቶማስ አይቶ እንዴት ይቅርብን ብለው ነሐሴ አንድ ቀን ጀምሮ ሱባኤ ገቡ፡፡ በሱባኤው መጨረሻ ነሐሴ 16 ቀን ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የለመኑትን ልመና ተቀብሎ እመቤታችንን መንበር፣ ቅዱስ ጴጥሮስን ንፍቀ (ረዳት) ቄስ)፣ ቅዱስ እስጢፋኖስን ገባሬ ሰናይ (ዋና) ዲያቆን አድርጎ ቀድሶ አቁርቦአቸዋል፡፡ ከዚህ በኋላ እመቤታችንን ሐዋርያት በግልጽ ትንሣኤዋን ዕርገቷን እያዩዋት ከጌታችን ጋር በክብር በይባቤና በመዝሙር ወደ ሰማይ ዐርጋለች፡፡ ቅዱስ ያሬድ በመዝሙሩ «እመቤታችን ድንግል ማርያም ከምድር ወደ ሰማይ ዐረገች በሰማይም ከልጇ ጋር በአብና በመንፈስ ቅዱስ ቀኝ ተቀመጠች»፡፡

የእመቤታችን ትንሣኤ፣ ዕርገት ልዩ የሆነበት ምስጢር
በመጽሐፍ ቅዱስ ትምህርት መሠረት ትንሣኤ ጊዜያዊና ዘለዓለማዊ በመባል ይታወቃል፡፡ ጊዜያዊ ትንሣኤ የሚባለው የእግዚአብሔር ከሃሊነት የሚገለጽበት ተኣምራዊ ሥራ ሆኖ በተወሰኑ ሰዎች ላይ ይፈጸምና ዳግም ሞትን የሚያስከትል ነው፡፡ ለምሳሌ ኤልያስ ያስነሣውን ወልደ መበለት (1ኛ ነገ 17፥8-24) ዐጽመ ኤልሳዕ  ያስነሣውን ሰው (2ኛነገ 13፥20፦21) ትንሣኤ ወለተ ኢያኢሮስን (ማቴ 9፥ 8-26) በዕለተ ስቅለት ከመቃብር ወጥተው በቅድስት ከተማ የታዩ ሙታን (ማቴ 27፥52-53) በቅዱስ ጴጥሮስ ጸሎትና ምልጃ የተነሣች ጣቢታን (ሐዋ ሥ 9፥36-41) እንዲሁም ትንሣኤ አልዓዛርን መጥቀስ ይቻላል፡፡

አልዓዛር ከሞተ በኋላ በአራት ቀን እንደተነሣ ወንጌላዊው ቅዱስ ዮሐንስ ጽፏል፡፡ «በታላቅ ድምፅ አልዓዛር ሆይ ወደ ውጭ ና ብሎ ጮኸ፡፡ የሞተውም እጆቹና እግሮቹ  በመግነዝ እንደተገነዙ ወጣ፤ ፊቱም በጨርቅ እንደተጠመጠመ ነበር፡፡ ኢየሱስም ፍቱትና ይሂድ ተውት አላቸው(ዮሐ 11፥43-44)፡፡  ኢየሱስ ክርስቶስ ሲያነሣውም ለማየት በመቃብሩ ዙሪያ የነበሩ አይሁድ ከሞተ በኋላ በአራት ቀን መነሣቱን ተመልክተው አደነቁ የአልዓዛር እኅቶችም  ተደሰቱ፡፡ አልዓዛር ግን ለጊዜው ቢነሣም ቆይቶ ተመልሶ ዐርፏል ወደፊት ትንሣኤ ዘጉባኤ ይጠብቀዋል፡፡

የቅድስት ድንግል ማርያም ትንሣኤ የክብርና የሕይወት ትንሣኤ ሲሆን ሁለተኛ ሞትን አያስከትልም ትንሣኤ ዘጉባኤንም አይጠብቅም፡፡ መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የትንሣኤያችን በኩር ሆኖ በሞተ በሦስተኛው  ቀን ተነሥቷል፡፡ እናቱ እመቤታችንም በልጇ ሥልጣን፤  እንደ ልጇ ትንሣኤ በሦስተኛው ቀን ተነሥታ ትንሣኤ ዘጉባኤን ሳትጠብቅ በክብር ዐርጋለች፡፡  እንደዚህ ያለውን ትንሣኤ ከእርሷ በቀር ሌሎች ቅዱሳን ወይም ነቢያትና ሐዋርያት አላገኙትም በዚህም ሁኔታ የቅድስት ድንግል ማርያም ትንሣኤ ከማናቸውም ትንሣኤ ልዩ ሆኖ እናገኘዋለን፡፡ ይህም ትንሣኤ ዘለዓለማዊ የሆነ ከዳግም ሞተ ሥጋ ነጻ የሆነ ትንሣኤ ነው፡፡

ስለ ቅድስት ድንግል ማርያም ከመቃብር መነሣት ነሐሴ 16 ቀን የሚነበበው መጽሐፈ ስንክሳር እንደሚያስረዳን አባቷ ዳዊት በገናውን እየደረደረ ጸሐፊው የነበረው ዕዝራም መሰንቆውን ይዞ ቅዱሳን መላእክት ነቢያትና ጻድቃን እያመሰገኗት በብሩህ ደመና ወደ ሰማይ ዐረገች ከዚያም በክብር ተቀመጠች፡፡ በዚያም ስፍራ ሁለተኛ ሞት ወይም ሐዘን ጩኸትና ስቃይ የለም የቀደመው ሥርዐት አልፎአልና (ራዕ 21፥4-5)፡፡

የእመቤታችን ዕርገትም በመጽሐፍ ቅዱስ ከተገለጸው ከእነ ሄኖክና ኤልያስ ዕርገት የተለየ ነው፡፡  ሄኖክ ወደ ሰማይ ያረገው በምድር ሳለ እግዚአብሔርን በእምነቱና በመልካም ሥራው ስለአስደስተና በሥራውም ቅዱስ ሆኖ ስለተገኘ ሞትን እንዳያይ ዐረገ፡፡ ወደፊት ገና ሞት ይጠብቀዋል ሞቶም ትንሣኤ ዘጉባኤ ያስፈልገዋል፡፡ «ሄኖክ ሞትን እንዳያይ በእምነት ተወሰደ እግዚአብሔርም ስለ ወሰደው አልተገኘም» (ዕብ 11፥5)፡፡

ነቢዩ ኤልያስም በእሳት ሠረገላ ተነጥቋል «እነሆ የእሳት ሠረገላና የእሳት ፈረሶች በመካከላቸው ገብተው ከፈሉአቸው፤ ኤልያስም በአውሎ ነፋስ ወደ ሰማይ ወጣ»  (2ኛ ነገ 2፥10)፡፡ ነቢዩ በእሳት ሠረገላም ቢነጠቅም ወደፊት ሞት ይጠብቀዋል፤ ትንሣኤ ዘጉባኤም ያስፈልገዋል፡፡

 

ኢትዮጵያዊው ሊቅ ቅዱስ ያሬድም በድርሰቱ ስለ ዕርገትዋ ጽፏል፡፡ በቃልዋ የታመነች በሥራዋም የተወደደች ቅድስት ድንግል ማርያምን መላእክት እያመሰገኗትና በመንፈሳዊ ደስታ እያጀቧት ወደ ሰማይ አሳረጓት ሲል በዘመረው መዝሙር አስረድቶናል፡፡
የእመቤታችን አማላጅነት የትንሣኤያችን በኲር የሆነው የአምላካችን ኢየሱስ ክርስቶስ ቸርነቱ ከሁላችን ጋር ይሁን አሜን፡፡

የተራራው ምስጢር/ማቴ 17፡1-9/

ዲያቆን ታደለ ፈንታው


ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በፊልጶስ ቂሣርያ መነ ይብልዎ ሰብእ ለወልደ እጓለ እመሕያው የሰው ልጅን ማን እንደሆነ ይሉታል ? የሚል ጥያቄን ለደቀ መዛሙርቱ አቀረበላቸው ፡፡ አንዳንዶች ከነቢያት አንዱ ነህ አሉት ፡፡ በሥምም እየጠቀሱ መጥምቁ ዮሐንስ : ኤልያስ : ኤርምያስ ነህ በማለት ግምታቸውን አስቀመጡ፡፡ ደቀመዛሙርቱ በቅዱስ መጽሐፍ እንደተነገረ ገና በእምነት አልጠነከሩም ነበርና ግምታቸው የተዘበራረቀ ነበረ፡፡

 

ከሐዋርያት አንዱ ሊቀ ሐዋርያት ቅዱስ ጴጥሮስ የእርሱ ተራ በደረሰ ጊዜ የሰጠው ምስክርነት ግን ድንቅ የሆነ ምስክርነት ነበር፡፡ «አንተ ክርስቶስ የሕያው እግዚአብሔር ልጅ ነህ»/ማቴ 16፡13/ የሚል፡፡ የዮና ልጅ ስምዖን በዚህ ምስክርነቱ ብፁዕ ነህ ተብሎ ተጠርቷል፡፡ ጌታችን እንዲህ አይነቱን ምስክርነት ሥጋና ደም አልገለጸልህም በሰማይ ያለው አባቴ እንጂ አለ ፡፡ በዘመናችን ብዙዎች የሥጋና ደም ሀሳብን ይዘው አምጻኤ አለማትነቱ፤ ከሃሊነቱ፤ ጌትነቱ፤ ተአምራቱ፤ መግቦቱ፤ ዓይን ነሥቶ ዓይን ለሌለው ዓይን ሰጥቶ መመገቡ አልታያቸው ብሎ አማላጅ ነህ ይሉታል፡፡ ያለባሕርይው ባሕርይ ሰጥተው በየመንደሩ፤ በየዳሱ አለ ብለው ይጠሩታል፤ እርሱ ግን «እነሆ ክርስቶስ በመንደር ወይም በእልፍኝ ውስጥ አለ ቢሏችሁ አትመኑ» አለ ፡፡ ከራሳቸው ልቡና አንቅተው ስለጌታችን የተሳሳተ መረዳት ያላቸው ሰውንም የሚያሳስቱ የሥጋና ደም ኃሳባቸውን ቀላቅለው ንፁህ የሆነውን የወንጌል ቃል የሚበርዙ ወገኖች ብፁዓን ናችሁ አልተባሉም ፡፡

 

ይህ ምስክርነት በተሰጠ ማለትም «በቂሣርያ የሰውን ልጅ ማን ይሉታል»ባላቸው በሰባተኛው ቀን ከደቀ መዛሙርቱ ሦስቱን ለብቻቸው ይዞአቸው ወደረጅምና ከፍ ወደአለ ተራራ ወጣ ፡፡ በከፍታው ላይ ያለ ልዑል እግዚአብሔር ረጅምና ከፍ ያለ ነገርን ይወዳል ፡፡ ንጉሡ ዖዝያን በሞተበት ዓመት ነቢየ እግዚአብሔር ኢሳይያስ እግዚአብሔርን የተመለከተው በረጅምና ከፍ ባለ ዙፋን ላይ ነበር»ጌታችን ሰው ሆኖ ሥጋን ሲዋኻድም ከፍጥረታት ሁሉ ከፍ ያለውን አማናዊ ዙፋን እርሱም የእመቤታችንን ማኅጸን ነበረ የመረጠው፡፡ ይኸንን ሁኔታ ሊቁ አባ ሕርያቆስ እንዲህ ብሎ በማድነቅ ይጠይቃል፡፡ «ድንግል ሆይ ሰባት የእሳት መጋረጃ ከሆድሽ በስተየት በኩል ተጋረደ በስተቀኝ ነውን? በስተግራ ነውን ? ታናሽ ሙሽራ ስትሆኝ፡፡ ለአባታችን ያዕቆብም የገለጸለት መሰላል ከምድር ከፍ ያለ መሰላል ነበረ፡፡ ምሳሌነቱን ከፍጥረታት ሁሉ ከፍ ላለች ለእመቤታችን ነው፡፡ የጌታችን ከፍ ያለ ነገር መዉደድ ምሳሌው ልዑለ ባሕርይ ነኝ ሲል ነው፡፡

 

ለምን በደብረ ታቦር ተራራ ላይ ተገለጠ ?


በመጀመሪያ ተራራ የመንግሥተ ሰማያት ምሳሌ ነው ፡፡ ተራራን በብዙ ድካም እንዲወጡት መንግሥተ ሰማያትንም በብዙ መከራ ያገኟታል ፡፡ ይህንን ሁኔታ ቅዱስ ጳውሎስ ሲገልጥ እስመ በብዙህ ጻዕር ወበጻማ ኃለወነ ንባኣ መንግሥተ እግዚአብሔር በብዙ ጭንቅ መከራ ወደ እግዚአብሔር መንግሥት እንገባ ዘንድ አለን በማለት አስረድቷል ፡፡ ተራራውን ሐዋያርት በሲኖዶስ ታቦር ብለው ጠርተውታል፡፡ ይህንን ሁኔታ ቅዱስ ጴጥሮስ ሲናገር «የእርሱን ግርማ አይተን እንጂ በብልሃት የተፈጠረውን ተረት ሳንከተል የጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስን ኃይልና መምጣት አስታወቅናችሁ ፡፡ ከገናናው ክብር በእርሱ ደስ የሚለኝ የምወደው ልጄ እርሱ ነው እርሱን ስሙት የሚል ያ ድምጽ በመጣለት ጊዜ ከእግዚአብሔር አብ ክብርንና ምስጋናን ተቀብሎአልና ፤ እኛም በቅዱሱ ተራራ ከእርሱ ጋር ሳለን ይህ ድምጽ ከሰማይ ሲወርድ ሰማን/1ኛ ጴጥ1፤16/ ብሏል ፡፡

 

ጌታችን ምስጢረ መለኮቱን በታቦር ያደረገው በሌላ ተራራ ያላደረገው አስቀድሞ ታቦር ትንቢት የተነገረበት ተራራ በመሆኑ ነው፡፡ ነቢዩ ዳዊት «ታቦር ወአርሞንዔም በስመ ዚአከ ይትፌስሑ» ብሎ ተናግሯል፡፡ የጌታችን ሰው መሆን የነቢያት ትንቢት ፍጻሜ ማግኘቱን ማሳያ ነው፡፡

 

አሥራ ሁለቱንም ደቀ መዛሙርት የመረጣቸው ጌታችን ነው ፡፡ በመጀመሪያ ሙሴን ለመስፍንነት አሮንን ለክህነት የመረጠበት ግብር እንዳልታወቀ ከደቀመዛሙርቱ ሦስቱን የመረጠበትን ምክንያት የሚያውቀው እርሱ ብቻ ነው ፡፡ እንደ ቤተ ክርስቲያናችን አስተምህሮ ግን ሦስቱን ወደ ተራራ ይዞአቸው ስምንቱን ከእግረ ተራራ ጥሎአቸው የሄደበት ምክንያት ስለነበራቸው ነው፡፡ የመጀመሪያው ከሌሎቹ የሚበልጡበት ምክንያት ነበራቸውና፡፡ ቅዱስ ጴጥሮስ ይወደው ነበርና ቅዱስ ዮሐንስ ጌታ ይወደው የነበረ ደቀ መዝሙር ተብሎ በብዙ ቦታ ተገልጧል፡፡ ቅዱስ ያዕቆብ አንተ የምትጠጣውን ጽዋ እኛም እንጠጣለን ብሏል/ማቴ20፤22/፡፡እንደገናም ቅዱስ ጴጥሮስ አንተ የሕያው እግዚአብሔር ልጅ ነህ ብሎ መስክሮ ሥለነበረ ምስክርነቱ በእርሱ ብቻ የሚቀር ሳይሆን እግዚአብሔር አብም በደመና ሆኖ የሰጠው ምስክርነት «በእርሱ ደስ የሚለኝ ልጀ እርሱ ነው እርሱን ስሙት» በማለት የተናገረው ከቅዱስ ጴጥሮስ ምስክርነት ጋር ያለው ድንቅ ስምምነት ይገለጥ ዘንድ ነው፡፡ በዚህም ቅዱስ ጴጥሮስ የሰጠው ምስክርነት ሥጋና ደም ያልገለጠለት መሆኑ በተረዳ ነገር ታውቋል ፡፡ እንደገናም ቅዱስ ዮሐንስንና ያዕቆብን ይዞአቸው ወደተራራ የወጣበት ምክንያት የዘብዴዎስ ልጆች እናት /እናታቸው/ ማርያም ባውፍልያ ጌታችን መንግሥቱ ከዚህ ዓለም መስሎአት ልጆቿን አስከትላ እየማለደች ሰገደችለት ፡፡ እንዲህም የሚል ልመናን ስለልጆችዋ አቀረበች፡፡

 

ወትቤሎ ረቢ ሊተ ከመ ይንበሩ እሉ ደቂቅየ አሐዱ በየማንከ ወአሐዱ በጸጋምከ በመንግሥትከ፡፡

በነገሥህ ጊዜ እኒህ ልጆቸ አንዱ በቀኘህ አንዱ በግራህ እንዲቀመጡ አድርግልኝ፡፡

ወአውሥአ እግዚእ ኢየሱስ ወይቤላ ኢተአምሩ ዘትስእሉ የምትለምኑትን አታውቁም አለ፡፡


ጌታችን መንግሥቱ ሰማያዊት እንጂ ምድራዊት አለመሆኑን ይገልጥላቸው ዘንድ ይዞአቸው ወደተራራ ወጣ፡፡ ስምንቱን ከእግረ ደብር ትቷቸው የወጣበት ምክንያት በይሁዳ ምክንያት ነው፡፡ ክብሩንና መንግሥቱን እንዳያይ ይሁዳ ትንቢት ተነግሮበታልና ለይቶም እንዳይተወው ከምሥጢረ መንግሥቱ ቢለየኝ ከሞቱ ገባሁበት ብሎ ምክንያት እንዳያገኝ ስምንቱን ጥሎአቸው ወጣ፡፡ ነገር ግን እግዚአብሔር ነቢዩ ሙሴን ከእስራኤል ሽማግሌዎች ሕዝቡን ያስተዳድሩ ዘንድ ሰባ ሰዎችን መርጦ ወደ ቅዱሱ ተራራ እንዲያቀርባቸውና ከመንፈሱ ወስዶ በሽማግሌዎቹ ላይ እንዲያፈስባቸውና ሙሴን እንዲያግዙት አዘዘው ፡፡ ከእያንዳንዱ ነገድ ስድስት ሰዎችን መረጠ ከአስራሁለቱ ነገድ የተመረጡት ሰባ ሁለት ሰዎች ሆኑ፤ እንደ እግዚአብሔር ቃል ሰባዎቹን ሰዎች ይዞ የቀሩትን ሁለቱን ኤልዳድንና ሞዳድን ከእግረ ደብር ትቷቸው ወደ ተራራው ወጣ፡፡ በደብረ ሲና ለሰባው ሊቃናት የተገለጠው ምስጢር ከተራራው ሥር ለነበሩ ሁለቱ ሰዎችም ተገልጧል፡፡ በተመሳሳይ ሁኔታ በርእሰ ደብር ለሦስቱ ደቀ መዛሙርት የተገለጠው ምስጢር በእግረ ደብር ላሉ ለስምንቱም ተገልጧል ፡፡

 

ሙሴና ኤልያስ


ሙሴና ኤልያስ በቅዱሱ ተራራ ከጌታችን ጋር የተነጋገሩ ነቢያት ነበሩ ፡፡ በቅዱሱ ተራራ በተከበበ ብርሃን ውስጥ ሆነው ስማቸውን የጠቀስናቸውን ነቢያትን እንመለከታለን ፡፡ እነዚህ ፆም የሚያስገኘውን ጥቅም ያሳዩ ናቸው አርባ አርባ ቀናትን ጾመዋል ፡፡ በቅዱሱም ተራራ ከተገኙት ቅዱሳን መካከል ናቸው ፡፡ እነዚህ ለመገኘታቸው ምክንያት ነበራቸው ፡፡ ጌታችን አስቀድሞ እውነት እውነት እላችኋለሁ ኃለው እምእለ ይቀዉሙ ዝየ እለ ኢይጥዕምዎ ለሞት እስከ ይሬእይዎ ለመንግሥተ እግዚአብሔር ከዚህ ቁመው ካሉት የእግዚአብሔርን መንግሥት እስኪያዩ ድረስ የማይሞቱ አሉ ብሎ ተናግሮ ነበርና ነቢዩ ኤልያስን፥ ሙሴ እባክህ ክብርህን አሳየኝ ብሎ ለምኖ ነበርና ፊቴን ማየት አይቻልህም ነገር ግን ክብሬን በዓለቱ ላይ እተውልሃለሁ ብሎ ተናግሮት ስለነበረ እግዚአብሔር የተናገረው ቃል ከሞት በኋላ እንኳን ተፈጻሚነቱ የማያጠያይቅ መሆኑ ይታወቅ ዘንድ ሙሴም በቅዱሱ ተራራ ላይ ተገኘ፡፡ እንደገናም ጌታችን ስለማንነቱ ሲጠየቅ ሙሴ ነህ ኤልያስ ነህ ብለውት ስለነበረ እርሱ አምላከ ሙሴና አምላከ ኤልያስ መሆኑ ይታወቅ ዘንድ ከነቢያት ሁለቱ ተገኙ፡፡ እንደገናም ሙሴ የሕጋውያን ኤልያስ የደናግል ምሳሌ ነው፤ ወደ እግዚአብሔር መንግሥት የተጠሩት ሁለቱም ወገኖች ናቸውና ፡፡

 

ስለምን ግርማ መለኮቱን ገለጠ ?


ጸሐፍት ፈሪሳውያን የሕጉ ባለቤት ሠራዔ ሕግ እርሱ መሆኑን ባለመገንዘባቸው በተደጋጋሚ ሕጉን ጥሷል በማለት ይከሱት ነበረ ፡፡አይሁድ ይህ ሰው ከእግዚአብሔር አይደለም ፤ ከእርሱስ ቢሆን ሰንበትን አይሽርም ነበር ብለዋልና ከእግዚአብሔር ዘንድ እንደወጣ የሰንበትም ጌታዋ መሆኑ ይታወቅ ዘንድ ክብሩን መግለጥ ነበረበት፡፡ እንደገናም ቃሌን የሚጠብቅ ቢኖር ለዘላለም ሞትን አይቀምስም በማለት ሲያስተምራቸው በውኑ አንተ ከሞተው ከአባታችን ከአብርሐም ትበልጣለህን ? በማለት ጠየቁት ፡፤ እውነት እውነት እላችኋለሁ አብርሃም ሳይወለድ እኔ አለሁ ብሎአቸው ነበርና ክብሩን መግለጥ ነበረበት ፡፡ በሕይወት ካሉት ኤልያስን ከሞቱት ሙሴን የማምጣቱ ምስጢር በሞትና በሕይወት ላይ ስልጣን ያለኝ እኔ ነኝ ሲል ነው፡፡ ሙሴን ከመቃብር ኤልያስን ከብሔረ ሕያውያን ማምጣቱ የሰማይና የምድር ገዢ እኔ ነኝ ሲል ነው፡፡ እንደገናም በሐዋርያቱ የተሰጠውን ምስክርነት በባሕርይ አባቱ በአብ ለማስመስከር ነው፡፡ አስቀድሞ «የሁለት ወገኖች ምስክርነት እውነት እንደሆነ ተጽፏል ስለእራሴ የምመሰክር እኔ ነኝ አብ ስለእኔ ይመሰክራል /ዮሐ.8፥17/ ብሎአቸው ነበርና ነው ፡፡

 

በቅዱሱ ተራራ ላይ


ከሐዋርያት ሦስቱ ከነቢያት ሁለቱ በተገኙበት ልብሱ እሳት ክዳኑ እሳት የሆነ እግዚአብሔር ወልድ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በፊታቸው ተለወጠ፡፡ አካሉ ሙሉ ብርሃን ሆነ፡፡ ጽጌያት ከአዕጹቃቸው እንዲፈነዱ፥ፊቱም እንደ ፀሐይ ብሩህ ሆነ፡፡ ልብሱም እንደበረድ ነጭ ሆነ፤ ክብሩን ግርማውን ጌትነቱን ገለጠ፡፡ ሙሴና ኤልያስ ከእርሱ ጋር ሲነጋገሩ ተሰሙ፡፡ ከደመናውም ውስጥ «ዝንቱ ውእቱ ወልድ ዘአፈቅር ዘቦቱ ሠመርኩ፤ ልመለክበት የወደድሁት ለተዋሕዶ የመረጥሁት ልጄ ይህ ነው፡፡ ወሎቱ ስምዕዎ እርሱን ስሙት የሚል አስፈሪ ድምጽ መጣ፡፡ ቅዱስ ጴጥሮስ ከዚህ መኖር ለእኛ መልካም ነው አለው አንተ የአምላክነት ሥራህን እየሠራህ ብንራብ እያበላኸን፣ ብንታመም እየፈወስከን፣ ብንሞት እያነሣኸን፤ ሙሴ የወትሮ ሥራውን እየሠራ፣ ደመና እየጋረደ፣ መና እያወረደ፣ ባሕር እየከፈለ፣ ጠላት እየገደለ፡፡ ኤልያስ የወትሮ ሥራውን እየሠራ፣ ሰማይ እየለጎመ፣ እሳትን እያዘነመ፣ ዝናም እያቆመ፣ በዚህ መኖር ለእኛ መልካም ነው፡፡ ወእመሰ ትፈቅድ ንግበር በዝየ ሠለስተ ማኅደረ ከዚህ ሦስት አዳራሽ እንሥራ፤ አሐደ ለከ አንዱን ለአንተ፤ ወአሐደ ለሙሴ አንዱን ለሙሴ፤ ወአሐደ ለኤልያስ አንዱን ለኤልያስ አለ፡፡ ይህንን ገና እየተናገረ እንዳለ ብሩህ ደመና መጥቶ ጋረዳቸው፡፡ አብ የሠጠው ምስክርነት ተሰማ፡፡ እመቤታችን በገሊላ ቃና እርሱን ስሙት /ዮሐ. 2፡5/ በማለት ስለ ልጅዋ የሰጠቸው ምስክርነት ይኸው ነበረ፡፡ የተዓምረ ማርያም ደራሲ የእመቤታችን ሀሳብ እንደ እግዚአብሔር ሀሳብ ነው የሚለው መንፈስ ቅዱስ የሚያናግረውን እንዲህ ዓይነቱን ታላቅ ሀሳብና ምስክርነት ነው ፡፡

 

ከዚህ ትምህርት የምንማረው ምንድር ነው ?


አስተምህሮአችን መሠረቱን በነቢያትና ሐዋርያት ላይ ያደረገ መሆኑን በቅዱሱ ተራራ ላይ የተገኙት ነቢያትና ሐዋርያት ምስክሮች ናቸው፡፡ እኛም በነቢያትና ሐዋያርት መሠረት ላይ ታንጻችኋል ተባለልን፡፡ ስለጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ማንነት የታመነ ምስክርነት አግኘተናል፡፡ አስቀድሞ ሐዋርያው «በመጀመሪያ ቃል ነበረ ቃልም በእግዚአብሔር ዘንድ ነበረ ቃልም እግዚአብሔር ነበረ/ዮሐ1፡1/ በማለት የሰጠንን ምስክርነት እንደገናም ጸጋንና እውነትን ተመልቶ በእኛ ላይ አደረ በማለት ያመጣውን ቅድመ ዓለም ከአብ ያለእናት በዚህ ዓለም ቅድስት ከምትሆን ከእመቤታችን ከድንግል ማርያም ያለአባት የተወለደውን አምላክ ወልደ አምላክ በማመን የወንጌል ጋሻን ደፍተን የእምነት ወንጌልን ተጫምተን በማመን እንበረታለን እንጂ ባለማመን ምክንያት አንጠፋም፡፡ ክርስቲያኖች ምስጢረ መለኮቱን የገለጠበትን ከጌታችን ዓበይት በዓላት አንዱ የሆነውን የደብረ ታቦርን በዐል የምናከብረው በዚህ መንፈስ ነው ፡፡

 

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ጠብቃ ለትውልድ ካስተላለፈችው ታላላቅ መንፈሳውያት እሴቶች መካከል በጌታችን  በእመቤታችንና በቅዱሳኑ ሥም በዓላትን ማክበር ነው ፡፡ ከእነዚህም በዓላት መካከል አንዱ የደብረ ታቦር በዐል ነው፡፡ በዓሉም በተለየ መልኩ ይከበራል፤ ዳቦ በመድፋት፤ ጠላ በመጥመቅ፤ በተለይም የአብነት ተማሪዎች ከሕዝቡ በመለመን ስሙን ይጠራሉ፡፡ ይህ ልንጠብቀው የሚገባን መንፈሳዊ እሴታችን ነው፡፡ ጌታችን የቅዱሳኑን መታሠቢያ በተመለከተ ሲናገር በደቀ መዝሙር ሥም ቀዝቃዛ ዉኃ ብቻ ያጠጣ ዋጋው አይጠፋበትም እንዳለ /ማቴ.10፥42/ በባለቤቱ ሥም የሚደረገውማ እንደምን አብዝቶ ዋጋ አያሰጥ፡፡ ለሚወዱኝ እስከሺህ ትውልድ ድረስ ምሕረትን የማደርግ እኔ እግዚአብሔር ነኝ /ዘጸ.21፥6/ ስላለ በዓሉን በማክበር የበረከቱ ተሳታፊ መሆን ይገባል::

ወስብሃት ለእግዚአብሔር
Normal 0 false false false EN-US X-NONE X-NONE MicrosoftInternetExplorer4

Normal 0 false false false EN-US X-NONE X-NONE MicrosoftInternetExplorer4

mariam[1].gif

አስደናቂው ሞት

ዲ/ን ታደለ ፋንታው
ነሐሴ 1/ 2003 ዓ.ም.

ክብረ ድንግል ማርያም

እግዚአብሔር ዘላለማዊ ኃይሉንና አምላክነቱን ለዓለም ከገለጸበት ታላቅ ሥራ መካከል በእመቤታችን በቅድስት ድንግል mariam[1].gifማርያም የገለጸው ድንቅ ሥራው በቤተ ክርስቲያን ታሪክ ቀዳሚውን ሥፍራ ይይዛል፡፡ ይህንን ሁኔታ ድንግል ማርያም “ብርቱ የሆነ እርሱ ታላቅ ሥራን በእኔ አድርጓል ስለዚህም ምክንያት ፍጥረት ሁሉ ያመሰግኑኛል” ሉቃ.፩፥፵፱/1፥9/ በማለት ገለጸችው፡፡ ቅድሰት ኤልሳቤጥም የጌታዬ እናት” አለቻት /ሉቃ.፩፥፵፫/1፥43/ “መልአኩ ቅዲስ ገብርኤል ከሴቶች መካከል ተለይተሽ የተባረክሽ ነሽ” /ሉቃ.፩፥፳፰/1፥28/ አላት፡፡ ቅዱስ ዳዊት ልጄ ይላታል መዝ.፵፬፥፱/44፥9/ ሰሎሞን እኅቴ ይላታል /መኃ.፭፥፩/5፥1/ ወንጌላዊው ቅዱስ ዮሐንስም እናት ሆና ተሰጠችው /ዮሐ.፲፱፥፳፮/19፥26/ ይህንን ድንቅ ሥራ ውስንና ደካማ የሆነ አእምሮ ሊገነዘበው ከሚችለው በላይ ነው፡፡

ቅዱስ አግናጢዎስ ዘአንጾኪያ ለኤፌሶን ክርስቲያኖች በጻፈው መልእክቱ እንደገለጸው” የቅድስት ማርያም ዘለዓለማዊ ድንግልና፤ አማኑኤልን መውለዷ፤ የማይሞተው ጌታ ሞት” እነዚህ ሦስቱ ከዚህ ዓለም ጥበበኞችና ገዢዎች የተሰወሩ ምሥጢራት ነበሩ፤ እነዚህ ድንቅ ምሥጢሮች በራሳቸው ከንግግርና ከቋንቋዎች ሁሉ በላይ ሁነው የሚነገሩ በእግዚአብሔር የዝምታ መጎናጸፊያ የተጠቀለሉ ድብቅና ጣፋጭ ምሥጢሮች ናቸው ይላል፡፡

ምስጋናዋ የበዛለት ቅዱስ ኤፍሬም ሶርያዊ “አቤቱ መሰንቆ ልቡናዬን አነቃቃ የልቤንም እንዚራ፤ ድምፁን ከፍ አድርጎ የዳዊት ልጅ የሆነችውን የጌታውን እናት ድንግል ማርያምን ያመሰግናት ዘንድ፥ ለዓለም ሕይወት የሚሰጠውን የወለደች እናቱ የሆነች እርሷን ከፍ ከፍ ያደርጋት ዘንድ” ብሏል፡፡ በሌላም አንቀጽ “ከሕሊናት ሁሉ በላይ ለሆነ ለዚህ ነገር አንክሮ ይገባል፤ ምድራዊት ሴት ፈጣሪዋን ወለደችው እርሱም እናቱን ፈጠረ” አለ፡፡ ስለ እነዚህ ነገሮች ሁሉ ምን ማለትን እንችላለን? እግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስ ስለ ድንግል ማርያም ያልተናገረበት ጊዜ ያላናገረው ቅዱስ እንደሌለ እንመለከታለን፡፡

በእግዚአብሔር በሰውና በመላእክቱ ፊት የከበረ ሰው መታሰቢያው ለዘለዓለም ነው፡፡ በቤቱ በቅጥሩ የማይጠፋ የዘለዓለም ስምን ይቀበላልና፡፡ /ኢሳ.፶፭፥፫/55፥3/ ይህንን ታላቅ በረከት እንደሚሰጣቸው የተናገረ የማይዋሸው ቅዱስ እግዚአብሔር ነው፡፡ ከእግዚአብሔር ወልድ እናት ከድንግል ማርያም የበለጠ በሰውና በእግዚአብሔር ዘንድ የከበረ ማንን ልንጠራ እንችላለን? ከእርሷስ ሲታሰብ ሊከበርም የሚችል በቅድስና ሕይወት ያለፈ ማን ይኖራል?

አስቀድሞ ሁሉን ያዘጋጀ እግዚአብሔር ነው፡፡ ቅዱስ እግዚአብሔር ፍጥረቱንና ዓለሙን ለማዳን የመረጠው ጊዜ በደረሰ ጊዜ ከድንግል ማርያም በድንግልና ተወለደ፡፡ አስቀድሞ በመልአኩ አፍ እንዳናገረ ክብሩ በእርሷ ላይ ታየ /ኢሳ.፷፥፪/60፥2/ ማኅፀኗን ከተማ አድርጎ ዘጠኝ ወር ከአምስት ቀን በእርስዋ አደረ፡፡ በእመቤታችን ያደረ መንፈስ ቅዱስ “ያነጻቸው ዘንድ ይቀድሳቸውም ዘንድ በሥጋም በነፍስም መርቶ ወደ እግዚአብሔር መንግሥት ያገባቸው ዘንድ በነቢያት በሐዋርያት ላይ እንዳደረው አይደለም፤ ከሦስቱ አካል አንዱ አካል እግዚአብሔር ወልድ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየስስ ክርስቶስ ከሥጋዋ ሥጋን ከነፍስዋ ነፍስን ነስቶ ፍጹም ሰው ፍጹም አምላክ ሆነ እንጂ፡፡ ቅዱስ ሉቃስ ይህን ዘለዓለማዊ እውነት “መንፈስ ቅዱስ በአንቺ ላይ ይመጣል፤ የልዑል ኃይልም ይጸልልሻል ስለዚህ ከአንቺ የሚወለደው ቅዱስ የእግዚአብሔር ልጅ ይባላል” /ሉቃ.፩፥፵፭/1፥45/ በማለት ገልጾታል፡፡

ኢትዮጵያዊው ሊቅ ደራሲና ገጣሚ አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ “የእስራኤል ንጉሥ በእስራኤል ልጅ አደረ፤ የዳዊት አምላክ ከዳዊት ልጅ ሥጋን ለበሰ፤ የዕብራውያን ጌታ በዕብራውያን ልጅ ማኅፀን ተወሰነ፡፡ ለአብርሃም የዕብራይስጥ ልሳን ያስተማረው ከቀድሞም ያልሰማውን ልሳን እንዲናገር አፉን ጆሮውን የከፈተለት ከዕብራዊት ድንግል ተወለደ፤ በድንግልና ወተት አደገ፤ ጥቂት ጥቂት እያለ አደገ፥ የሕፃናትን ሥርዓት እንዳያጎድል አፉን የሚፈታባት ዘመን እስኪፈጸም ጥቂት ጥቂት እያለ በዕብራይስጥ ልሳን ሲናገር ኖረ፡፡ ለሙሴ በዕብራይስጥ ልሳን በጣቶቹ የተጻፉትን ዐሠርቱ ቃላት በድንጋይ ሰሌዳ የተጻፈውን የሰጠው የዕብራይስጥ ፊደል ለመማር ከመምህር እግር በታች ተቀመጠ፡፡ የባቢሎን አውራጃ በምትሆን ሰናዖርም የፍጥረትን ሁሉ ቋንቋ የበተነ እርሱ የአሕዛብን ቋንቋ እንደማያውቅ ሁሉ እናቱ አፍ በፈታችበት ልሳን በዕብራይስጥ ልሳን ሲናገር ኖረ፤ ጆሮ ይህንን ነገር ከመስማት የተነሣ የሚለመልምበት ይህ ነገር ዕጹብ ድንቅ ነው፡፡ ለዚህ አንክሮ ይገባል አለ፡፡ ይህ በሰው ጥበብ በብራናና በቀለም የተጻፈ እውነት ሳይሆን ለድኅነት በተጠሩ ሰዎች ሁሉ ልቡና በአምላክ ጥበብ የተጻፈ እውነት ነው፡፡

አስደናቂው የድንግል ማርያም ሞት

ኢትዮጵያዊው ሊቅ አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ በመጽሐፈ አርጋኖን ድርሰቱ ከሚያሰጥመው ባሕር ሞገድ የተነሣ የማትነቀነቅ፥ መልኅቆቿም በሦስቱ ሥላሴ ገመድ የተሸረቡ ናቸው ይህቺ ደግሞ ከነፋሳት ኃይል የተነሣ የማትናወጥ በጭንጫ ላይ ያለች የዕንቈ ባሕርይ ምሰሶ ናት፤ እርሷን የተጠጋ መውደቅ መሰናከል የለበትም” የሚላት እመቤታችን ሞት አይቀርምና እርሷም እንደሰው የምትሞትበት ጊዜ ደረሰ፡፡ እግዚአብሔር አያዳላምና፡፡ /ሮሜ.፪፥፲፩/2፥11/ ቅድስት ድንግል ማርያም የኃያሉ እግዚአብሔር እናቱ፥ መቅደሱ፥ ታቦቱ፥ መንበሩ ሆና እያለ ሞትን መቅመሷ በራሱ የሚያስገርም ምሥጢር ነው፡፡ ከቤተ ክርስትያን ወገን ሞትን እንዳያዩ የተወሰዱ ቅዱሳን ሄኖክ፥ ኤልያስ፥ ሌሎችም እንዳሉ የቅዱሳት መጻሕፍት ምስክርነት አለ፡፡ ይህ ከኅሊናት ሁሉ በላይ የሆነው ምሥጢር ርቀቱ በመጽሐፈ ዚቅ እንዲህ ተብሏል፡፡ “ለምንት ይዜኃር ኃያል በኃይሉ ወባዕል በብዝኃ ብዕሉ ኢያድለወ  ሞት ክርስቶስ ለሥጋ አባሉ ሞትሰ ለመዋቲ ይደሉ ሞታ ለማርያም የአጽብ ለኩሉ፡፡ ኃይለኛ በኃይሉ ለምን ይታጀራል? ባለ ጸጋም በሀብቱ ብዛት፡፡ ክርስቶስ ለአካሉ አላዳላም፤ ሞትስ ለሟች ይገባዋል የእመቤታችን የቅድስት ማርያም ሞት ግን አስደናቂ ነው”

እመቤታችን ያረፈችው በጥር ሃያ አንድ ቀን ነው፤ በአባት በእናቷ ቤት ሦስት ዓመት ኖረች፤ ዐሠራ ሁለት ዓመት በቤተ መቅደስ ኖረች፤ ከልጇ ጋር ሠላሣ ሦስት ዓመት ከሦስት ወራት፤ ከጌታ ስቅለት በኋላ ዐሥራ አምስት ዓመታት ኖረች፤ ጌታን የጸነሰችበትን ወራት ስንጨምር በዚህ ዓለም በሥጋ የቆየችበት ጊዜ ስድሳ አራት ዓመት ይሆናል፡፡

የቤተ ክርስቲያን ትውፊት የድንግል ማርያም ሞት በሚከተሉት ምክንያቶች እንደሆነ ያስረዳል፤ የመጀመሪያው “ለመለኮት ማደርያ ለመሆን የበቃችው ኃይል አርያማዊት ብትሆን ነው እንዷ ምድራዊት ሴትማ እንደምን ሰማይና ምድር የማይችለውን ልትሸከመው ይቻላታል?” የሚሉ ወገኖች ነበሩና በርግጥም እግዚአብሔር ወልድ የተዋሐደው የሰው ልጆችን ሥጋ እንጂ የመላእክትን አለመሆኑን ለማጠየቅ ነው፡፡ ይህንን ሁኔታ ቅዱስ ጳውሎስ ሲያስረዳ “እንግዲህ ልጆቹ በሥጋና በደም ስለሚካፈሉ፥ እርሱ ደግሞ በሞት ላይ ሥልጣን ያለውን በሞት እንዲሽር፥ ይኸውም ዲያብሎስ ነው፥በሕይወታቸው ሁሉ ስለሞት ፍርሃት በባርነት ይታሰሩ የነበሩትን ሁሉ ነጻ እንዲያወጣ፥ በሥጋና በደም እንዲሁ ተካፈለ፡፡ የአብርሃምን ዘር ይዟል እንጂ የያዘው የመላእክትን አይደለም” አለ፡፡ /ዕብ.፪፥፲፬-፲፭/2፥14-15/ በዚህም ድንግል ማርያም የአዳም ዘር መሆኗ ታወቀ፡፡ ሁለተኛው ቅዱስ ያሬድ እንዳለው ጌታችን በፍርዱ አድልዎ የሌለበት መሆኑ ይታወቅ ዘንድ ነው፡፡ ሥጋ የለበሰ ሁሉ በለበሰው ሥጋ ሞትን ይቀምስ ዘንድ የግድ ነውና፡፡

ትንሣኤ

በቃል መነገሩ በአንደበት መዘከሩ ለአምላካችን ለልዑል እግዚአብሔር ክብር ምስጋና ይግባውና “ከሞት ወጥመድ በላይ እንኳን የሆነ ሌላ ኃይል አለ፤ ይሄውም ሞት ፈጽሞ ሊያሸንፈውና ሊገዳደረው የማይችል የእግዚአብሔር መለኮታዊ ኃይል ነው፡፡ በሰይጣን ዘንድ ያለው የሞት ኃይል ነው ሕያው እግዚአብሔር የሕያዋን አምላክ ነውና ሞት ሊያሸንፈው ሊደርስበትም የማይችለውን ሕይወት ይሰጣል፡፡ ይህንን እግዚአብሔር የሚሰጠውን ሕይወት ሰይጣን በእጁ ሊነካው ከቶውንም አይችልም፡፡ እግዚአብሔር ለሙታን ሕይወትን ይሰጣል የሞትና የሕይወት ባለቤት ነው፡፡” የእመቤታችን ድንግል ማርያም ዕርገት

ከሞት ሥልጣንና ኃይል በላይ የሆነው ይኸው የእግዚአብሔር መለኮታዊ ሥልጣን የድንግል ማርያምን ሥጋ መልካምም ሆነ ክፉ ለሠሩ ሰዎች ዋጋ ይከፍል ዘንድ ለፍርድ እስከሚመጣበት ጊዜ ድረስ በመቃብር ውስጥ ተጠብቆ እንዲቆይ፤ ፈርሶና በስብሶ በምድር ላይ እንዲቀር አላደረገም፡፡ ከሙታን መካከል ተለይታ ተነሥታለች፡፡ እንድትነሣም ያደረገ የጌታ ኃይል ነው፤ በራሷ የተነሣች አይደለችም፡፡ መንፈስ ቅዱስ በድንግልና ጸንሳ በድንግልና መውለዷን በትንቢት እንዳናገረ ትንሣኤዋንም በትንቢት ሲያናግር ኑሯል፡፡ ይህ ታላቅ ምሥጢር በቅዱስ ዳዊት አንደበት “ተንሥእ እግዚኦ ውስተ ዕረፍትከ አንተ ወታቦተ መቅደስከ፤ አቤቱ ወደ ዕረፍትህ ተነሥ አንተና የመቅደስህ ታቦትም” /መዝ.፻፴፩፥፰/131፥8/ ብሎ ገልጾታል፡፡ ቅዱስ ዳዊት በዚህ የትንቢት ክፍል ትንሣኤዋን አስረድቷል፡፡ ታቦት የጽላቱ ማደሪያ ነው፡፡ በታቦቱ ውስጥ የሚያድረው በእግዚአብሔር ጣቶች የተጻፈው ሕጉ ነው፡፡ ይህ እግዚአብሔር ያከበረው ነገር ሆኖ ሊመጣ ላለው ነገር ማሳያ ነው፡፡ እውነተኛዋ ታቦት ማርያም ናት፡፡ ሙሴ በተቀበለው ታቦት ውስጥ ያለው ጽላት በውስጡ የያዘው ሕጉን ነው፤ በድንግል ማርያም ላይ ያደረው ግን የሕጉ ባለቤት ነውና፡፡ ከፍጡራን ከፍ ከፍ የማለቷ ድንቅ ምሥጢርም ይህ ነውና፡፡ ትምክህቷም፣ ትውክልቷም ጌታ እግዚአብሔር እንደሆነ በወንጌላውያኑ ተነግሮላታል፡፡ መንፈስ ቅዱስ ያላናገራቸውን ከልባቸው አንቅተው አይጽፉምና፡፡ እርሷም” ነፍሴ ጌታን ታከብረዋለች መንፈሴም በአምላኬ በመድኃኒቴ ሐሴትን ታደርጋለች” አለችን /ሉቃ.፩፥፵፯/1፥47/፡፡ ይህ ቃል ንጽህናዋ ቅድስናዋ በተረዳ ነገር ታውቆ ፍጥረት ሁሉ ከልቡ ከሚያከብራት እመቤት የተነገረ ቃል እንጂ ራሳቸውን ያለአጥርና ያለከልካይ አድርገው ቃሉን ከሚሸቃቅጡ ሰዎች ወገን የተሰጠ ምስክርነት አይደለም፡፡

እርስዋ ከኪሩቤል ትበልጣለች፤ ከሱራፌልም ትከብራለች ጌታችን የሱራፌልን፥ ኪሩቤልን ባሕርይ ባሕርዩ አላደረገም፡፡ የመላእክትንም ባሕርይ እንደዚሁ፥ የእርሷን አካል ባሕርዩ አደረገ እንጂ፡፡

የክርስቲያኖችን ትንሣኤ ሙታን የሚመሰክር ልዕልና

ከምድር ሰዎች ሁሉ ጥበበኛ የሆነው ሰሎሞን እንዲህ አለ፡- “ወዳጄ ሆይ ተነሽ፤ ውበቴ ሆይ ነይ፡፡ እነሆ ክረምት አለፈ፥ ዝናሙም አልፎ ሄደ አበቦች በምድር ላይ ተገለጡ፥ የዜማም ጊዜ ደረሰ፥ የቁርዬም ቃል በምድር ላይ ተሰማ”፡፡ /መኃ.፪፥፲-፲፬/2፥10-14/ ይህ ትንቢት የዚህ ዓለም ድካሟ ሁሉ መፈጸሙን ያስረዳል፡፡ ልጇን ይዛ ከሀገር ሀገር በረሀብና ጥም የተንከራተተችበት ጊዜ አሁን አለፈ፡፡ ታናሽ ብላቴና ሳለች ልጇን አዝላ በግብጽ በረሃ የተቀበለችው መከራ ሁሉ ፍጻሜ አገኘ፡፡ ከእግረ መስቀል ሥር ወድቃ የልጇን የቆሰለ ገላ እየተመለከተች የደረሰባት ልብ የሚሰነጥቅ ኀዘን ወደ ደስታ ተለወጠ፡፡ በነፍሷ ሰይፍ ያልፋል ተብሎ የተነገረው ልብ የሚሰነጥቅ መከራ እንደ ነቢዩ ቃል ትንቢት የሚቀጥልበት ጊዜ ተፈጸመ፡፡ እርሷ ባለችበት ሥፍራ የሕይወት ትንሣኤ ያላቸው ሰዎች ይሆኑ ዘንድ አስቀድማ ከሙታን ተለይታ በመነሣት የተጠበቀልን ተስፋ ማሳያ ሆነችን፡፡ በእግዚአብሔር መንግሥት ስደት መከራ ኃዘን ሰቆቃ የለም፤ መገፋት መግፋትም የለም፡፡

እመቤታችን ትንቢቱ የተፈጸመባት ሁና እያለ ከማንኛውም ሐዋርያ በላይ ለእግዚአብሔር ቃል መስፋፋት የወንጌል ዘር በተዘራበት ቦታ ሁሉ ነበረች፡፡ ለመንግሥቱም እንደሚገባ ሁና ኑራለች፡፡ በማኅፀን የተጀመረው የማዳን ሥራ፤ ፍጻሜውን ያገኘው በቀራንዮ ነው፡፡ በቤተ ክርስቲያናችን አስተምህሮ የጌታ ልደቱና ጥምቀቱ፣ ሞቱ ትንሣኤው ዕርገቱና ዳግመኛ መምጣቱ በነገረ ድኅነት ትምህርታችን እጅግ ጠቃሚ የሆኑ ምሥጢራት ናቸው፡፡ ቤተልሔም የሥጋዌውን ምሥጢር ሲያሳይ ዮርዳኖስ ቀዳማዊ ልደቱን ያሳያል፡፡ የመጀመርያው የእኛ ባሕርይ ሲሆን ሁለተኛ የጌታ የራሱ የባሕርይ ገንዘቡ የሆነ ነው፡፡ እርሱ የሰው ልጅ ሆነ፤ እኛ ደግሞ የእግዚአብሔር ልጆች ሆንን ይህ ሁሉ የተደረገው ከድንግል ማርያም በነሳው ሥጋ ነው፡፡ እርሱ የእኛን ተፈጠሮ ገንዘቡ ስላደረገ፤ እኛ ደግሞ የእርሱን ቅድስና ገንዘብ በማድረግ የመንግሥቱ ተካፋዮች ሆንን፡፡ የእኛ የሆነው ሁሉ የእርሱ የእርሱ የሆነው የእኛ በመሆኑ ከፍ ከፍ እናደርገዋለን፡፡ ለዚህ ክብር በቀታ ያከበረችንን ከእግዚአብሔር ጋር ያዛመደችንን እመቤት እንደምን አናከብራትም?

የእኛ መንፈሳዊ ልደት የተገኘው ጌታ በሥጋ ከቅድስት ድንግል ማርያም በተወለደው ልደት ነው፡፡ “የቅድስት ድንግል ማርያም ማኅጸን አምላክና የሰው ልጆች የተገናኙበት፤ አምላክና ሰው የተዋሐዱበት መካነ ምሕረት ነው፡፡ እግዚአብሔር ዙፋኑን ዘጠኝ ወር ከአምስት ቀናት የዘረጋበት መካነ ሰላም ነው፤ የእግዚአብሔር ዙፋን ፍጹም በማይናወጥና ጸጥታ በነገሠበት ስፍራ የሚዘረጋ የክብር ዙፋን ነው፡፡ ይህም ዙፋን የቅድስት ድንግል ማርያም ማኅጸን ነው፡፡”

በቀራንዮ አደባባይም በኀዘን ነበረች፡፡ ሐዋርያት ጉባኤያትን ሲያበዙ አብራቸው ነበረች፤ ይህ ሁሉ ታላቅ ሥራ ከተፈጸመ በኋላ ዓረፍተ ዘመን ገታት፡፡ በሥጋ ዓረፈች፡፡ ያረፈችው በጥር ሃያ አንድ ቀን ነው፤ ሐዋርያትም ሊቀብሯት ሲሹም ከአይሁድ ክፋት የተነሣ ልጇ ሌላ ክብርን ደረበላት ከጌቴሴማኒ ሥጋዋ ተነጥቆ በገነት በዕፀ ሕይወት ሥር እስከ ነሐሴ ዐሥራ ስድስት ቀን ለሁለት መቶ አምስት ቀናት ቆይታለች፡፡ ልጇ ወዳጇ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ሞትን በሥልጣኑ እንዳሸነፈ የልጇ መለኮታዊ ኃይል ሞትን አሸንፋ እንድትነሣ አደረጋት፤ ጠቢቡ ሰሎሞን ስለ ትንሣኤዋ የተናገረው ቃል ተፈጸመ፡፡ ሊቁ “ለዛቲ ብእሲት ሠረቀ ላዕሌሃ ብዕለ ጸጋሁ ለአብ ወአግዓዛ እምእኩይ ውስተ ሰናይ እሞት ውስተ ሕይወት፤ በድንግል ማርያም ላይ የአብ የባለጸግነቱ ብዛት ተገለጠ ከሞት ወደ ሕይወት ከክፉ ዓለም ወደ በጎ ዓለም አሸጋግሯታልና፤ ያለው ይኸንን ነው”፡፡ ከእንግዲህ ወዲያ ልጇ ሲንገላታ፣ ሲሰደድ ሲገረፍ፣ ሲሰቀል፣ ሲቸነከር ያየችበት ዓለም አለፈ፡፡ አሁን የልጇን ልዕልና ከሚያደንቁ ጋር ታደንቃለች፤ ከፍ ከፍ ከሚያደርጉት ጋር ታከብረዋለች፡፡ ይኸም ከገቡ የማይወጡበት ኀዘን መከራ ችግር በሌለበት ሰማያዊት ሃገር ነው፡፡ ቅዱሳን ሩጫቸውን ጨርሰው የድል አክሊልን የሚቀዳጁበት ሥፍራ ነው፡፡ በዚህም ከፍጡራን ሁሉ ከፍ ባለ በታላቅ ክብርና ጸጋ ለዘላለም እንደምትኖር እናምናለን፡፡

ልመናዋ ክብሯ ፍቅሯ አማላጅነቷ የልጇም ቸርነት በሁላችንም ላይ አድሮ ይኑር፡፡

ምንጭ ፡ ሐመር 18ኛ ዓመት ቁጥር 5

ሦስት አራተኛው መሬት

የእግዚአብሔርን ቅንነት የተረዳ ቅዱስ አባት

ሐምሌ 82003 ዓ.
ቅዱስ ኪሮስ ወደ አባ በብኑዳ በደረሰ ጊዜ ዐፅሙ በየቦታው ተበትኖ አንበሳ ሲበላው አገኘ በዚህም ሠዓት በጣም አምርሮ እያለቀሰ “ጌታ ሆይ፥ ለምን እንዲህ ታደርጋለህ ፍርድህ መልካም አይደለም፤ በመንግሥት፥ በመብልና በመጠጥ በደስታ የኖሩትን በክብር እንዲቀበሩ ታደርጋለህ፥ ስለ አንተ ሲሉ አባትና እናትን ሚስትን ልጆችን ደስታን ሁሉ ትተው በተራራና በዋሻ በጾምና በጸሎት የኖሩትን ደግሞ ሥጋቸውን ለዱር አራዊት ትሰጣለህ፥ “የአንተን ፍርድ ነገር ላልሰማ እንዳልነሣ ሕያው ስምህን” ብሎ መሬት ላይ ተኛ፡፡

ቅዱስ ኪሮስ የሮም ንጉሥ የነበረው የአብያና የሚስቱ ሜናሴር ሁለተኛ ልጅ ነው። ስሙንም ዲላሶር አሉት። ንጉሥ አብያ ካረፈ በኋላ ታላቁ ቴዎዶስዮስ ነገሠ፡፡ ዲላሶርም በከተማ ውስጥ የሚሠራውን ዓመፅ በዐየ ጊዜ በሌሊት ተነሥቶ፥ ከሀገር ወጥቶ፥ ትንሽ በዓት አግኝቶ ዐሥር ቀን በዚያች ቆየ፡፡ መንፈስ ቅዱስ ኪሮስ ብሎ ጠራውና “ለብዙዎች አባት ትሆናለህ፥ በቃልህም ክርዳድ ይነቀላል፥ የአንድ ቀን መንገድ ሒድና ገዳማዊ መነኰስ ታገኛለህ፥ ከእርሱም ልብሰ ምንኲስና ትለብሳለህ” አለው፡፡ እንደ ታዘዘው በሔደ ጊዜ ከአንዲት በዓት የራስ ፀጉሩ እስከ እግሩ የሚደርስ፣ ግርማው የሚያስፈራ ገዳማዊ ወጥቶ “ኪሮስ መነኲሴ ለመሆን ወደዚህ መጣህን አለው፡፡ ኪሮስም ግርማውን እያደነቀ ቀርቦ ተባረከና ሦስት ቀን ከቆየ በኋላ “ኪሮስ ሆይ፥ እንደ እኔ መሆን ትፈልጋለህን” አለው፡፡ እርሱም “አዎ፥ በጣም እፈልጋለሁ” ባለው ጊዜ አባ በብኑዳ ትንሽ ደመናን ጠርቶ በዚያ ላይ በመሆን ከአስቄጥስ ገዳም በመሄድ የምንኲስናን ልብስ ተቀብሎ በዚያችው ደመና ኪሮስ ካለበት ቦታ ተመለሰ፡፡ ያመጣውን አልባሰ ምንኲስናም ለኪሮስ አለበሰው፡፡
ለአባ በብኑዳ ሁልጊዜ በሠርክ ሰማያዊ ኅብስትና ጽዋዐ ወይን ቅዱስ ሚካኤል ያመጣለት ነበር፡፡ አባ ኪሮስ በዚያ ለአባ በብኑዳ እየታዘዘ ሲኖር አንድ ገዳማዊ ሰው ወደ አባ በብኑዳ መጥቶ ሳለ ምንም ነገር እንደ ሌለው ዐይቶ “ምን ትበላለህ” ቢለው “አምላካችን ይሰጠናል” አለው፡፡ ያ እንግዳ መነኲሴም በልቡ “እንደ እኛ ሰው አይደለምን” እያለ ሲያስብ አባ በብኑዳ በመንፈስ ዐውቆ “ለምን እንዲህ ታስባለህ” “እኔም እንዳንተ በደለኛና ኀጥእ የሆንኩ መነኲሴ ነኝ” አለው፡፡ ይህን እየተነጋገሩ ሳለ የሠርክ ጸሎት ደርሶ በኅብረት ሲጸልዩ ፈጽሞ ደስ የሚል መዓዛ መጣ፥ ወዲያውም የተዘጋጀ ኅብስትና ጽዋዐ ወይን ይዞ ቅዱስ ሚካኤልን ሲመጣ ዐየውና ተቀበለው፥ ያ እንግዳ መነኲሴ ግን አላየውም፥ አሁንም “አስቀድሞ ያልነበረ ይህን ጽዋና ኅብስት ከየት አገኘው ይህ ባሕታዊ መሠሪ ነው” እያለ አሰበ፥ አባ በብኑዳም “ለምን እንዲህ ክፉ ታስባለህ?” አለው፥ መነኲሴውም አድንቆ ተቀምጠው መመገብ ጀመሩ፡፡
ያ እንግዳ መነኲሴ ግን ከዚያ ኅብስተ ሰማይ ቆርሶ በልብሱ ደብቆ ወደ አስቄጥስ ገዳም ሔደ፡፡ በዚያ ያሉ መነኰሳትንም ሰብስቦ ያን በረድ የሚመስል ኅብስተ ሰማይ አሳያቸው፡፡ “የት አገኘኸው” ቢሉት፥ “በዮርዳኖስ ገዳም ውስጥ በብኑዳ የሚባል መሠሪ ሰው አለ፥ ኑ ተከተሉኝና ታመጡት ዘንድ ወደዚያ ልውሰዳችሁ” አላቸው፡፡ ይህን ሲነጋገሩ ቅዱስ ሚካኤል መጥቶ ያችን የኅብስት ቁራሽ ወደ ሰማይ ወሰዳትና በልዑል ፊት ሰገደ፥ እግዚአብሔርም “መልካም አገልጋዬ ሆይ፥ የተቀደሰውን ለውሻ የሰጠ በብኑዳ ክፉ አደረገ፥ ስለዚህም በአንበሳ ተሰብሮ እንዲሞት አደረግኹ፥ ይህም በረከት ይከለከላል፥ ይህንንም ኅብስት በበረሃ ላለ ፊልሞና ለሚባል መነኲሴ እስከ ዕለተ ሞቱ ሲሳይ እንዲሆነው ስጠው” አለው፡፡ ቅዱስ ሚካኤልም እንደ ታዘዘው አደረገ፡፡ የአስቄጥስ ገዳም ቅዱሳንም ያን መነኲሴ “እኛን ማን መምህርና ፈራጅ አድርጐ ሾመን” አሉት፥ በዚህ ጊዜ አዘነና ወደ ማደርያው ሔዶ ታንቆ ሞተ፡፡
አባ በብኑዳም ይመጣለት የነበረው መና ተከለከለ፥ ሦስት ቀን ምንም ሳይቀምስ ከቆየ በኋላ እያለቀሰ አባ ኪሮስን “ልጄ ሆይ፥ ሰይጣን ወደ ማደርያችን ገብቶአል፥ ያገኘን ይህ ነገር ምንድ ነው” አለው፡፡ አባ ኪሮስም “ያ መነኲሴ መጥቶ ከሄደ በኋላ እግዚአብሔር ተቆጥቷል” አለው፡፡  አባ በብኑዳም “የእግዚአብሔር ፈቃድ ይሁን” አለ፡፡ ከዚያም አባ ኪሮስ ፍሬን እየሰበሰበ ይመለስ ነበር፥ አባ በብኑዳ ግን በቀንም ሆነ በማታ ከበኣቱ ሳይወጣ ይጸልይ እንደ መንኰራኲርም ይሰግድ ነበር፡፡
አባ ኪሮስም እንዲህ እያለ ሲኖር፥ አንድ ቀን የዕለት ሲሳይ ፍለጋ ወደ አንድ ሀገር ሄዶ ሳለ የኬልቄዶን ንጉሥ ሞቶ፥ ሕዝቡ ሁሉ እየጮኹና እያለቀሱ፥ ምድር እየረገጡ፥ ብዙ የፈረሰኛ ሰልፍ ተሰልፎ፥ በአስከሬኑ ላይ ድባብ እየዘረጉ ካህናት በማዕጠንት በፊቱና በኋላው እየዘመሩ ባየ ጊዜ አንዱን ሰው “ይህ የማየው ምንድን ነው?” ብሎ ቢጠይቀው “የኬልቄዶን ንጉሥ ስለ ሞተ ነው” አለው፡፡ አባ ኪሮስም “ለሞተ ሰው ይህን ያህል ይደረጋልን እኔስ ንጉሥ ለልጁ ሰርግ ያደረገ መስሎኝ ነበር” አለ፡፡ ይህን ብሎ አልፎ ፍሬ ሰብስቦ ወደ ማደርያው ወደ አባ በብኑዳ በደረሰ ጊዜ ዐፅሙ በየቦታው ተበታትኖ አንበሳ ሲበላው ባገኘ ጊዜ በጣም አምርሮ እያለቀሰ “ጌታ ሆይ፥ ለምን እንዲህ ታደርጋለህ ፍርድህ መልካም አይደለም፤ በመንግሥት፥ በመብልና በመጠጥ በደስታ የኖሩትን በክብር እንዱቀበሩ ታደርጋለህ፥ ስለ አንተ ሲሉ አባትና እናትን ሚስትን ልጆችን ደስታን ሁሉ ትተው በተራራና በዋሻ በጾምና በጸሎት የኖሩትን ደግሞ ሥጋቸውን ለዱር አራዊት ትሰጣለህ፥ የአንተን ፍርድ ነገር ላልሰማ እንዳልነሣ ሕያው ስምህን ብሎ መሬት ላይ ተኛ፡፡ አርባ ዓመት ሲሆነው ግማሽ ሥጋው አለቀ፤ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በመልአክ አምሳል ተገጾ “ተጋዳይ የሆንክ አርበኛ ኪሮስ ሆይ፥ ሰላም ላንተ ይሁን፥ ተነሥ” አለው፡፡
ኪሮስም “አንተ ማነህ መልአከ እግዚአብሔር ከሆንክ በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ በል” አለው፡፡ ጌታችንም “በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ” አለ፡፡ ኪሮስ መነሣት ባቃተው ጊዜ ምድርን “ሥጋውን አትያዥ” ባላት ጊዜ ፈጥኖ ተነሣ፥ ኪሮስም ጌታችን እንደ ሆነ ዐወቀው፤ መላ ሰውነቱን ዳበሰው፤ ሰውነቱ እንደ ሕፃን ሆነ፤ በምድር ላይ ሰግዶ ጌታችን እንደ መብረቅ ሲለወጥና እልፍ አእላፋት መላእክት ሲያመሰግኑት አያቸው፡፡ ጌታችንም “ኪሮስ ሆይ፥ አንተ ሚስትህን፣ ልጆችህን፣  መንግሥትህን የተውህልኝ የማርያም ልጅ ኢየሱስ ነኝ፥ ስለ ሁሉ ብዙ የብዙ ብዙ ታገኛለህ፥ በምድር ላይ እንዳንተ ትዕግሥትን የለበሰ አላገኘሁም፥ ለዚያ እንግዳ መነኲሴ ቅድሳቴን ለምን ሰጣችሁት ስለዚህ ነው የበብኑዳን ሥጋ ለአራዊት የሰጠሁት፤ በዚህ ምክንያት በፊቴ እንዳይወቀስ ነው፡፡ ለሁሉ ሥራ ፍዳ አለውና፥ አምላኩ በምድር ላይ የገሠጸው ሰው ብፁዕ ነው፥ ያለውን አልሰማህምን” ኪሮስም “ጌታዬ ሆይ፥ ፍርድህ ቅን ነው” አለ፡፡ ጌታችንም “ከዚህ በኋላ የነፍስን ከሥጋ መለየት ታይ ዘንድ በገዳማት ሒድ፥ ከዚያም ወደ ማደሪያህ ተመለስ” ብሎት ተሠወረ፡፡
አባ ኪሮስ በጌታችን ታዝዞ ደብረ ባሳት በደረሰ ጊዜ ቤተ ክርስቲያንን ተሳልሞ፥ የእመቤታችንን ሥዕል ዐይቶ ከዐይኖቹ እንባ እያፈሰሰ “እመቤቴ ሆይ፥ አስቢኝ” አላት፡፡ ሥዕሊቱም “ኪሮስ ሆይ፥ መምጣትህ መልካም ነው፤ የአባትህን ዐፅም ትጠብቅ ዘንድ ወደ ማደርያህ ተመለስ” አለችው፡፡ ይህን ሰምቶ ከሥዕሏ ፊት ሰባት መቶ ስግደት ሰገደ፤ በዕብራይስጥ ቋንቋም “እንግዳ ነህና በቃህ፥ በምሕረት መዝገብም ተመዝግቦልሃል” የሚለውን ቃል ሰማ፡፡ ከዚያም መስፈርስ የሚባል ሕማም ለብዙ ጊዜ የታመመና በምድር ላይ የወደቀ ሰውን አገኘ፡፡ በራስጌው ቅዱስ ሚካኤልን፥ በግርጌው ገብርኤልን በቀኙም ሩፋኤልን በግራውም ሰዳክኤልን በክንፋቸው ጋርደውት ዐየ፡፡ እነርሱም “በገዳዮች ፊት ሞትን የማይፈራ ሆይ፥ እንዴት ነህ” ብለው ሰላምታ ሰጡት፡፡ እርሱም አድንቆ “በልዕልና ነዋሪዎች ሆይ፥ በዚህ ለምን ተቀመጣችሁ” አላቸው፡፡ እነርሱም “ይህን ድሀ እንድንጠብቀው ከእግዚአብሔር ታዝዘናል” አሉት፡፡ “እስከ መቼ” ቢላቸው “አምላካችን እስከሚያሳርፈው ድረስ” ብለውታል፡፡
ከዚህም በኋላ ወደ ታመመው ተመልሶ “በዚህ ቦታ ከኖርህና ከታመምህ ምን ያህል ዘመን ነው” ብሎ ጠየቀው፡፡ በሽተኛውም “በዚህ ቦታ ስኖር 65 ዓመት ነው፤ ከታመምኩ ሃያ ዓመት ነው” አለው፡፡ መልሶም “አበ ምኔቱና የገዳሙ መነኰሳት ይጐበኙሃል” አለው፡፡ በሽተኛውም “አባቴ ሆይ፥ የለም፥ ፊታቸውን ከዐየሁ ዐሥራ አምስት ዓመት ነው” አለው፡፡ አባ ኪሮስም “አባትህ ማነው እናትህስ ማናት” ብሎ በጠየቀው ጊዜ “አባቴ የኬልቄዶን ንጉሥ ነው፥ እናቴም ንግሥት ናት፥ በአባቴ ቤት ያሉ ሰዎች ወርቁንና ብሩን ቀጭኑንም ልብስ ከብዛቱ የተነሣ በእግሮቻቸው ይረግጡታል” አለው፡፡ ጥያቄውን በመቀጠል “ወደዚያች ገዳም ማን አደረሰህ?” ብሎ ጠየቀው፡፡ እርሱም “እንደ አንተ ያሉ ሁለት ሰዎች ወደ አባቴ ቤት መጥተው ከዚያ አደሩ፡፡ እኩለ ሌሊትም ሲሆን ፊቱ ብሩህ የሆነ ሰው ወደ እኔ መጥቶ ሚሳኤል ብሎ ጠርቶ ሲነጋ ተነሥተህ ከእነዚህ ቅዱሳን ጋር ሒድ አለኝ፡፡ እኔም ወጥቼ ወደዚህ ገዳም ደረስኩ” አለው፡፡ አባ ኪሮስም የአባቱን የበብኑዳንና የሌሎችንም ቤተ መንግሥትን እየተዉ የመነኑ ቅዱሳንን ሁኔታ እያነሣ አጽናናው፡፡ “እግዚአብሔርም የሚወደውን ይገሥጻልና አታድንቅ” አለው፡፡ ያ በሽተኛ /ሚሳኤልም/ “እውነት ነው ለእኔ ይገባኛል። ስለ ኃጢአቴም ይህን ተቀበልኩ” ብሎ መለሶ ዝም አለ፡፡
ያን ጊዜ በሞት ያሰናብተው ዘንድ አባ ኪሮስ ወደ እግዚአብሔር ጸለየ፡፡ ጌታችንም በክብር መጣ፡፡ ጌታችንም አባ ኪሮስን “ምን ያህል እንደምወድህ የመላእክት ሠራዊት ያዩና ያውቁ ዘንድ ይህችን የገነት ተክል አበባ ከእጄ ወስደህ በፊቱ ላይ ጣል” አለው፡፡ ኪሮስም እንዲሁ አደረገ፡፡ ያን ጊዜ የበሽተኛው የሚሳኤል ነፍስ ያለ ጻዕር በፍጥነት ወጣች፡፡ መድኃኒታችንም ተቀብሎ ሳማት፡፡ ከእርሱ ጋርም በብርሃን ሠረገላ ውስጥ አስቀመጣት፥ አውጥቶም በሰማያዊ ክብር አኖራት፥ አባ ኪሮስም አለቀሰ፡፡ አባ ኪሮስም የገዳሙን መነኰሳት “ያን በሽተኛ ቅበሩት” ሲላቸው ፈቃደኞች ባለመሆን እያንጐራጐሩ ነበር፡፡ አራቱ የመላእክት አለቆች ሥጋውን በከርቤና በሚዓ አጠኑ፡፡ የገዳሙ መነኰሳትም “የሚሸተን ምንድን ነው ይህ መነኰስ ሥራይን ያውቅ ይሆንን” ተባባሉ፡፡ ሥጋውንም በገዳሙ በእንግዳ መቃብር ቀበሩት፥ ከመቃብሩም ጥሩ ውኃ ፈለቀ፥ ለበሽተኖችም ፈውስ ሆነ፡፡ አባ ኪሮስም እነዚያን መነኰሳት በክፉ ሥራቸው ገሠጻቸው፥ መከራም ይመጣባችኋል አላቸው፡፡ ሊወግሩትም ድንጋይ በአነሡ ጊዜ ሠረገላ መጥቶ ወደ ማደርያው አደረሰው፡፡ በማግሥቱም ሽፍቶች መጥተው የዚያን ገዳም መነኰሳት በሙሉ ፈጁአቸው፥ ገዳሙንም አቃጠሉት፡፡
አባ ኪሮስ በበአቱ ሆኖ ሠራዊተ ጽልመት የእነዚህን ክፉዎች መነኰሳት ነፍሳት እያቻኰሉ ወደ ሲኦል ሲወስዷቸው ዐይቶ ይገባቸዋል አለ፡፡ በኋላ ግን እኒህ ስሑታን አሳቱኝ ብሎ እግዚአብሔር ይምራቸው ዘንድ 40 ቀንና ሌሊት ጾመ፡፡ “አልምራቸውምና አትድከም” የሚል ቃልን ሰማ፡፡ ከዚያም ከጋለ ድንጋይ ላይ ተኝቶ ሥጋው በእሳት እንደ ተጠበሰ እስኪሆን ቆየ፤ ቃልም “አልምራቸውምና አትድከም” አለው፡፡ እንደ ገና በሆዱ ተኝቶ ዐይኑ ወልቆ ታወረ፡፡ ሰይጣንም ከሩቅ ሆኖ “ብዙዎችን በኪዳንህ ያሳትክና ገንዘቤን ልትወስድ የተነሣህ ኪሮስ አንተ ነህን አሁን ዐይንህ ጠፋ ማን ይረዳሃል ማንስ ይመራሃል አለው፡፡ ይህን ሲሰማ አባ ኪሮስ ወደ ጌታችን ፈጽሞ እያለቀሰ ጸለየ፥ ጌታችንም ወደርሱ መጥቶ “ኪሮስ ሆይ፥ ሰላም ላንተ ይሁን፥ በእውነት አንተ ሰውን ወዳጅ ነህ፥ ድካምህ ሁሉ በኢየሩሳሌም ሰማያዊት ተመዝግቦአል፡፡ ልጁን በስምህ ለሚጠራ፥ በእምነት ሆኖ የገድልህን መጽሐፍ ያጻፈ፥ ያነበበ፥ መባዕና ዕጣን ለቤተ ክርስቲያንህ የሰጠውን ላንተ ዓሥራት ይሆን ዘንድ ሰጠሁህ፤ ካንተም ጋራ ባሕረ እሳትን ይለፍ፥ ደስም ይሰኝ” አለው፡፡ ይህንኑ ብሎ ራሱን በእጆቹ ይዞ ፈወሰው፡፡ ቅዱስ ኪሮስም “በፊትህ ሞገስ ካገኘሁ እነዚያን መነኲሳት ማርልኝ” አለው፡፡ ጌታችንም ያመጧቸው ዘንድ አዘዘ፥ ነፍሳቸውንም ከሥጋቸው ጋር አዋሕዶ አሥነሳቸው፥ አባ ኪሮስንም በዐዩ ጊዜ አፈሩ፡፡ በአባ ኪሮስ ልመና አልባሰ ምንኲስና ለበሱ፥ ወደ ገዳማቸው የሚወስድ መንገድንም አሳይቶአቸው እንዲሔዱ አዘዛቸው፡፡ ከገዳማቸውም ደርሰው ቤተ ክርስትየን ሠርተው በጾም በጸሎትና እንግዳ በመቀበል ኖሩ፡፡
ከብዙ ጊዜ በኋላ ቅዱስ ኪሮስ፥ የእነዚያን መነኰሳት ሕይወታቸውን ያይ ዘንድ መልአኩን ላክ ብሎ በጸለየ ጊዜ፥ ጌታችን፡- “አንተው ሔደህ ጐብኛቸው” ብሎ ደመናን ጠርቶ፥ በዚያች ላይ አውጥቶ፥ በሰላም ሒድ ብሎ አሰናበተው፡፡ ኪሮስም ወዲያው ደርሶ ወደ ሚሳኤል መቃብር ሔደ፥ መነኰሳትም ባዩት ጊዜ ከአበምኔቱ ጋር ሮጠው ሔደው አቅፈው እየሳሙት “ደኅና ነህን” አሉት። እርሱም “ውሻና ነዳይ ለምሆን ለእኔ ይህ ክብር ለምኔ ነው” አላቸው፡፡ እነርሱም ባለማወቃችን ያሳዘንህን ይቅር በለን ባሉት ጊዜ “እግዚአብሔር ይቅር ይበላችሁ፥ ነገር ግን ሁላችሁም የእግዚአብሔር አገልጋይ ሚሳኤል ሆይ፥ ይቅር በለን በሉ” አላቸው፡፡ እነርሱም “የእግዚአብሔር አገልጋይ ሚሳኤል ሆይ፥ ይቅር በለን” አሉ፡፡ በዚህን ጊዜ “እግዚአብሔር ይቅር ይበላችሁ፥ በእናንተ ምክንያት ወደ መንግሥተ ሰማያት ገብቻለሁና” የሚል ቃል ሰሙ፡፡
እነርሱም “ይህ የናቅነውና የጣልነው ሚሳኤል አይደለምን” ብለው እያደነቁ ዐፅሙን ወደ ቤተ ክርስቲየን ውስጥ ሊያስገቡት በፈለጉ ጊዜ “ባለበት ተዉት ነገር ግን በጸሎቱ ትጠቀሙ ዘንድ ተዝካሩን አድርጉ” አላቸው፡፡ እርሱም እየመከራቸው ወደ ቤተ ክርስቲያን ደረሱ፡፡ አባ ኪሮስም “የክርስቶስ ማደረያው ሆይ፥ ሰላም” ብሎ በተሳለመ ጊዜ “በሐከ ፈላሲ ክቡር፥ ክቡር መጻተኛ ሆይ ሰላም” ስላለው አደነቀ፡፡ አበ ምኔቱ በቤቴ እደር ቢለውም አይሆንም ብሎ በሚሳኤል ማደርያ በነበረው አንጻር ሔዶ አደረ፡፡ በማግሥቱም “ከእንግዲህ ወዲህ በመንግሥተ ሰማያት እንጂ በዚህ ምድር አንተያይምና በጸሎታችሁ አስቡኝ” ብሎ ተሰናብቷቸው ወደ ማደሪያው ተመልሶ አጋንንትን ኑ ሲላቸው እየመጡ፥ ሒዱ ሲላቸው እየሔዱ ሲገዛቸው ኖረ፡፡ ከዚያም በኋላ ቅዱስ ኪሮስ በገድልና በትሩፋት እየተቀጠቀጠ ለብዙ ዘመናት ከኖረ በኋላ ሐምሌ 8 ቀን ቅዱስ ዳዊት እየዘመረለት እልፍ አእላፋት ቅዱሳን መላእክት በተገኙበት ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ነፍሱን ከሥጋው ለይቶ አሳርጓታል፡፡ ጌታችንም የአስቄጥስ ገዳም አባ ባውማ ሥጋውን ገንዞ እንዲቀብረው አደረገ። እርሱም የንጉሥ ዘይኑን ልጅ ቅድስት ኢላርያን ሥጋዋን የገነዘ ነው። ደግሞም አባ ባውማ ጌታችን እንዳዘዘው በመንፈስ ቅዱስ የቅዱስ ኪሮስን ገድሉን የጻፈ ነው። “እኔ አባ ባውማም የቅዱስ ኪሮስን ገድሉን ጽፌ ለሚያነበውና ለሚሰማው ሁሉ መጽናኛ ይሆን ዘንድ ወደ አብያተ ክርስቲያናት ሁሉና ወደ ገዳማትም ላክሁ።” እንዳለ ስንክሳር ዘወርኀ ሐምሌ
ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም በጻድቁ አቡነ ኪሮስ ጸሎት ይማረን በረከቱም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን፡፡
ሰላም ለኪሮስ ዘሰዓሞ ነደ ከናፍር፡፡ ወበዘባኑ ተጽዕነ ለእግዚአብሔር፡፡ ወከመ ትጻእ ነፍሱ ዘእንበለ ጻዕር፡፡ ኀለየ እንዘ ይብል በመሰንቆ ሐዋዝ መዝሙር፡፡ ለጻድቅ ብእሲ ሞቱ ክቡር፡፡
 
ምንጭ፡- ያረጋል አበጋዝ (ዲ/ን) ና አሉላ ጥላሁን ፣ 1997። ነገረ ቅዱሳን 3። ማኅበረ ቅዱሳን፣ አ.አ።
        ስንክሳር በግዕዝና በአማርኛ ከመጋቢት እስከ ጳጒሜን፣ 1993
ትንሣኤ ዘጉባኤ ማተሚያ ቤት፣ አ.አ።

ማኅበረ ቅዱሳን የስብከተ ወንጌል ማስፋፊያ ፕሮግራም ቢሮ ያከናውናቸውን ተግባራት አስታወቀ።

በይብረሁ ይጥና

ሥራዎቹንም የሚያሳይ ዓውደ ጥናት በኢትዮጵያ የስብሰባ ማእከል እንደሚካሔድ ተገልጧል

በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ሰንበት ትምህርት ቤቶች ማደራጃ  መምሪያ ማኅበረ ቅዱሳን በትምህርትና ሐዋርያዊ አገልግሎት ዋና ክፍል የስብከተ ወንጌል ማስፋፊያ ፕሮግራም ማስተባበሪያ ቢሮ እስካሁን ያከናወናቸውንና በቀጣይ ሊሠራ ያቀዳቸውን ተግባራት አስታወቀ፡፡
 
የፕሮግራሙ ማስተባበሪያ ቢሮ ሓላፊ አቶ ዳንኤል ተስፋዬ እንዳስታ ወቁት በ2001 እና 2002 ዓ.ም ፕሮግራሙን ለምእመናን የማስተዋወቅና የመቅረጽ ሥራ ተሠርቶ በተወሰነ ደረጃ ወደ ትግበራ ተገብቷል፡፡

በ2003 ዓ.ም በጠቅላይ ቤተክህነት ለትምህርትና ሐዋርያዊ ተልእኮ መምሪያ ክፍል የተነደፈውን ፕሮግራም እንዲያውቀው ተደርጓል፡፡ መምሪያውም ለፕሮግራሙ ማስፈጸሚያ የሚሆን አስፈላጊውን ድጋፍ እንደሚያደርግ ቃል ተገብቷል፡፡

እንደዚሁም ከጠቅላይ ቤተክህነት ሰበካ መንፈሳዊ ጉባኤ መምሪያ ጋር በመሆን ፕሮግራሙ ተግባራዊ ከሚደረግባቸው ሃያ ሀገረ ስብከቶች ለተውጣጡ ሥራ አስኪያጆችና ሰባክያነ ወንጌል በጠቅላይ ቤተክህነት አዳራሽ ፕሮግራሙን የማስተዋወቅ ሥራ ከተሠራ በኋላ ለተግባራዊነቱ አስፈላጊውን ትብብር እንዲያደርጉ ደብዳቤ ተበትኗል ሲሉ አመልክተዋል፡፡

ፕሮግራሙ በዋናነት የሚያተኩረው ስብከተ ወንጌልን ለምእመናን ማዳረስ ሲሆን የንድፈ አሳቡ መነሻ ደግሞ በተለይ በጠረፋማና ገጠራማ አካባቢ ለሚገኙ ምእመናን ጉባኤ ማካሔድና ሰባኬ ወንጌል ከመመደብ ጀምሮ ለአካባቢው ካህናትና የሰንበት ትምህርት ቤት አመራር አባላትም የአቅም ግንባታ ሥልጠና መስጠት ነው፡፡

ፕሮግራሙ በመላው ሀገሪቱ ከሚገኙ ዐርባ አምስት ሀገረ ስብከቶች መካከል ችግሩ ይበልጥ ይከፋል ተብሎ በታመ ነባቸው ሃያ ሀገረ ስብከቶች መሆኑን አቶ ዳንኤል  ጠቁመው፣ በኦሮሚያና ደቡብ ክልል በሚገኙ ጠረፋማና ገጠር አካባቢዎች ልዩ ትኩረት ይደረጋል ብለዋል፡፡

የፕሮግራሙ ማስተባበሪያ ቢሮው በ2003 ዓ.ም እሠራቸዋለሁ ብሎ ካቀዳቸው ዕቅዶች መካከል፤ ዐሥር ሐዋርያዊ ጉዞ በማድረግ፣ ሃያ የሕዝብ ጉባኤያትን ማካሔድ፣ በተለያዩ ቋንቋዎች ዐሥራ ሁለት የስብከame=”Medium List 2 Accent 5″/> » አለው፡፡

ሊቀ ነቢያት ሙሴ ከእስራኤል ሽማገሌዎች ጋር በኮሬብ በነበረው ዐለት ያደረገው ስብሰባ በሐዲስ ዘመን ከተሰበሰቡት ሲኖዶሶች /ጉባኤዎች/ ጋር ይመሳሰላል፡፡

ሙሴ በሌላ ጊዜ በእግዚአብሔር ትእዛዝ ከእስራኤል ሽማግሌዎችና ከካህናቱ ጋር ወደ ደብረ ሲና ለመውጣት ያደረገው ስብሰባ ከሲኖዶስ ጋር የሚመሳሰል ነው፤/ዘፀ.19፡1-25/፡፡ በተለይም የእግዚአብሔርን ክብር ያዩ ዘንድ ሙሴና የእስራኤል ሽማግሌዎች፣ ከካህናቱ ጋር ወደ ደብረ ሲና ወጥተው በሩቅ ቆመው ለእግዚአብሔር ክብር ስግደት በማቅረብ የተሰበሰቡት ስብሰባ ሲኖዶስን የሚመስል ነው እንላለን፡፡ /ዘፀ.24111/፡፡

በሌላ በኩል የእስራኤል ልጆች ወደ ምድረ ከነዓን ለመግባት በሲና ምድረ በዳ በሚጓዙበት ወቅት የሚበላ ዳቦና የሚጠጣ ውኃ ሲያጡ ወደ ሙሴ ይጮኹ ነበር፡፡ ሙሴም የሕዝቡን ችግር ለእግዚአብሔር እያሰማ ሕዝቡ ማግኘት የፈለጉትን ያሰጣቸው ነበር፡፡ በዚሁ መሠረት አንድ ቀን የእስራኤል ልጆች እጅግ ጎምጅተው «የምንበላው ሥጋ ማን ይሰጠና? በግብፅ ሳለን ያለዋጋ ዓሣውንም፣ ዱባውንም፣ በጢሁንም፣ ነጭ ሽንኩርቱንም፣ ቀይ ሽንኩርቱንም እንደ ልብ እንበላ ነበር፡፡ አሁን ግን ሰውነታችን ደረቀች፣ ዐይናችንም ከዚህ መና በቀር የሚያየው የለም» ብለው አጉረመረሙ፡፡


በዚህ ጊዜ እግዚአብሔር ሙሴን ጠርቶ ከሕዝቡ ሰባ ሽማግሌዎችን የሕዝቡ አለቆችና ሸማግሌዎች ይሆኑ ዘንድ መርጦ ወደ መገናኛው ድንኳን እንዲያቀርባቸው አዘዘው፡፡ ሙሴም እግዚአብሔር እንዳዘዘው ሰባዎቹን ሰዎች ከሕዝቡ መርጦ ወደ ማደሪያው ድንኳን አቀረባቸው፡፡ እግዚአብሔርም ለሙሴ ከሰጠው መንፈስ ወስዶ በእነርሱ አሳደረባቸው፡፡ መንፈስም
/መንፈስ ቅዱስ/ በሰባው ሰዎች ላይ ባደረ ጊዜ ትንቢት ተናገሩ፡፡ በዚያው ወቅትም ከሰባው ጋር ተመርጠው ወደ ድንኳኑ ሳይመጡ በሕዝቡ ሰፈር የቀሩ ኤልዳድና ሞዳድ የተባሉ ሰዎች ነበሩ፡፡ መንፈስም ባሉበት ወረደባቸው፡፡ እነርሱም ትንቢትን ተናገሩ፡፡ ከዚያ በኋላ ከእነዚህ ሰባ ሁለት ሽማግሌዎች ጋር ሙሴ የሕዝቡን ችግር እንዲሸከም ታዘዘ፡፡ ከዚያም እግዚአብሔር ከእነዚህ ሰባ ሁለት ሽማግሌዎች /72 ሊቃናት/ ፊት በሙሴ አማካይነት ለእስራኤል ልጆች ሥጋ አዘነበላቸው፤/ዘኁል.11፥115/፡፡

በመሆኑም የእነዚያ ሰባ ሁለት ሽማግሌዎችና የሙሴ በማደሪያው ድንኳን መሰብሰብና የመንፈስ ስጦታን መቀበል በዘመነ ሐዲስ ከተደረጉት የቅዱስ ሲኖዶስ ጉባኤዎች ጋር የሚመሳሰል ነው፡፡ ኢያሱም ከሙሴ ዕረፍት በኋላ ሕዝበ እስራኤልን ለመምራት እንዲችል በእግዚአብሔር ትእዛዝ ሙሴ ኢያሱን በማኅበሩ ሁሉ ፊት /በጉባኤ ፊት/ በአንብሮተ እድ እንደሾመው መጽሐፍ ይነግረናል፤ /ዘኁል.27፥1523/፡፡ ስለሆነም የኢያሱ በጉባኤው ፊት መሾም ሰባቱን ዲያቆናት በአንብሮተ እድ ከሾሙት ከሐዋርያት ጉባኤ ጋር የሚመሳሰል ነው፤ /ሐዋ.6፥16/፡፡

እንደዚሁም በመጽሐፈ ነገሥት ካልዕ በምዕራፍ 2፥12 እና በምዕራፍ 4፥30 ላይ እንደተገለጸው፤ ደቂቀ ነቢያት በነቢዩ በኤልሳዕ ፊት ያደረጉት ስብሰባ ከቅዱስ ሲኖዶስ ስብሰባ ጋር የሚመሳሰል ነው፡፡ ስለዚህ በዘመነ ሐዲስ ቅዱሳን ሐዋርያት ካደረጉት የቅዱስ ሲኖዶስ ስብሰባ በፊት በዘመነ ብሉይ በሕዝበ እስራኤል መካከል የተከሰተውን ችግር ለማስወገድና ሕዝበ እስራኤንም በጉባኤ ውሳኔ ለመምራት ቅዱስ ሲኖዶስን የመሰሉ ስብሰባዎች መደረጋቸውን በአጭሩ ለማስረዳት ተሞክሮአል፡፡

ሲኖዶስ ዘቅዱሳን ሐዋርያት

የቤተክርስቲያን ታሪክ እንደሚያስረዳን የክርስቶስን ቤተክርስቲያን በቅዱስ ሲኖዶስ መምራት የጀመሩት ቅዱሳን ሐዋርያት ናቸው፡፡ ቅዱሳን ሐዋርያት ሐዋርያዊ አገልግሎታቸውን በሥምረት ለመምራት በዘመናቸው የተለያዩ ጉባኤዎችን እንዳደረጉ መጽሐፍ ቅዱስ ይነግረናል፡፡ ይኸውም በአስቆሮታዊው ይሁዳ ምትክ ሌላ ሐዋርያ ለመምረጥ ያደረጉት ስብሰባ ነው፡፡ ይኸውም ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ከሞተና ከተቀበረ በኋላ በሦስተኛውም ቀን ከሙታን ተለይቶ ከተነሣ በኋላ ቅዱስ ሉቃስ እንደመሰከረው ለደቀመዛሙርቱ አርባ ቀን እየተገለጸላቸው፣ ስለእግዚአብሔር መንግሥትም እየነገራቸው /እያስተማራቸው/ በብዙም ማስረጃ ከሕማማቱ በኋላ ሕያው ሆኖና ከሙታን ተለይቶ መነሣቱን ለእነርሱ እየታያቸው ቆየ /ሐዋ.1፥1-4/፡፡

ስለ እርሱ የተጻፉትንም መጻሕፍት ያስተውሉ ዘንድ አእምሮአቸውን ከፈተላቸው፡፡ እንዲህም አላቸው፣ «ክርስቶስ መከራ ይቀበላል፣ በሦስተኛውም ቀን ከሙታን ተለይቶ ይነሣል፣ በስሙም ንስሐና ኃጢአት ስርየት ከኢየሩሳሌም ጀምሮ ለአሕዛብ ሁሉ ይሰበካል» ተብሎ እንዲሁ ተጽፎአል፡፡ እናንተም ስለዚህ ምስክሮቼ ናችሁ፡፡ እነሆም «አባቴ የሰጠውን ተስፋ እኔ እልክላችኋለሁ፣ እናንተ ግን ከላይ ኃይልን እስክትለብሱ ድረስ በኢየሩሳሌም ከተማ ቆዩ ብሎ አዘዛቸው፡፡ ከዚያም ወደ ቢታንያ ወደ ደብረ ዘይት አወጣቸው፣ እጆቹንም አንሥቶ ባረካቸው፣ ሲባርካቸውም ከእነርሱ ተለየ፣ ወደ ሰማይም ዐረገ» /ሉቃ.24፥41-53/፡፡ እነርሱም ጌታ ወዳረገበት ወደ ሰማይ ትኩር ብለው ሲመለከቱ ሳሉ እነሆ ነጫጭ ልብስ የለበሱ ሁለት ሰዎች /ሁለት መላእክት/ በአጠገባቸው ቆሙ፡፡ ደግሞም እንዲህ አሉአቸው «እናንተ የገሊላ ሰዎች ሆይ ወደ ሰማይ ትኩር ብላችሁ እየተመለከታችሁ ስለምን ቆማችሁ? እነሆ ይህ ከእናንተ ወደ ሰማይ የወጣው ኢየሱስ ወደ ሰማይ ሲያርግ እንዳያችሁ እንዲሁ ይመጣል» ሲሉ ነገሩአቸው፡፡ /ሐዋ.1፥6-11/፡፡

ሐዋርያትም ሰገዱለትና በብዙ ደስታ ከደብረ ዘይት ወደ ኢየሩሳሌም ተመለሱ፡፡ ከዚያም ዘወትር እግዚአብሔርን እያመሰገኑና እያወደሱ /እየባረኩ/ በመቅደስ /በጽርሐ ጽዮን/ ኖሩ /ሉቃ.24፥50/፡፡ በአንድነት ተሰብስበው ሳሉ በአጠቃላይ መቶ ሃያ ሰዎች ያህል ባሉበት ቅዱስ ጴጥሮስ ተነሥቶ በይሁዳ ቦታ ሌላ ሰው መተካት እንዳለበት ንግግር አደረገ፡፡ «ወንድሞች ፥ሆይ፣ ኢየሱስን ለያዙት መሪ ስለሆናቸው ስለ ይሁዳ መንፈስ ቅዱስ አስቀድሞ በዳዊት አፍ የተናገረው ይፈጸም ዘንድ የተገባ ሆነ፤ እርሱም ከእኛ ጋር ተቆጥሮ ነበርና፣ ለዚህም ሐዋርያዊ አገልግሎት ታድሎ ነበርና» ብሎ በመናገር ስለ አስቆሮቱ ሰው ስለ ይሁዳ ዐመፅና አሟሟት ገለጻ አደረገ፡፡ ከዚያም ይሁዳን ስለሚተካው ሰው አስመልክቶ «ከዮሐንስ ጥምቀት ጀምሮ ከእኛ ዘንድ እስካረገበት ቀን ድረስ ጌታ ኢየሱስ በእኛ መካከል በገባበትና በወጣበት ዘመን ሁሉ እኛ ጋር አብረው ከነበሩት ሰዎች፣ ከእነዚህ አንዱ ከእኛ ጋር የትንሣ ኤው ምስክር ይሆን ዘንድ ይገባል» ብሎ ገለጸ፡፡

ወዲያውም በጉባኤው ስምምነት መሠረት የመቶ ሃያው ማኅበር አባላት ከነበሩት መካከል በርያስ የተባለውን ዮሴፍንና ማትያስን፣ሁለቱን በመካከል አቆሙአቸው፡፡ ስለ እነርሱም ሲጸልዩ፤ «የሁሉን ልብ የምታውቅ አንተ ጌታ ሆይ፣ ይሁዳ ወደ ገዛ ራሱ ይሔድ ዘንድ በተዋት በዚህች አገልግሎትና ሐዋርያነት ቦታን እንዲቀበል የመረጥኸውን ከእነዚህ ከሁለቱ አንዱን ሹመው» ብለው ጸለዩ፡፡ ቀጥሎም ዕጣ ተጣጣሉላቸው፤ ዕጣውም ለማትያስ ወደቀ /ወጣ/፡፡ እርሱም ዐሥራ አንዱ ሐዋርያት ጋር ተቆጠረ» /ሐዋ.1፥15-26/፡፡

ማትያስን መርጠው እግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስ እንዲሾመው ከጸለዩ በኋላ ቁ ሩ ከሰብዐ ሁለቱ አርድእት ውስጥ የነበረው ረድእ ማትያስ በእግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስ ተሹሞ ከቀሩት ሐዋርያት ጋር ገብቶ ተቆጠረ፡፡ በዚህ ሁኔታ ሁሉም በአንድ ልብ ሆነው ከአርያም /ከሰማይ/ የሚላክላቸውን ኃይል ማለት ጸጋ መንፈስ ቅዱስን ደጅ እየጠኑና እየተጠባበቁ በጽርሐ ጽዮን ተሰብስበው እግዚአብሔርን እያመሰገኑ ሰነበቱ፡፡ በዓለ ሃምሳም የተባለው ቀን በደረሰ ጊዜ ጌታ ባረገ በዐሥረኛው ቀን ሁሉም በአንድነት አብረው እየጸለዩ ሳለ ድንገት እንደሚነጥቅ አውሎ ነፋስ ከሰማይ ወደ እነርሱ ድምፅ መጣ፡፡ ተቀምጠው የነበሩበትንም ሁሉ ሞላው፤ እንደ እሳትም የተከፋፈሉ ልሳኖች /የእሳት ላንቃ/ የመሰሉ ታዩአቸው፤ በእያንዳንዳቸውም ላይ ተቀመጠባቸው፣ መንፈስ ቅዱስም ይናገሩ ዘንድ እንደሰጣቸው በልዩ ልዩ ልሳኖች ይናገሩ ጀመር፤ /ሐዋ.2፥1-5/፡፡

በዚህ ጊዜ ጌታችን ከትንሣ ኤው በፊት «እኔ በአብ ዘንድ የምልክላችሁ አጽናኝ /ጰራቅሊጦስ/ ከአብ የሚወጣ /ዘይሠርጽ/ የጽድቅ /የእውነት/ መንፈስ በመጣ ጊዜ ስለ እኔ ይመሰክራል፣ እናንተም ደግሞ ከመጀመሪያ ጀምሮ ከእኔ ጋር ኖራችኋልና ትመሰክራላችሁ» ብሎ የተናገረው ተስፋ ተፈጸመ፡፡ ደግሞም ወደ ሰማይ በሚያር ግበት ወቅት «እነሆ አባቴ የሰጠውን ተስፋ እኔ እልክላችኋለሁ፣ እናንተ ግን ከላይ ኃይል እስክትለብሱ ድረስ በኢየሩሳሌም ከተማ ቆዩ» ሲል የሰጠው ሰማያዊ ተስፋ ተፈጸመ፤ /ሉቃ.24፥49፤ሐዋ.2፥43/፡፡

ከዚህ በላይ እንዳየነው ከበዓለ ሃምሳ ዋዜማ ጀምሮ በኢየሩሳሌም በጽርሐ ጽዮን የተካሔደው የመጀመሪያው የሐዋርያትና የሰብዓ አርድእት ጉባኤ እጅግ በጣም ታላቅ ጉባኤ ስለነበረ የመጀመሪያው የሐዋርያት ሲኖዶስ ሊባል ይገባዋል፡፡ ምክንያቱም፦

1. ቅድስተ ቅዱሳን ድንግል ማርያም የነበረችበት ጉባኤ በመሆኑ፤
2. ቅዱስ ማትያስን የመረጠና የሾመጉባኤ በመሆኑ፤
3. ለሐዋርያትና ከእነሱ ጋር በጸሎት ተሰብስበው ለነበሩት ሁሉ ጸጋ መንፈስ ቅዱስ የወረደበት ጉባኤ በመሆኑ፤
4. በዚያው ቀን የመንፈስ ቅዱስ ጸጋ በመውረዱ ምክንያት በሐዋር ያት ስብከት ሦስት ሺሕ የሚያህል ሕዝብ በኢየሱስ ክርስቶስ አምኖ የቤተክርስቲያን አባል የሆነበት ቀን በመሆኑ ጉባኤው የቤተክርስቲያን የመጀመሪያ ሲኖዶስ ተብሎ ሊጠራ ይገባል፡፡ በመሆኑም  ቤተክርስቲያን ታሪክ የቅዱስ ሲኖዶስ ታሪካዊ አመሠራረት ከዚህ ቀዳሚው ጉባኤ መሆኑ የሚያከራክር አይደለም፡፡ በሌላ መንገድም በቤተክርስቲያን ታሪክ እንደተመዘገበው ከሦስተኛው መቶ ክፍለ ዘመን ጀምሮ በየጊዜው በተለያዩ ቦታና ዘመን የተደረጉ የአህጉረ ስብከት /Regionsl or local/ ሲኖዶሶችና በዓለም አቀፍ ደረጃ የተደረጉ ሲኖዶሶች መሠረታቸው የኢየሩሳሌሙ የመጀመሪያው የሐዋርያት ጉባኤ ነው ቢባል እርግጥ ነው፡፡

ሁለተኛው የሐዋርያት ሲኖዶስ

ሁለተኛው የሐዋርያት ሲኖዶስ ተብሎ ሊጠራ የሚገባው ጉባኤ፤ ራሳቸው ሐዋርያት ተሰብስበው የቤተክርስቲያን አገልጋዮችን በአንብሮተ እድየሾሙት ዐቢይ ሲኖዶስ ተደርጎ እንደነበረ መጽሐፍ ያረጋግጥልናል፡፡ ዐሥራ ሁለቱ ሐዋርያት /ደቀመዛሙርት/ ምእመናንን በሙሉ ጠርተው፤ «እኛ የእግዚአብሔርን ቃል /ወንጌልን/ ትተን ማዕድን እናገለግል ዘንድ የሚገባ ነገር አይደለም፡፡ ወንድሞች ሆይ በመልካም የተመሰከረላቸውን፣ መንፈስ ቅዱስና ጥበብም የሞላባቸውን ሰባት ሰዎች ከእናንተ ምረጡ፣ ለዚህም ጉዳይ እንሾማቸዋለን፣ እኛ ግን ለጸሎትና ቃሉን ለማገልገል እንተጋለን» ብለው ገለጹላቸው፡፡ ይህም ቃል /ንግግር/ ሕዝቡን ሁሉ ደስ አሰኛቸው፡፡ ስለዚህም እምነትና መንፈስ ቅዱስም የመላበትን ሰው እስጢፋኖስን፣ ፊልጶስንም ጵሮኮ ሮስንም፣ ኑቃሮናንም ጰርሜናንም መረጡ፡፡ በሐዋርያትም ፊት አቆሙአቸው ሐዋርያት ከጸለዩ በኋላ እጃቸውን ጫኑባቸው /ሐዋ. 6፥1-7/፡፡

ከላይ እንደተገለጸው ዐሥራ ሁለቱ ሐዋርያት ከአርድእትና ከምእመናኑ ጋር ተሰብስበው ከተወያዩ በኋላ፤ ሐዋርያት በወሰኑት ውሳኔ ሕዝቡ በሙሉ ተደስተው ሰባቱን የቤተክርስቲያን አገልጋዮች መርጠው ዐሥራ ሁለቱ ሐዋርያት አቅርበው የሾሙት ጉባኤ በመሆኑም ጉባኤው ከወሰነው ታላቅ ቁም ነገር የተነሣ  «ሲኖዶስ» ተብሎ ሊጠራ ይችላል፡፡ ነገር ግን እንደሚታወቀው በቤተ ክርቲያን ታሪክ መሠረት በተለምዶ የመጀመሪያው የቤተክርስቲያን ጉባኤ ወይም የመጀመሪያው ሲኖዶስ ተብሎ የሚጠራው በኢየሩሳሌም 50/51 ዓ.ም የተደረገው ጉባኤ ነው፡፡

ሦስተኛው የሐዋርያት ሲኖዶስ

ይህ በኢየሩሳሌም የተደረገው ሦስተኛው የሐዋርያት ጉባኤ ቅዱስ ሲኖዶስ ተብሎ ሊጠራ ይገባል፡፡ ነገር ግን በተለምዶ የመጀመሪያው የሐዋርያት ጉባኤ /ሲኖዶስ/ እየተባለ መጠራቱ ሁሉም የሚያውቀው ነው፡፡ ጉባኤው ሊደረግ የተፈለገበት ዋና ምክንያት የሚከተለው ነው፡፡ በሐዋርያት ዘመን በአንጾኪያ ከተማ በነበረችው ቤተክርስቲያን ነቢያትና መምህራን ነበሩ፡፡ እነርሱም በርናባስ፣ ኔጌር የተባለው ስምዖን፣ የቀሬናው ተወላጅ ሉክዮስ፣ የአራተኛው ክፍል ገዥ የነበረው የሄሮድስ ባለሟል ምናሔና ሳውል እነዚህ ሁሉ ጌታን እያመለኩና እየጾሙ ሳለ መንፈስ ቅዱስ፤ «በርናባስንና ሳውልን ለጠ ራኋቸው ሥራ ለዩልኝ፤ ፍልጥዎሙ ሊተ ለበርናባስ ወለሳውል ለገብር ዘፈቀድክዎሙ» አላቸወ፡፡ እነርሱም መንፈስ ቅዱስ እንደነገራቸው አደረጉ፡፡ ከጾሙ ከጸለዩና እጃቸውንም ከጫኑ በኋላ አሰናበቱአቸው   /ሐዋ.13፥1-3/፡፡

ከዚያም ጳውሎስ በርናባስና ማርቆስ ከሌሎቹ ጋር ወደ ቦታው ሁሉ እየዞሩ ወንጌልን ሰበኩ፡፡ በየሰንበቱም በአይሁድ ምኩራብ እየተገኙ ስለ ኢየሱስ ክርስቶስ አዳኝነትና ስለ ትንሣ ኤው ይሰብኩ ነበር፡፡ እንደዚሁም በልስጥራ፣ በደርቤን፣ በጲስድያ፣ በጵንፍልያ፣ በጴርጋሞን፣ በጵርሄንም የእግዚአብሔርን ቃል /ወንጌልን/ እየሰበኩ ሕዝቡን ያጽናኑ ነበር፡፡ አንጾኪያም በደረሱ ጊዜ ቤተክርስቲያንን /ምእመናንን/ ሰብስበው እግዚአብሔር ከእነርሱ ጋር ያደረገውን ሁሉ ለአሕዛብም የሃይማኖት ደጅ አንደተከፈተላቸው ተናገሩ፡፡
ነገር ግን በዚያን ጊዜ አንዳንዶች ከይሁዳ ሀገር ወደ አንጾኪያና ወደ ሌሎቹ አውራጃዎች ወረዱና «እንደሙሴ ሥርዓት ካልተገረዛችሁ ትድኑ ዘንድ አትችሉም» እያሉ ወንድሞችን /ምእመናንን/ ያስተምሩ ጀመር፡፡ በዚያን ጊዜ በእነዚያ ሰዎች በጳውሎስና በበርናባስ መካከል ብዙ ጠብናክርክር ተፈጠረ፡፡ ጠቡና ክርክሩ እያየለ በሔደ ጊዜ ጳውሎስ፣ በርናበስና ከእርሱ ጋር የነበሩ የወንጌል አገልጋዮች ተነጋግረው ወደ ሐዋርያት ለመሔድ ወሰኑ፡፡ ወደ ኢየሩሳሌምም በደረሱጊዜ ቤተክርስቲያን /ምእመናን/ ሐዋርያትና ቀሳውስት /Aposstles and the elders/ ተቀበሉአቸው፡፡ እነ ጳውሎስም በዞሩባቸው አህጉረ ስብከት ሁሉ ያደረጉትን /የፈጸሙትን/የወንጌል አገልግሎትና የገጠማቸውን ችግር ሁሉ በዝርዝር ሪፖርት አቀረቡ፡፡ በዚያን ጊዜ በጌታ ካመኑት ከፈሪሳውያን ወገን የሆኑት ሰዎች ተነሥተው «ትገርዙአቸው ዘንድና የሙሴንሕግ እንዲጠብቁ ታዝዙአቸው ዘንድ ይገባል» ብለው ለሐዋርያት ተናገሩ፡፡ እነሆም በዚያን ጊዜ ሐዋርያትናቀሳውስት /Apostles and the elders/ ለመመካከርና ለመወሰን በአንድነት ተሰበሰቡ፡፡ የዚህ ዐቢይ ሲኖዶስ ሰብሳቢ /ሊቀመንበርም/ ቅዱስ ያዕቆብ ኤጲስ ቆጶስ ዘኢየሩሳሌም እንደነበር በቤተክርስቲያን ታሪክ ተገልጿል፡፡ በጉባኤውም በቀረበው ጉዳይ ላይ ቅዱስ ጴጥሮስ የመጀመሪያውን ንግግር አደረገ፡፡ ከቅዱስ ጴጥሮስ ንግግር በኋላም ጳውሎስና በርናባስ ተነሥተው እግዚአብሔር በእጃቸው በአሕዛብ መካከል ያደረገውን ምልክትና ድንቅ ነገር ሁሉ ለሲኖዶሱ ተረኩ፡፡ ከዚያም የጌታ ወንድም እየተባለ የሚጠራው የኢየሩሳሌም ኤጲስ ቆጶስና የጉባኤው ሰብሳቢ ቅዱስ ያዕቆብ ንግግር አደረገ፡፡ ከቅዱስ ያዕቆብ ንግግር በኋላ
ሐዋርያትና ቀሳውስት /Apostles and the elders/ ከቤተክርስቲያኑ /ምእመናኑ/ሁሉ ጋር ከእነርሱ የተመረጡትን ሰዎች ከጳውሎስና ከበርናባስ ጋር ወደ አንጾኪያ ይልኩ ዘንድ ተስማሙ፡፡ ከእነ ጳውሎስ ጋር እንዲሔዱ የተመረጡትም በርስያን የተባለው ይሁዳናሲላስ ነበሩ፡፡ የጉባኤውም አባላት በጉባኤ የተወሰነውን ውሳኔ ጽፈው በተመረጡት ወንድሞች እጅ ላኩ፡፡ መልእክተኞቹም ተሰናብተው ወረዱ፤ ሕዝቡንም ሰብስበው ከሐርያት ጉባኤ የተላከውን ደብዳቤ ሰጡአቸው፡፡ ባነበቡትም ጊዜ ከምክሩ የተነሣ  ደስ አላቸው፡፡ ይሁዳና ሲላስም ደግሞ ነቢያት ነበሩና ወንድሞችን በብዙ ቃል መክረው አጽናኑአቸው፡፡ አያሌ ቀንም ከእነርሱ ጋር ከተቀመጡ በኋላ ከወንድሞቻቸው በሰላም ተሰና ብተው ወደ ሐዋርያት ተመለሱ፡፡ ቤተክርስቲያን ሐዋርያዊትና ሲኖዶሳዊት ለመሆንዋ ተደጋግሞየተነገረ ነው፡፡ በመንፈስ ቅዱስ የተመሩ ቅዱሳን ሐዋርያት ቤተክርስቲያንን በስብከተ ወንጌል ስለአሰባሰቡና ስለአጠናከሩ ቤተክርስቲያን በሲኖዶስ እየተመራች ከዚህ ዘመን በመድረስዋ ሲኖዶሳዊት /ጉባኤያዊት/ እየተባለች ትጠራለች፡፡

ከቅዱሳን ሐዋርያት ቀጥለው የተነሡት አባቶችም ቤተክርስቲያንን በሚመሩበት ወቅት፡-
ሀ. የቤተክርስቲያንን ቅዱሳት መጻሕፍት ከመናፍቃን መጻሕፍት ለመለየትና ቁጥራቸውን
    በቀኖና /በሕግ/ ለመወሰን፤
ለ. ሥርዐተ ቅዳሴንና ሥርዐተ ጸሎትን በቀኖና /በሕግ/ ለመመደብ፤
ሐ. አጽዋማትንና በዓላትንም ለመወሰን የሲኖዶስ ስብሰባ በማድረግ ከላይ የተዘረዘሩትን ሁሉ ወስነዋል፡፡ በሌላ በኩልም ከመጀመሪያው ክፍለ ዘመን ጀምሮ በየጊዜው መናፍቃን /ሐራ ጥቃዎች/ በተነሡ ጊዜ ቅዱሳን የቤተክርስቲያን አባቶች ርትዕት፣ ስብሕት /ኦርቶዶክስ/ ሃይማኖትን ለመጠበቅ ሐራጥቃዎችን በቀኖናዋ ውግዘት ለማስወገድ በሲኖዶስ እየተሰበሰቡ ይወስኑ ነበር፡፡ በዚህ መሠረት ከሦስተኛው ክፍለ ዘመን አጋማሽ ጀምሮ በየሀገሩ የአካባቢ ሲኖዶሶች /Regional or Local synods/ ተደርገዋል፡፡ ከተደረጉት ሲኖዶሶችም ለአብነት ጥቂቶቹን ቀጥለን እንመለከታለን

1.    በ257ዓ.ም በካርቴጅ የተደረገው ሲኖዶስ፡- በዚህ የአካባቢ /regional/ ሲኖዶስ ሰማንያ አራት ኤጲስ ቆጶሳት ተሳትፈዋል፡፡ የሲኖዶሱ ሰብሳቢ ቅዱስ ሲፕሪያኖስ ነበር፡፡ በዚህ ጉባኤ ሥርዓተ ጥምቀትንና መናፍቃንን፣ ቅዱሳት መጻሕፍትንና የኤጲስ ቆጶሳትን ሥልጣን የተመለከቱ ቀኖናዎች ተወስነዋል፡፡
2.    268 – 270 ዓ.ም በተከታታይ በአንጾኪያ ሲኖዶስ ተደርጎአል፡፡ በዚህ ሲኖዶስ ዐሥራ አራት ኤጲስ ቆጶሳት ተሰብስበው በምስጢረ ሥጋዌ የኅድረትንና የፅምረትን /ምንታዌ አካላትን/ ትምህርት ማስፋፋት የሞከረውን ኤጲስ ቆጶስ ጳውሎስ ሳምሳጢን መክረው አልመለስ ስላለ አውግዘው ከቤተክርስቲያን ለይተውታል፡፡
3.    በዚሁ ዓይነት በአንካራ በ314 ዓ.ም ፣በጋንግራ 365 ዓ.ም፣ በሳርዲካ በ343ዓ.ም፣ በአንጾኪያ በድጋሚ በ341 ዓ.ም፤ በላኦዶቂያ በ334 እና በ381 ዓ.ም የተጠራው ሲኖዶስ ስድሣ  ቀኖናዎችን ዐውጆአል፡፡ እንደዚሁም በድጋሚ በካርቴጅ በ419 ዓ.ም የተሰበሰበው ሲኖዶስ )138 ቀኖናዎችን ዐውጆአል፡፡ ይህ ሲኖዶስ «የአፍሪካ ኤጲስ ቆጶሳት ሲኖዶስ» በሚል መጠሪያ ይታወቃል፡፡
በአጠቃላይ ከሐዋርያት በኋላ የተነሡ ሐዋርያውያነ አበው /Apostolic Fatheres/ የቤተክርስቲያንን አስተዳደርና የቤተክርስቲያንን ችግር በሲኖዶስ እየተሰበሰቡ በመመርመርና አስፈላጊውንም በመወሰን ቤተክርስቲያንን መርተዋል፡፡ ያውም ከሰባ ዓ.ም ጀምሮ እስከ 313 ዓ.ም ድረስ የነበረው ጊዜ አሕዛብ በቁር የበዙ በትና በመንግሥት አስተዳደርም አጠቃላይ ሥልጣን ግን የጨበጡበት ዘመን ስለነበረ፤ በዚህ ዘመን ከፀረ እግዚአብሔርና ከፀረ ክርስትና ኃይሎች ጋር በመጋደል በብዙ ሺሕ የሚቆጠሩ ክርስቲያኖች ስለ ሀልዎተ እግዚአ ብሔርና ኦርቶዶክሳዊ ሃይማኖታቸው መሥዋዕት ሆነው የተሰውበት ዘመን ነበር፡፡ በመሆኑም ዘመኑ ዘመነ ሰማዕታት እየተባለ ይጠራል፡፡

ከቅዱሳን ሐዋርያት ቀጥለው የተነሡት አባቶችም ቤተክርስቲያንን በሚመሩበት ወቅት፡-
ሀ. የቤተክርስቲያንን ቅዱሳት መጻሕፍት ከመናፍቃን መጻሕፍት ለመለየትና ቁጥራቸውን
    በቀኖና /በሕግ/ ለመወሰን፤
ለ. ሥርዐተ ቅዳሴንና ሥርዐተ ጸሎትን በቀኖና /በሕግ/ ለመመደብ፤
ሐ. አጽዋማትንና በዓላትንም ለመወሰን የሲኖዶስ ስብሰባ በማድረግ ከላይ የተዘረዘሩትን ሁሉ ወስነዋል፡፡ በሌላ በኩልም ከመጀመሪያው ክፍለ ዘመን ጀምሮ በየጊዜው መናፍቃን /ሐራ ጥቃዎች/ በተነሡ ጊዜ ቅዱሳን የቤተክርስቲያን አባቶች ርትዕት፣ ስብሕት /ኦርቶዶክስ/ ሃይማኖትን ለመጠበቅ ሐራጥቃዎችን በቀኖናዋ ውግዘት ለማስወገድ በሲኖዶስ እየተሰበሰቡ ይወስኑ ነበር፡፡ በዚህ መሠረት ከሦስተኛው ክፍለ ዘመን አጋማሽ ጀምሮ በየሀገሩ የአካባቢ ሲኖዶሶች /Regional or Local synods/ ተደርገዋል፡፡ ከተደረጉት ሲኖዶሶችም ለአብነት ጥቂቶቹን ቀጥለን እንመለከታለን

1.    በ257ዓ.ም በካርቴጅ የተደረገው ሲኖዶስ፡- በዚህ የአካባቢ /regional/ ሲኖዶስ ሰማንያ አራት ኤጲስ ቆጶሳት ተሳትፈዋል፡፡ የሲኖዶሱ ሰብሳቢ ቅዱስ ሲፕሪያኖስ ነበር፡፡ በዚህ ጉባኤ ሥርዓተ ጥምቀትንና መናፍቃንን፣ ቅዱሳት መጻሕፍትንና የኤጲስ ቆጶሳትን ሥልጣን የተመለከቱ ቀኖናዎች ተወስነዋል፡፡
2.    268 – 270 ዓ.ም በተከታታይ በአንጾኪያ ሲኖዶስ ተደርጎአል፡፡ በዚህ ሲኖዶስ ዐሥራ አራት ኤጲስ ቆጶሳት ተሰብስበው በምስጢረ ሥጋዌ የኅድረትንና የፅምረትን /ምንታዌ አካላትን/ ትምህርት ማስፋፋት የሞከረውን ኤጲስ ቆጶስ ጳውሎስ ሳምሳጢን መክረው አልመለስ ስላለ አውግዘው ከቤተክርስቲያን ለይተውታል፡፡
3.    በዚሁ ዓይነት በአንካራ በ314 ዓ.ም ፣በጋንግራ 365 ዓ.ም፣ በሳርዲካ በ343ዓ.ም፣ በአንጾኪያ በድጋሚ በ341 ዓ.ም፤ በላኦዶቂያ በ334 እና በ381 ዓ.ም የተጠራው ሲኖዶስ ስድሣ  ቀኖናዎችን ዐውጆአል፡፡ እንደዚሁም በድጋሚ በካርቴጅ በ419 ዓ.ም የተሰበሰበው ሲኖዶስ )138 ቀኖናዎችን ዐውጆአል፡፡ ይህ ሲኖዶስ «የአፍሪካ ኤጲስ ቆጶሳት ሲኖዶስ» በሚል መጠሪያ ይታወቃል፡፡
በአጠቃላይ ከሐዋርያት በኋላ የተነሡ ሐዋርያውያነ አበው /Apostolic Fatheres/ የቤተክርስቲያንን አስተዳደርና የቤተክርስቲያንን ችግር በሲኖዶስ እየተሰበሰቡ በመመርመርና አስፈላጊውንም በመወሰን ቤተክርስቲያንን መርተዋል፡፡ ያውም ከሰባ ዓ.ም ጀምሮ እስከ 313 ዓ.ም ድረስ የነበረው ጊዜ አሕዛብ በቁር የበዙ በትና በመንግሥት አስተዳደርም አጠቃላይ ሥልጣን ግን የጨበጡበት ዘመን ስለነበረ፤ በዚህ ዘመን ከፀረ እግዚአብሔርና ከፀረ ክርስትና ኃይሎች ጋር በመጋደል በብዙ ሺሕ የሚቆጠሩ ክርስቲያኖች ስለ ሀልዎተ እግዚአ ብሔርና ኦርቶዶክሳዊ ሃይማኖታቸው መሥዋዕት ሆነው የተሰውበት ዘመን ነበር፡፡ በመሆኑም ዘመኑ ዘመነ ሰማዕታት እየተባለ ይጠራል፡፡

ዓለም አቀፍ ሲኖዶሶች

ከዚህ በላይ ለማየት እንደተሞ ከረው በአካባቢ በሚገኙት አብያተ ክርስቲያናት ዙሪያ ወይም ውስጥ የቀኖና ወይም የዶግማ ችግሮች ሲከሰቱ በአቅራቢያ ሀገሮች ከሚገኙ ኤጲስ ቆጳሳት ሲኖዶሶች እየተጠሩ ለተነሡት ችግሮች መፍትሔ ይሰጡ ነበር፡፡

ነገር ግን በአካባቢ በሚደረጉት ሲኖዶሶች የማይፈቱ ከሆኑ በዚያኑ ጊዜ ዓለም አቀፍ ከሚባለው የዓለም ሊቃነ ጳጳሳትና ኤጲስ ቆጶሳት የጋራ የሆነ ዐቢይ ዓለም አቀፍ ጉባኤ /Ecumerical council/ እያደረጉ ችግሮቹን በመመርመር መፍትሔ ይሰጡ ነበር፡፡

የመጀመሪያው የኒቂያ ዓለም አቀፍ ሲኖዶስ በ325ዓ.ም ኒቂያ በተባለች ከተማ ከመደረጉ በፊት አርዮስና ኑፋቄአዊ ትምህርቱን መርምሮ ውሳኔ ለመስጠት አርዮስ በኖረበትና በተነሣ በት ሀገር በእስክንድርያ በመጀመሪያ በ320 ዓ.ም፤ ቀጥሎም በ321 ዓ.ም ሲኖዶስ ተደረገ፡፡ የዚያሲኖዶስ ሰብሳቢ የእስክንድርያ ሊቀ ጰጳስ የነበረው እለ እስክንድሮስ ዘእስክንድርያ ነበር፡፡ ችግሩ በዚያ ዓይነት ይፈታል ተብሎ ቢሞከርም ሰባት መቶ ደናግል፣ ዐሥራ ሁለት ዲያቆናት፣ ስድስት ቀሳውስት /የደብር አለቆች/ ከሦስት የሚበልጡ ኤጲስ ቆጶሳት ትምህርቱን ተቀብለው አርዮስን ስለደገፉ አርዮስ በሲኖዶሱ ምክር ሊመለስ አልቻለም፡፡ ስለዚህ ከአራት ዓመት በኋላ በሊቀ ኤጲስ ቆጶሳት እለእስክንድሮስ አስተባባሪነት በንጉሠ ነገሥቱ በቆስጠንጢኖስ ተባባሪነት 318 አበው ሊቃነ ኤጲስ ቆጶሳት በኒቂያ ከተማ በ325 ዓ.ም የሲኖዶስ ስብሰባ አድርገው ከኑፋቄው አልመለስ ያለውን እልከኛውን አርዮስንና ትምህርቱን አውግዘው ሃይማኖትን አጸኑ፡፡ በመንፈስ ቅዱስ መሪነት በአንድ ልብ ሆነው «አንቀጸ ሃይማኖት /ጸሎተ ሃይማኖት/» የተባለውን የዶክትሪን ዐዋጅ አጸደቁ፡፡ ከሃያም ያላነሱ ቀኖናዎችን አጽድቀው አሠራጩ ፡፡

ከዚያም በመቀጠል ከሃምሳ ስድስት ዓመት በኋላ መንፈስ ቅዱስ ፍጹም አምላክ መሆኑን የካዱ መናፍቃን /ሐራጥቃዎች/ /heretics/ ተነሥተው በምሥራቅ በኩል የነበረችውን ቤተ ክርስቲያን ባስቸገሩ ጊዜ በቁስጥንጥንያ ከተማ በ381 ዓ.ም ከመላው ዓለም አንድ መቶ ሃምሳ አበው ሊቃነ ኤጲስ ቆጶሳት ተሰበሰቡ፡፡ «መንፈስ ቅዱስ ከአብና ከወልድ ያነሰ ነው /ሕጹጽ ነው/» ብለው የተነሡትን መቅዶን ዮስንና ተከታዮቹን ተመክረውና ተለምነው ከክሕደታቸው ስላልተ መለሱ አወገዙአቸው፡፡ ትምህርታቸውንም በማውገዝ ውሳኔ አሳለፉ፡፡ በመቀጠልም ቅዱሳት መጻሕፍትን በመመርኮዝ «መንፈስ ቅዱስ እንደ አብና እንደ ወልድ ፍጹም አምላክ መሆኑን፣ ጌታና ማኅየዊ እየተባለም ከአብና ከወልድ ጋር አንድ ባሕርይ ስለሆነ ከሁለቱ አካላት ጋር በአንድ መለኮት እንደ ሚመሰገንና እንደሚሰገድለት፤ እንዲሁም ከአብ ብቻ መሥረጹን ገልጸው ወሰኑ» ውሳኔውም ከኒቂያው አንቀጸ ሃይማኖት/ከጸሎተ ሃይማኖት/ ጋር ተጨምሮ እንዲጻፍ አደረጉ፡፡ በዚሁም መሠረት በአሁኑ ዘመን በመላው ዓለም በየቤተክር ስቲያኑ በተለያየ ቋንቋ የሚጸለየው ጸሎተ ሃይማኖት «የኒቂያ- ቁስጥ ንጥንያ አንቀጸ ሃይማኖት»/ Nicene-constantinople creed/ እየተባለ ይጠራል፡፡

ከቁስጥንጥንያው ዓለም አቀፍ ሲኖዶስ በኋላ ሃምሳ ዓመታት ቆይቶ ንስጥሮስ የተባለ መናፍቅ ተነሣ ፡፡ እሱም የቁስጥንጥንያ ትርያርክ ነበር፡፡ ከ426ዓ.ም ጀምሮ በቁስጥንጥንያ ምስጢረ ሥጋዌን በማፋለስ «ክርስቶስ ሁለት አካላት፣ ሁለት ገጻት፣ ሁለት በመስተጻምር /በሲናፊያ/ አንድ የሆኑ ባሕርያት ያሉት ነው» እያለ አስተማረ፡፡ በዚህም መርሖ መሠረት «ቃለ እግዚአብሔር /ሎጎስ/ እና ክርስቶስ በመስተፃመር /በሲናፊያ/ አንድ ስለሆኑ ክርስቶስ አንድ ነው» ብሎ አስተማረ፡፡

ከዚሁም አያይዞ «ድንግል ማርያም እግዚአብሔርን ልትወልድ አትችልም፤ ከእርስዋ የተወለደው ክርስቶስ ነው፡፡ ስለሆነም እርስዋን ወላዲተ ክርስቶስ እንጂ ወላዲተ እግዚአብሔር /ወላዲተ አምላክ/ አንላትም» በማለት አስተማረ፡፡ በዚሁ ችግር ምክንያት በ431 ዓ.ም ከመላው ዓለም አበው ሊቃነ ኤጲስ ቆጶሳትና ኤጲስ ቆጶሳት በኤፌሶን ተሰብስበው ሦስተኛውን ዓለም አቀፍ ሲኖዶስ አደረጉ፡፡

ንስጥሮስን ሦስት ጊዜ ጠርተውት አልቀርብም ስላለ የጻፋቸውን መልእክታት ተመልክተውና ስሙን ጠርተው አወገዙት፡፡ ክርስቶስንም «ወልድ ዋሕድ፣ ፍጹም  አምላክ፣ ፍጹም ሰው፣ ከሁለት ባሕርይ / ከመለኮትና ከትስብእት/ አንድ ባሕርይ፣ አንድ አካል» መሆኑን የሚያረጋግጡትን የቅዱስ ቄርሎስን መልእክታት ተቀብለው አጸደቁ፡፡ ቅድስት ድንግል ማርያምንም «በአማን ወላዲተ አምላክ» መሆንዋን አረጋገጡ፡፡

በሊቀ ኤጲስ ቆጶስ ዮሐንስ ዘአንጾኪያ እየተመራ ወደ ኤፌሶን የመጣው የአንጾኪያ ኤጲስ ቆጶሳት ቡድን ግን የንስጥሮስን ውግዘት ተቃወመ፡፡ በዚህ ምክንያት የአንጾኪያ ቤተክርስቲያን በኤፌሶን ከተሰበሰቡት የአብያተ ክርስቲያናት መሪዎች ተለየች፡፡ እስከ 433 ዓ.ም በእስክ ንድርያና በአንጾኪያ አብያተ ክርስቲያናት መካከል መለያየት ጠነከረ፤ የጠብ ግድግዳም ተመሠረተ፡፡ በ433 ዓ.ም ግን በንጉሠ ነገሥት ቴኦዶስዮስ ካልዕ አስታራቂነት ሁለቱም አብያተ ክርስቲያናት ታረቁ፡፡ በቅዱስ ቄርሎስ ዘእስክንደርያና በዮሐንስ ዘአንጾኪያ መካከልም ሰላም ተመሠረተ፡፡ በዚሁ ዕርቅ መሠረት አንጾኪያውያን አበው በኤፌሶን የተወሰነውን ውሳኔ ተቀበሉ፡፡ በንስጥሮስ መወገዝና መወገድም ተስማሙ፡፡ አንድነትም ተመሠረተ፡፡

ቅዱስ ቄርሎስ በ444 ዓ.ም ሲያርፍ በኋላ የሲኖዶሱ ዋና ጸሐፊ  የነበረው ዲዮስቆሮስ ዘእስክንድርያ ትርያርክ ሆኖ ተሾመ፡፡ ከጥቂት ዓመታት በኋላ በ488ዓ.ም ከቁስጥ ንጥንያ በሊቀ ኤጲስ ቆጶስ ፍላቭያን የሚመራ የአካባቢው ኤጲስ ቆጶሳት የተሳተፉበት ሲኖዶስ /Local Synods/ ተደረገ፡፡ ወደዚህም ሲኖዶስ አውጣኪ ተከሶ ቀረበና ተወገዘ፡፡ እርሱም ወደ ሮምና ወደ እስክንድርያ ትርያክ«አላግባብ ተወገዝሁ» ብሎ አቤቱታ ጻፈ፡፡

«የአውጣኪን ጉዳይ ለመመርመርና ተረፈ ንስጥሮሳውያንን ለማስወገድ» በሚል አጀንዳ ለሁለተኛ ጊዜ በ449 ዓ.ም በኤፌሶን ሲኖዶስ ተደረገ፡፡ በስብሰባውም አንድ መቶ ሠላሳ ስአምስት ኤጲስ ቆጶሳት ተሰበሰቡ፡፡ የሲኖዶሱ ሊቀ መንበር ትርያክ ዲዮስቆሮስ ሆነ፡፡ በአጀንዳው መሠረትጉዳዮች ተመረመሩ፡፡ አውጣኪንም መረመሩት፡፡ ሊቀ ኤጲስ ቆጶስ ፍላቭያኖንስና ፌኦዶሪትን ግን ጉባኤው መርምሮ መንፈቀ ንስጥሮሳውያን ሆነው ስላገኛቸው በጊዜያዊ ውግዘት ተቀጥተውና ታስረው እንዲቆዩ ተደረገ፡፡ የፖፕ ልዮን ጦማረ ሃይማኖትም ቀርቦ በዲዮስቆሮስና በሌሎች የጉባኤው አባላት ተመርምሮ ከንስጥሮስ ትምህርት ጋር ተዛምዶ ስለተገኘ በጦማሩና በጦማሩ ባለቤት ላይ ውግዘት አከል ተግሳጽ እንዲተላለፍባቸው ተደረገ፡፡ ፖፕ ልዮን ግን ይህንን ታሪክ ሰምቶ በዲዮስቆሮስ ጥርሱን ነከሰ፡፡

ጉባኤውንም «የወረበሎች ጉባኤ» /Synodd of listriks/ ብሎ ጠራው፡፡ ከዚህ ንዴት የተነሣ  በሁለተኛው ዓመት በ451 ዓ.ም በኬልቄዶን ጉባኤ እንዲደረግ ተወሰነ፡፡ በዚህ ጉባኤስድስት መቶ ሠላሳ ኤጲስ ቆጶሳት ተሰብስበው በልዮን መልእክተኞች እየተመሩ ቅዱስ ዲዮስቆሮስን ከንጉሡ ጋር ተሻርከው ከመንበሩ አወረዱት፡፡ ታስሮም በደሴተ ጋግሪ ሦስት ዓመት ተቀመጠ፡፡ ከዚያም እንዳለ በእስራትና በበሽታ ምክንያት 454 ዓ.ም ዐረፈ፡፡ከቅዱሳን ሐዋርያት ዘመን ጀምሮ እስከ አምስተኛው ክፍለ ዘመን አጋማሽ ድረስ ያየነው ታሪክ እንደሚያስረዳን ቅዱስ ሲኖዶስ የቤተክርስቲያን መሪ እንደሆነ ነው፡፡ ቤተክርስቲያንምከተጠቀሰው የመጀመሪያው ዘመን ጀምሮ እስካለንበት ዘመን ድረስ መለኮታዊ አገልግሎትዋን ስታካሒድ የኖረችው በመንፈስ ቅዱስ በሚመራው በቅዱስ ሲኖዶስ በመመራት ነው፡፡ በቤተክርስቲያናችን ትውፊት መሠረትም የሐዋርያትንና የአርድእት ቀኖናዎች የሊቃውንትም ጭምር ሲኖዶስ /መጽሐፈ ሲኖዶስ/ እየተባለ ይጠራል፡፡ ከዚህ በላይ እንደተ መለከትነውና እንደምናውቀው በአካባቢ የተነሡትን የሃይማኖትም ሆኑ የቀኖና ችግሮች በመጀመሪያ በአካባቢው ሀገሮች ባሉት ሊቃነ ኤጲስ ቆጶሳት ሲኖዶስ ወሳኝነት ይፈቱ ነበር፡፡ ከእነርሱም አቅም በላይ ሆነው የተገኙ ችግሮች ደግሞ «ዓለም አቀፍ ሲኖዶስ» /Ecumerical Synods/ እየተጠራ ሲወሰን እንደነበረ ተመልክተናል፡፡

ከዚያም ሌላ በየትኛውም ሀገር የምትገኘው የክርስቶስ ቤተክርስቲያን /Local Synods/ ከዘመነ ሐዋርያት ጀምሮ እስካለንበት ዘመን ድረስ አንድ ማእከል አንድ ሲኖዶስ ብቻ እንዳላት ተገንዝ በናል፡፡ ለምሳሌ የኢየሩሳሌም ቤተክርስቲያን በአንድ የኢየሩሳሌም ቅዱስ
ሲኖዶስ፣ የእስክንድርያ ቤተክርስቲያን በአንድ የእስክንድርያ ቅዱስ ሲኖዶስ፣ የቁስጥንጥንያ ቤተክርስቲያን በአንድ የቁስጥንጥንያ ቅዱስ ሲኖዶስ፣ የግሪክ ቤተክርስቲያን በአንድ የግሪክ ቅዱስ ሲኖዶስ ብቻ ሲመሩ መኖራቸውን እናውቃለን፡፡

ለአንዲት ነጻ ሀገር አንድ ርላ ሜነት /One Panriament/ ብቻ እንዳላት ሁሉ ለአንዲት ነጻ ቤተክርስቲያንም አንድ ቅዱስ ሲኖዶስ /Autocephalous Church/ ብቻ እንዳላት የታወቀና የተረጋገጠ ነው፡፡

ቅዱስ ሲኖዶስ ስንል /በተለይ ሀገራዊ Local/ የሚከተሉትን ነገሮች ይይዛል፡-
– ኤጲስ ቆጶሳት
– የታወቀ ሕጋዊ መንበር
– ታሪካዊና ሕጋዊ መሠረት
ለምሳሌ የግብፅን ቤተክርስቲያን ሲኖዶስ ብንመለከት
– ወደ ሃምሳ የሚጠጉ ኤጲስ ቆጶሳት
– የእስክንድርያ /የቅዱስ ማርቆስ/ መንበር
– በታሪክ የታወቀና ቅዱስ ሲኖዶሱ ያጸደቀው ሕግ አላቸው

 የኢትዮጵያ ቅዱስ ሲኖዶስ፦

–    ኤጲስ ቆጶሳት
–    የአዲስ አበባ መንበር /መንበረ ፓትርያክ ቅድስተ ቅዱሳን ማርያም የሚገኝ/
በቤተክርስቲያን ሕግ የጸደቀ ከመነሻውም /ሲኖዶስ በኢትዮጵያ ሲጀመር የነበረ ሕግ አላት፡፡
 

ለእግዚአብሔር በፍርሃት ተገዙ /መዝ 2፡11-12/

በዲ/ን አሉላ መብራቱ

 

የዐቢይ ጾም የመጀመሪያ ሳምንት (ዘወረደ) ለአጠቃላይ ጾሙ መግቢያ የሚሆኑ ሦስት መሠረታዊ ጉዳዮች ላይ ያተኮሩ ትምህርቶች(መልዕክቶች) ይተላለፉበታል። እነዚህን ቀጥለን እንመለከታለን።

1.    ስለ ጾም

ዘወረደ የታላቁ ጾም የመጀመሪያ ሳምንት ስለሆነ ቤተ ክርስቲያን የጾም አዋጅ ታውጅበታለች፤ ስለ ጾም ጥቅምና እንዴት መጾም እንዳለብን ታስተምረናለች፡፡ጾመ ድጓው “አከለክሙ መዋእል ዘኃለፈ ዘተቀነይክሙ ለግእዘ ሥጋክሙ፤ ለሥጋቸሁ ፈቃድ የተገዛችሁበት ያለፈው ዘመን ይበቃችኋል፤ ከአሁን በኋላ ግን ጹሙ፣ ጸልዩ ለእግዚአብሔር ተገዙ” እያለ የጾም አዋጅ ያውጃል።

ጾም ፈቃደ ስጋን ለፈቃደ ነፍስ፣ ፈቃደ ነፍስን ለፈቃደ እግዚአብሔር/ለመንፈስ ቅዱስ/ የምናስገዛበት መንፈሳዊ መሳሪያ ነው፡፡ጾሙ ይህ የሚደረግበት መሆኑን ቤተክርስቲያን ሳምንቱ በሚጀመርበት ሰንበት በሚሰበከው ምስባክ እንዲህ ብላ ታሳስባለች፤ “ለእግዚአብሔር በፍርሃት ተገዙ፣በረዓድም ደስ ይበላችሁ” /መዝ 2፡11-12/ ጾም ከምግብና ከመጠጥ እንዲሁም ከሌሎች ምቾቶችና ደስታዎች ከመከልከል ያለፈ ጥልቅ ትርጉም ያለው ተግባር ነው። ጾም ውጤታማ እንዲሆን እነዚህ መከልከሎች ከጸሎት ፣ ከፍቅርና ራስን ከማዋረድ ጋር መተባበር አለባቸውና በዚህ ሳምንት ቤተ ክርስቲያን እንዲህ እያለች ታስተምራለች፦“ንጹም ጾመ ወናፍቅር ቢጸነ ከመ ያብርህ ብርሃነ ስብሃቲሁ በላዕሌነ፤ (የእግዚአብሔር) የክብሩ ብርሃን በላያችን ላይ ያበራ ዘንድ ጾምን እንጹም ፤ወንድማችንንም እንውደድ”

(ጾመ ድጓ)።በዘወረደ እሁድ የሚነበቡት ምንባባትም ይህንን መልዕክት የያዙ ናቸው።“ነገር ግን ፈጣሪያችን የምትበልጠውን ጸጋ ይሰጣል፤ ስለዚህም “እግዚአብሔር ትዕቢተኞችን ይቃወማል፤ ለትሑታን ግን ጸጋን ይሰጣል” ይላል፡፡ እንግዲህ እግዚአብሔርን እሺ በሉት፤ ሰይጣንን ግን እንቢ በሉት፤ ከእናንተም ይሸሻል፡፡ እግዚአብሔርን ቅረቡት፤ ይቀርባችሁማል፤ እናንተ ኃጥኣን እጆቻችሁን አንጹ፤ ሁለት ዐሳብም ያላችሁ እናንተ ልባችሁን አጥሩ፡፡ እዘኑና አልቅሱ፤ ሳቃችሁን ወደ ልቅሶ÷ ደስታችሁንም ወደ ኀዘን መልሱ፡፡ በእግዚአብሔር ፊት ራሳችሁን ዝቅ አድርጉ፤ እርሱም ከፍ ከፍ ያደርጋችኋል፡፡” /ያዕ 4÷6-10/

 “ በውኑ እንግዲህ በስሙ እናምን ዘንድ የከንፈሮቻችን ፍሬ የሚሆን የምስጋና መሥዋዕትን በየጊዜው ለእግዚአብሔር ልናቀርብ አይገባንምን? ነገር ግን ለድሆች መራራትን÷ከእነርሱም ጋር መተባበርን አትርሱ፤ እንዲህ ያለው መሥዋዕት እግዚአብሔርን ደስ ያሰኘዋልና፡፡” /ዕብ 13÷15-16/

“ ልባችሁ በመብል ያይደለ በጸጋ ቢጸና ይበልጣልና፤ በዚያ ይሄዱ የነበሩ እነዚያ አልተጠቀሙምና ። ” /ዕብ. 13፥9/በጾም የተጠቀሙ ቅዱሳንን እያሰብን ለጾም እንድንተጋም ወደ እነርሱ እንድንመለከት ቤተክርስቲያን ትጠቁማለች፡፡ ሳምንቱ በሚጀምርበት ሳምንት የሚነበበው የቅዱስ ጳውሎስ መልዕክትእንዲህ ይላል፡፡

“የእግዚአብሔርን ቃል የነገሩአችሁን ዋኖቻችሁን አስቡ፥ የኑሮአቸውንም ፍሬ እየተመለከታችሁ በእምነት ምሰሉአቸው።” /ዕብ. 13፥7/ጾመ ድጓው ከእነዚህ መካከል ጥቂቶቹን እንዲህ እያለ ያስታውሰናል፤“የእግዚአብሔር የክብሩ ብርሃን በላያችን ላይ ያበራ ዘንድ ጾምን እንጹም፤ ወንድሞቻችንም እንውደድ፤ ኤልያስ በጾም ወደ ሰማይ አርጓልና፤ዳንኤልም ከአናብስት አፍ ድኗልና፡፡”

2.    ስለ እግዚአብሔር ወልድ መውረድ (ሥጋዌ)

ከዐቢይ ጾም ጀምሮ እስከ ጰራቅሊጦስ ድረስ ያሉት ዕለታት ጌታችንና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የሰውን ልጆች ለማዳን ያደረጋቸው ነገሮች (ማስተማሩ፣ ተአምራት ማድረጉ፣ በፈቃዱ ተላልፎ መሰጠቱ፣ ሞቱ፣ ትንሣኤው፣ ዕርገቱ፣ መንፈስ ቅዱስን መላኩ…) በስፋት የሚነገርባቸው ናቸው።

የእነዚህ ሁሉ ነገሮች መሠረትና ያገኘናቸው ጸጋዎች ሁሉ ምንጭ የእግዚአብሔር ወልድ መውረድ (ሰው መሆን) ነው።ይህ ሣምንት የዐቢይ ጾም የመጀመሪያ ሣምንት እንደመሆኑ ቀጥለው ለሚነገሩት ነገሮች መሠረት የሆነው ይህ የእግዚአብሔር መውረድ ይነገርበታል። ዘወረደ (የወረደው) የሚል ስያሜ የተሰጠውም ከዚህ በመነሳት ነው።

ሣምንቱ በሚጀመርበት ሰንበት የሚነበበው ወንጌል ይህን መልእክት የሚያስተላልፍ ነው።“እውነት እውነት እልሃለሁ፥ የምናውቀውን እንናገራለን ያየነውንም እንመሰክራለን፥ ነገር ግን ምስክርነታችንንም አትቀበሉትም። በምድር ያለውን ስነግራችሁ ካላመናችሁኝ፥ በሰማይ  ያለውን ብነግራችሁ እንዴት ታምኑኛላችሁ? ከሰማይ ከወረደው የሰው ልጅ  በቀር ወደ ሰማይ የወጣ የለም፥ እርሱም በሰማይ የሚኖረው ነው። ሙሴ በምድረ በዳ እባቡን እንደ ሰቀለው የሰው ልጅ እንዲሁ ይሰቀል ዘንድ አለው፡፡ያመነበት ሁሉ ለዘለዓለም ሕያው ሆኖ እንዲኖር እንጂ እንዳይጠፋ።በእርሱ የሚያምን ሁሉ የዘለዓለም ሕይወትን እንዲያገኝ እንጂ እንዳይጠፋ እግዚአብሔር አንድያ ልጁን ቤዛ አድርጎ እስኪሰጥ ድረስ ዓለሙን እንዲሁ ወዶታልና።” /ዮሐ. 3፥11-16/ጾመ ድጓው የሚጀምረውም እንዲህ በማለት ነው፣ “ዘወረደ እምላዕሉ፣ አይሁድ ሰቀሉ…. እግዚአ ኩሉ ዘየሀዩ በቃሉ፤ ….በቃሉ የሚያድነውን ከላይ የወረደውን የሁሉን ጌታ አይሁድ ሰቀሉት… ”

3. ስለ ትምህርት

 ዐቢይ ጾም የትምህርት ዘመን ነው። በጥንት ቤተ ክርስቲያን አዳዲስ አማንያን /ንዑሰ ክርስቲያን/ የሚጠመቁት በትንሣኤ በዓል ስለነበር በዐቢይ ጾም ሰፊ ትምህርት ይሰጣቸው ነበር።ዛሬም ዐቢይ ጾም ጌታችን በዚህ ምድር በእግረ ሥጋ በተመላለሰባቸው ዘመናት ያደረጋቸው  ነገሮች (ትምህርቱ፣ ተአምራቱ፣ ሞቱ፣ ትንሣኤው … ) በሣምንታት ተከፋፍለውና ተደራጅተው የምንማርበት የትምህርት ዘመን ነው። በአብነት ትምህርት ቤቶቻችንም ዐቢይ ጾም ዋነኛ የትምህርት ዘመን መሆኑ ይታወቃል።

ስለዚህም ቤተ ክርስቲያን የትምህርት ዘመን በሆነው ዐቢይ ጾም መግቢያ ላይ ስለ ትምህርትና ስለ መምህራን እንዲህ እያለች ትሰብካለች፤

“የእግዚአብሔርን ቃል የነገሩአችሁን ዋኖቻችሁን አስቡ፥ የኑሮአቸውንም ፍሬ እየተመለከታችሁ በእምነት ምሰሉአቸው። ኢየሱስ ክርስቶስ ትናንትና ዛሬ እስከ ለዘላለምም የሚኖር እርሱ ነውና። ሌላ ልዩ ትምህርት አታምጡ።” /ዕብ. 13፥7-9/

“ለመምህሮቻችሁ ታዘዙ፤ ተገዙላቸውም፤ስለ እናንተ በእግዚአብሔር ፊት ምላሽ የሚሰጡ እንደመሆናቸው፣ ይህን ሳያዝኑ ደስ ብሎአቸው ያደርጉት ዘንድ ስለ ነፍሳችሁ ይተጋሉና፡፡” /ዕብ. 13፥17/

አምላካችን እግዚአብሔር ሆይ መዋዕለ ጾሙን በሠላም አሳልፈህ የትንሣኤህን ብርሃን ለማየት እንድታበቃን እንለምንሃለን። አሜን።