ሰላም!
ውድ የእግዚአብሔር ልጆች! እንዴት አላችሁልን? በፈቃደ እግዚአብሔር የጀመርነው ዐቢይ ጾም (ጾመ ክርስቶስ) ጨርሰን በዓለ ትንሣኤን እያከበርን ነው፤ በዓሉን እንዴት እያከበራችሁ ነው? የትንሣኤ በዓል ነጻነታችንን አግኝተን ትንሣኤ እንዳለን የተበሠረበት በዓላችን ነውና ታላቅ በዓል ነው፡፡
ጌታችንና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ስለ እኛ ሞቶ ሞትን ድል አድርጎ በመነሣቱ ትንሣኤያችንን አበሠረን፤ ከሞት በኋላ ሕይወት እንዳለን ዐወቅን፡፡ ታዲያ በጾሙ ወቅት እናደርገው እንደነበረው በጸሎት መበርታትና በመንፈሳዊ አገልግሎት መሳተፍ አለብን፤
በዘመናዊ ትምህርታችን መበርታት እንዳለብንም መዘንጋት አይገባም፡፡ አሁን ያለንበት ጊዜ ትምህርቱ መገባደጃ ወቅት ስለሆነ ከፈተና በፊት በርትተን በማጥናት ዕውቀትን አግኝተን ከክፍል ክፍል በጥሩ ውጤት መሸጋገር ይገባናል፤ መልካም! ለዛሬ ከበዓለ ትንሣኤ ጋር በተያያዘ ስለ ሰላም እንማራለን፡፡