የማያልቀው ሀብት

ነጭ አይሉት ጥቁር፣ አመዳማም አይደል ቀለሙ ይለያል፡፡ብዙዎች ስለ መልኩ መናገር ያዳግታቸውና ዝምታን ይመርጣሉ፤አያሌዎች ደግሞ በተፈጥሮው ተማርከው ውበቱን ያደንቃሉ፤ መግለጽ ግን ያቅታቸዋል፡፡

‹‹ይፈኑ ለክሙ ጰራቅሊጦስሃ፤ አጽናኝ መንፈስ ይልክላችኋል›› (ዮሐ.፲፬፥፲፮)

የቤዛነት ሥራውን ከፈጸመ በኋላ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በክብር ሲያርግ ለሐዋርያት የሰጣቸው ተስፋ አጽናኝና የእውነት መንፈስ የሆነውን መንፈስ ቅዱስን አብ እንደሚልክላቸው፣ እርሱም አጽናኝ የሆነ ጰራቅሊጦስ እንደሆነ ለዘለዓለሙም ከእነርሱ ጋር እንደሚሆን ነግሯቸው ነበር፡፡ ጌታችን እንደተናገረውም በሰጣቸው ተስፋ መሠረት ባረገ በዐሥረኛው ቀን በተነሣ ደግሞ በሃምሳኛው ቀን መንፈስ ቅዱስን ልኮላቸዋል፡፡

ርኅሩኁና የይቅርታ መልአክ

የርኅራኄ መዝገብ፣ ትሑት፣ ታዛዥና ለዘለዓለም ፈጣሪውን አመስጋኝ ሊቀ መላእክት ቅዱስ ሚካኤል ጌታ በሚያደርገው ቸርነት ላይ ለሰው አንድ ወገን የሚሆን መልአክ ነው፡፡ (ሄኖ.፮፥፭፣፲፪፥፭፣፲፥፲፪)

‹‹በጠበበው ደጅ ግቡ›› (ማቴ.፯፥፲፫)

ወዳጄ ሆይ! የምትጓዝበትን መንገድ የማታውቅ ከሆነ ትጠፋለህና በየትኛው መንገድ ላይ ልትራመድ እንደሚገባህ ልታገናዝብ ያስፈልግሃል። በፊትህ ሰፊ፣ አታላይና ጠባብ መንገዶች አሉና፡፡ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ለደቀ መዛሙርቱ እንዲህ በማለት አስጠንቅቋቸዋል። ‹‹በጠበበው ደጅ ግቡ፤ ወደ ጥፋት የሚወስደው ደጁ ሰፊ መንገዱም ትልቅ ነውና፤…፡፡›› (ማቴ.፯፥፲፫)

የምሕረት ቤት

የፍቅር ባለቤት፣ የምሕረት ጌታ፣ የዓለሙ ሁሉ መድኃኒት፣ የሰው ልጆች ቤዛ ጌታችን በተወለደባት በኢየሩሳሌም ከተማ በቤተ መቅደሱ አቅራቢያ የምትገኝ በዕብራይስጥ ቋንቋ “ቤተ ሳይዳ” በአማርኛው ደግሞ “የምሕረት ቤት” የተባለች የመጠመቂያ ቦታ ነበረች፡፡

የምእመናን ድርሻ በቤተ ክርስቲያን

ሰው ሲቀደስም ሲረክስም የሚኖረው በፈቃደ ሥጋ እና ፈቃደ ነፍስ መካከል ባለው የአሸናፊነትና ተሸናፊነት ትግል ነው፡፡የተቀደሰ ጾምን በተቀደሰ ሥርዓት ጹመን በረከተ ሥጋ በረከተ ነፍስ እናገኝ ዘንድ በሥርዓቱ፣ በትሕትና፣ በንስሓና በተሰበረ ልቡና ሆነን ልንጾም ይገባል።

‹‹ትነብር ውስተ ቤተ መቅደስ፤ በቤተ መቅደስ ውስጥ ትኖር ነበር›› ቅዱስ ያሬድ

ዓለም ሁሉ ተሰብስቦ ቢመዘን አንድ የራሷን ፀጉር የማያህል ደግ ፍጥረት፣ ከሰው የበለጠች ከመላእክት የከበረች፣ ንጽሕናዋንም ይሁን ቅድስናዋን ፍጥረት በአንደበቱ ተናግሮም ሆነ ጽፎ የማይጨርሰው፣ የአምላክ ማደሪያ፣ እመ አምላክ፣ እመ ብዙኃን፣ ሰዓሊተ ምሕረት፣ አቁራሪተ መዓት እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ወደ ቤተ መቅደስ የገባችበት ዕለት የከበረ በዓል ነው፡

ነቢዩ ኤልያስ

ውድ የእግዚአብሔር ልጆች ! እንዴት አላችሁ? ባለፈው ትምህርታችን ስለ ቅዱሳን ነቢያት፣ እነርሱ ስለ ጾሙትና የነቢያት ጾም ተብሎ ስለሚጠራው ጾም በጥቂቱ ተመልክተናል፤ለዛሬ የምንነግራችሁ ደግሞ ስለ ከቅዱሳን ነቢያት አንዱ ስለሆነው ስለ ነቢዩ ኤልያስ ነው፡፡

‹‹የእግዚአብሔር ሰው›› (፩ኛሳሙ.፱፥፮)

መልእክተኛውም ሚክያስን ‹‹እነሆ ነቢያት ሁሉ በአንድ አፍ ሆነው ለንጉሡ መልካሙን ይናገራሉ፤ ቃልህም እንደ ቃላቸው እንዲሆን መልካም እንድትናገር እለምንሃለሁ›› ይለዋል፡፡ (፩ኛ ነገ.፳፪፥፲፫) ነቢዩ ግን ‹‹ሕያው እግዚአብሔርን! እግዚአብሔር የሚነግረኝን እርሱን እናገራለሁ›› አለው፡፡

ሃያ አራቱ አለቆች (መጽሐፈ ስንክሳር)

ምስጋና ለሥሉስ ቅዱስ ይድረስና ሁልጊዜ በየዓመቱ በኅዳር ፳፬ ቀን እኛ የኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ምእመናን የካህናተ ሰማይ (ሱራፌ) በዓልን እንድናከብር አባቶች ሥርዓትን ሠርተውልናል፡፡