ትጋት

የክርስቲያናዊ ምግባራችን ጽናት ከሚገለጽባቸው ዋነኞቹ ተግባራት መካከል ትጋት አንዱ ነው፡፡ ጸሎትን፣ ጾምንና ስግደትን በማብዛት የሚገለጸው ትጋታችን ክርስትናችንን የምናጠነክርበት ምግባራችን ነው፡፡ ዘወትር ሥርዓተ ጸሎትና ጾምን ጠብቀን መኖራችን በመንፈሳዊ ሕይወታችን ጠንክረንና ማንኛውንም ፈተና አልፈን እንድናንጓዝ ይረዳናልና ትጋታችንን ማጠንከር የምንችለው ዕለት ከዕለት ስንጸልይ፣ በሥርዓት ስንጾምና አብዝተን ስንሰግድ ነው፡

“ትዋደዱ ዘንድ አዲስ ትእዛዝ እሰጣችኋለሁ” (ዮሐ.፲፫፥፴፬)

መውደድ በሰዎች መካከል የሚኖር ስሜት ነው፤ ያለ መዋደድም በዚህ ምድር ላይ መኖር አይቻለንም፤ መጠኑ ይብዛም ይነስ በሰው ልብ ውስጥ የመዋደድ ስሜት ይፈጠራል፡፡ ሰዎች ተቻችለንና ተሳስብን እንዲሁም ተዛዝነን የምንኖረው ስንዋደድ ነው፡፡ ግን ይህ ስሜት ከምንም ተነሥቶ በውስጣችን ሊፈጠር አይችልምና መውደድ መነሻው ምንድነው? የሚለውን ነገር ብንመረምር መልካም ነው፡፡

ተንሥኡ!

በከበረና ድንቅ ሥራው ሰውን ሕያው አድርጎ ሲፈጥረው እግዚአብሔር አምላክ እስትንፋስና ሕይወትን ሰጥቶ ካለመኖር ወደ መኖር ባመጣው ጊዜ የሕይወቱን ዘመናት አሐዱ ብሎ እንደጀመረ መጽሐፈ ኦሪት ያወሳናል፡፡ ወደ አፈር እስኪመለስ ድረስም ሞትን አልቀመሳትም ነበር፡፡ ጊዜው ሆነና ግን ሞተ፤ ተቀበረ፤ አፈርም ሆነ፤ በምድር ላይም ታሪኩ እንጂ ሥጋው አልቀረለትም፤ እናስ መቼ ይሆን የቀደመ ክብሩና ጸጋውን አግኝቶ፣ ሥጋውም ከነፍሱ ጋር ተዋሕዳ በሰማያዊት ቤቱ የሚኖረው?

ከጥምቀት በኋላ ክርስትና

ውድ የእግዚአብሔር ልጆች! እንዴት አላችሁ? የጥምቀት በዓል እንዴት አለፈ? እናንተስ የጥምቀትን በዓል እንዴት አከበራችሁት? ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ለእኛ አብነት ለመሆን እንዲሁም ደግሞ የዕዳ ደብዳቤያችንን ሊደመስስልን መጠመቁን ምክንያት በማድረግ በየዓመቱ በደስታ በምስጋና በዓሉን እናከብራለን፡፡ መቼም ልጆች! ከወላጆች አልያም ከጓደኞቻችን ጋር በመሆን አክብራችኋል፤ መልካም!

ሌላው ደግሞ ወቅቱ ለእናንተ ለተማሪዎች የዓመቱ አጋማሽ የምዘና ፈተና ነበር! ፈተናስ እንዴት ነበር? እንግዲህ የዓመቱ አጋማሽ የትምህርት ወቅት አልቆ ፈተናም ተፈትናችሁ ውጤት የተሰጣችሁ እንዲሁም ውጤት በመጠባበቅ ላይ ያላችሁ ትኖራላች፡፡ ከባለፈው ውጤታችሁ በመነሣት በቀጣዩ የትምህርት ጊዜ በርትታችሁ ለመማር እንደ ምታቅዱ ተስፋችን እሙን ነው፡፡ ደግሞ በዕረፍት ጊዜያችሁ መልካምን ነገር በማድረግ አሳለፉ፡፡ በርቱ! ለዛሬ የምንነግራችሁ ከጥምቀት በኋላ ክርስትና ምን ይመስላል የሚለውን እንመለከታለን፤ መልካም ቆይታ!

“ክፉውን በመልካም አሸንፍ እንጂ በክፉ አታሸነፍ” (ሮሜ ፲፪፥፳፩)

ክፉና በጎ የሰው ልጆች ባሕርያት ናቸው፡፡ ይሁን እንጂ እግዚአብሔር ዓለምን ሲፈጥር ለመልካም ነበረ፡፡ (ዘፍ.፩፥፲፪) ምንም እንኳን የፍጥረት አክሊል የሆነው ሰው ነጻ ፈቃዱን ተጠቅሞ ከብርሃን ጨለማን፣ ከሕይወት ሞትን፣ ከመታዘዝ አለመታዘዝን ቢመርጥም እግዚአብሔር አምላክ የፈጠረው ስሙን እንዲቀድስ ክብሩን እንዲወርስ ነበረ፡፡ ለዚህም ክፉና ደጉን መለየት ይችል ዘንድ አስቀድሞ የሚያስተውል አእምሮ ሰጥቶት ነበር፡፡ በኅሊናው መመራት ተስኖት የሰው ልጅ ከወደቀ በኋላ ዳግመኛ የተጻፈ ሕግ ሰጥቶታል፡፡ ሰዎች ራሳቸው ላይ የክፉ ብድራት እንዳይደርስባቸው አስበው በባልንጀራቸው ላይ ክፉ እንዳያደርጉ ክፉ ላደረጉ የክፉ ብድራት እንዲከፈላቸው ሙሴ ሕግን ጻፈላቸው፡፡

ሥርዓተ አምልኮ

በዓላት ከማንኛውም ቀናት የበለጠ አምላካችን እግዚአብሔርን የምናመሰገንባቸውና የምናወድስባቸው፣ የተቀደሱትን ዕለታት በማሰብና በመዘከር በዝማሬ፣ በሽብሻቦና በእልልታ የምናከብርባቸው ናቸው፡፡ ታቦታት ከመንበረ ክብራቸው የሚወጡባቸውና ሕዝበ ክርስቲያኑን የሚባርኩባቸው ስለሆኑም በክብርና በድምቀት ይከበራሉ፡፡   

“ወደ ምሥራቅ ተመልከቱ” (ሥርዓተ ቅዳሴ)

ምሥራቅ የቃሉ ፍቺ “የፀሐይ መውጫ” ማለት ነው፡፡ (አለቃ ኪዳነ ወልድ መጽሐፈ ሰዋሰው ወግሥ ወመዝገበ ቃላት ሐዲስ ገጽ ፮፻፹) በሥርዓተ ቅዳሴ ላይ ዲያቆኑ “ወደ ምሥራቅ ተመልከቱ” በማለት በዜማ ለምእመናኑ ያውጃል፤ በእርግጥ በቅዳሴ ጊዜ በመካከል የሚያነቃቁና የአለንበትን ቦታ እንድናስተውል የሚያደርጉ ሌሎች ዐዋጆች አሉ፡፡ ከእነዚህም መካከል “እለ ትነብሩ ተንሥኡ፤ የተቀመጣችሁ ተነሡ” የሚለው ነው፡፡ በቅዳሴ ጊዜ ከታመመ ከአረጋዊ በቀር ማን ማንም አይቀመጥም፡፡ ሰው እያስቀደሰ እየጸለየ ልቡናው ሌላ ቦታ ይሆንበታል፤ ይባዝናል፤ ያለበትን ትቶ በሌላ ዓለም ይባዝናል፡፡ አንዳንዴ ጸሎት እየጸለይን ሐሳባችን ሊበታተን ይችላል፡፡ ከየት ጀምረን የት እንዳቆምንም ይጠፋብናል፤ መጀመራችን እንጂ እንዴት እንደጨረስነውም ሳናውቀው ጨርሰን እናገኘዋለን፤ ዲያቆኑ በቅዳሴ ጊዜ “የተቀመጣችሁ ተነሡ” ማለቱ “የቆማችሁ በማን ፊት እንደሆነ አስታውሉ” ሲል ነው፡፡

እንዲሁም “ወደ ምሥራቅ ተመልከቱ” ሲባል ምን ማለት ነው? ዲያቆኑስ ምን እንድናደርግ ነው ያዘዘን? የሚለውን በመቀጠል እናያልን።

ምሕረት ሥጋዊና ምሕረት መንፈሳዊ

የምሕረት አምላክ ቸሩ ፈጣሪያችን እግዚአብሔር ኃጢአት በደላችንን ሁሉ ታግሦ እንደ ሥራችን ሳይሆን እንደ ቸርነቱ ለአዲሱ ዓመት አበቃን፡፡ ዕድሜ ለንስሓ ዘመን ለፍስሐ ያደለን አምላካችን በሰጠን የተፈጥሮ ጸጋ ተጠቅመን ከክፉ መንገዳችን እንድመልስ፣ ከኃጢአት እንድንነጻ እንዲሁም በጎ ሥራ እንድሠራ ነው፡፡ ምሕረቱ የበዛ ቁጣውም የራቀ ቸርነቱ አያልቅምና በእርሱ ጥላ ሥር ተጠልለን በሥነ ምግባር እንድንኖር መልካም ፈቃዱ ሆነ፡፡ ይህንንም በቅዱሳን ልጆቹ ላይ ፈጽሞ አሳይቶናል፡፡ በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ስም ክርስቲያን የተባልን በሙሉም ምሕረትን ስለማድረግ ልናውቅ ያገባናል፡፡ ሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያን ምሕረት በሁለት እንድሚከፈል ያስተምሩናል፤ እነርሱም ምሕረት ሥጋዊና ምሕረት መንፈሳዊ ናቸው፡፡

ዐቢይ ጾም

‹ዐቢይ›› የተባለው የዓለማት ፈጣሪ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ለአርአያነት ጾሞ የመሠረተው ጾም ስለሆነ ነው፡፡ በኦርቶዶክሳዊት ቤተ ክርስቲያን ካሉት ሰባት የአዋጅ አጽዋማት ረጅሙ (፶፭ ቀን ያለው) ስለሆነ ደግሞ ‹‹ሁዳዴ›› ይባላል፡፡ ኢትዮጵያዊው የዜማና የቅዱሳት መጻሕፍት ሊቅ ቅዱስ ያሬድ በዐቢይ ጾም ውስጥ የሚገኙትን ስምንት ሣምንታት ለትምህርት፣ ለአዘክሮና ለምስጋና በሚመች መልኩ ልዩ ስያሜዎች ሰጥቷቸዋል፡፡ ስለሆነም በእያንዳንዱ ሳምንት (ሰንበት) የሚነበቡ፣ የሚተረጎሙ፣ የሚዘከሩ፣ የሚዘመሩ ልዩ ልዩ መጽሐፍ ቅዱሣዊ ኩነቶችና አስተምህሮዎች አሉ፡፡

የነነዌ ጾም

ነነዌ የሜሶፖታምያ ከተሞች ከሆኑት መካከል አንዷ ናት፡፡ ከሞሱል ከተማ በተቃራኒ ከባግዳድ ሰሜን ምዕራብ ፫፻፶ ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ እንደ ነበረች በታረክ ይነገራል፡፡ በ፵፻ (ዐራት ሺህ) ቅድመ ልደተ ክርስቶስ በናምሩድ በኩል ከተቆረቆረችም በኋላ በ፲፻፬፻ (አንድ ሺህ ዐራት መቶ) ቅድመ ልደተ ክርስቶስ የአሦራውያን ዋና ከተማ ሆናለች፡፡ (ዘፍ.፲፥፲፩፣፪ኛነገ.፲፱፥፴፮)

በከተማዋም ታዋቂ የነበረ አስታሮት የተባለ የጣዖት ቤተ ነበረ፡፡ በዚህች ከተማ የሚኖሩት ሰዎች የሚሠሩት ክፋትና ኃጢአት እጅግ ከመብዛቱ የተነሣ ጽዋው ሞልቶ መጥፊያቸው ስለ ደረሰ ለፍጥረቱ ርኅራኄ ያለው እግዚአብሔር ግን ንስሓ ይገቡ ዘንድ ነቢዩ ዮናስን ልኮላቸዋል፡፡ ይህ ነቢይ ከአሕዛብ ወደ አሕዛብ ወደ ንስሓ ይጠራቸው ዘንድ ነበር የተላከ ነው፡፡