የምእመናን ድርሻ በቤተ ክርስቲያን ከምን ይጀምራል?

ቤተ ክርስቲያን የሁላችንም ቤት ናት፡፡ በቤታችን ሁላችንም የሥራ ድርሻ እንዳለን ሁሉ በመንፈሳዊት ቤታችን በቤተ ክርቲያንም እንዲሁ ሁላችንም ድርሻ ሊኖረን ይገባል፡፡ ቤተ ክርስቲያን የሊቀ ጳጳሳት፣ የካህናት እና በቤተ ክርስቲያን በአስተዳደር ሥራ ላይ የተሠማሩ ሰዎች ቤት ብቻ ሳትሆን የሁላችንም ቤት ናት፡፡

“ተዘጋጅታችሁ ኑሩ’’ (ማቴ.፳፬፥፵፬)

ጌታች አምላካችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ለቅዱሳን ደቀ መዛሙርቱ የነገራችው ኃይለ ነው፤ ‘’ጌታችሁ በምን ሰዓት እንደሚመጣ አታውቁምና እንግዲህ ንቁ፤ እወቁ ባለቤት ሌሊት ሌባ በየትኛው ጊዜ እንደሚመጣ ቢያውቅ ኖሮ በነቃ፤ ቤቱንም እንዲቆፈር ባልተወ ነበር’’ አላቸው፡፡ ስለዚህ እናንተ ደግሞ ተዘጋጅታችሁ ኑሩ፤ የሰው ልጅ በማታስቡት ሰዓት ይመጣልና፤

ጾመ ፍልሰታ ለማርያም

ውድ የእግዚአብሔር ልጆች! እንዴት ናችሁ? የክረምቱን ወቅት ምን ቁም ነገር እየሠራችሁበት ነው? ወደ ቤተ ክርስቲያን በመሄድ መንፈሳዊ ትምህርት እየተማራችሁ እንደሆነ ተስፋ እናደርጋለን፤ ልጆች! ለዛሬ የምንማረው ስለ ፍልሰታ ጾም ነው፤

‹‹በልቅሶ የሚዘሩ በደስታ ይሰበስባሉ›› (መዝ.፻፳፭፥፭)

የሰው ልጅ በዚህ ምድር ከሚፈራረቁበት የስሜት ነጸብራቆች ዋነኞቹ ኀዘን (ልቅሶ)ና ደስታ ናቸው። እርግጥ ነው እግዚአብሔር የሰውን ልጅ የፈጠረው እያመሰገነው በደስታ ይኖር ዘንድ ነበር፡። ስለዚህም እግዚአብሔር ሰውን የሚያስፈልገውን ሁሉ ካዘጋጀለት በኋላ በአትክልት ሥፍራ ኤደን ገነት በደስታ እንዲኖር አስቀመጠው፡፡ ነገር ግን የሰው ልጅ በገዛ ፈቃዱ ደስታ የሚሰጠውን ሕግ አፍርሶ የደስታ ምንጭ የሆነውን እግዚአብሔርን አጣ፤ በማጣት ብቻም አልቀረም ‹‹…ስለዚህ የተገኘባትን መሬት ያርስ ዘንድ እግዚአብሔር አምላክ ደስታ ከሚገኝባት ገነት አስወጣው…›› (ዘፍ. ፫÷፳፫)። የሰው ልጅ በድሎ ከኤደን ገነት ወደ ምድር (ዓለመ መሬት) ከመጣ በኋላ እግዚአብሔርን አሳዝኖ ጸጋውን አጥቷልና በሕይወቱ ኀዘን (ልቅሶ) ሰፊውን ጊዜ የሚወስድበት ፍጡር ሆነ። ለ፭ሺ ፭መቶ ዘመን የሰው ልጅ ፍጹም በሆነ ኀዘን ውስጥ ከኖረ በኋላ እግዚአብሔር ወልድ በተለየ አካሉ ሥጋን ተዋሕዶ በመገለጥ ለአዳም (ለሰው ልጅ) ካሣ በመሆን ወደ ፍጹም ደስታ መልሶታል።

ተስፋ

ሕይወታችን ያለ ተስፋ ባዶ ነው፤ ያለ ተስፋ መኖር አንችልም፤ ተስፋ ከሌለን ማንኛውንም ዓይነት የኑሮ ገጠመኝና ችግር ማሳለፍ አይቻለንም፡፡ የሰው ልጆች ዋነኛው ብርታት ተስፋ ማግኘትና በተስፋ መኖር ነው፡፡ የመጀመሪያው ሰው አዳም የአምላካችን የእግዚአብሔርን ሕግ ተላልፎ አትብላ የተባለውን ዕፀ በለስ ከበላ በኋላ የሞት ፍርድ ተፈርዶበት በምድር ላይ ሲኖር በኀዘንና በጭንቅ ነበር፡፡ ሆኖም ግን ፈጣሪ የልቡን ጭንቀትና ኀዘን ተመልክቶ ሊምረው ስለወደደ ከልጅ ልጁ ተወልደ እንደሚያድነው ቃል ገባለት፡፡ ይህም ለአዳም ትልቅ ተስፋ ስለነበረ ትንቢቱ ይፈጸም ዘንድ በተስፋ ጠብቋል፡፡

‹‹ትዕግሥትን ልበሱ›› (ቈላ.፫፥፲፪)

በሕይወታችን ውስጥ እጅጉን አስፈላጊ መጨረሻውም አስደሳች የሆነው ነገር ትዕግሥት ነው፤ በማንኛውም ሁኔታና ጊዜ ሆነን የምንጋፈጠውን ችግር፣ መከራና ሥቃይ በብርታትና በጽናት ለማለፍ የምንችለው ትዕግሥተኛ ስንሆን ነው፡፡ መታገሥ ከተቃጣ ሤራ፣ ከታሰበ ክፋት፣ ከበደልና ግፍ ያሳልፋል፤ ልንወጣው ከማንችለው ችግርም እንድንወጣ ይረዳናል፡፡

ትጋት

የክርስቲያናዊ ምግባራችን ጽናት ከሚገለጽባቸው ዋነኞቹ ተግባራት መካከል ትጋት አንዱ ነው፡፡ ጸሎትን፣ ጾምንና ስግደትን በማብዛት የሚገለጸው ትጋታችን ክርስትናችንን የምናጠነክርበት ምግባራችን ነው፡፡ ዘወትር ሥርዓተ ጸሎትና ጾምን ጠብቀን መኖራችን በመንፈሳዊ ሕይወታችን ጠንክረንና ማንኛውንም ፈተና አልፈን እንድናንጓዝ ይረዳናልና ትጋታችንን ማጠንከር የምንችለው ዕለት ከዕለት ስንጸልይ፣ በሥርዓት ስንጾምና አብዝተን ስንሰግድ ነው፡

“ትዋደዱ ዘንድ አዲስ ትእዛዝ እሰጣችኋለሁ” (ዮሐ.፲፫፥፴፬)

መውደድ በሰዎች መካከል የሚኖር ስሜት ነው፤ ያለ መዋደድም በዚህ ምድር ላይ መኖር አይቻለንም፤ መጠኑ ይብዛም ይነስ በሰው ልብ ውስጥ የመዋደድ ስሜት ይፈጠራል፡፡ ሰዎች ተቻችለንና ተሳስብን እንዲሁም ተዛዝነን የምንኖረው ስንዋደድ ነው፡፡ ግን ይህ ስሜት ከምንም ተነሥቶ በውስጣችን ሊፈጠር አይችልምና መውደድ መነሻው ምንድነው? የሚለውን ነገር ብንመረምር መልካም ነው፡፡

ተንሥኡ!

በከበረና ድንቅ ሥራው ሰውን ሕያው አድርጎ ሲፈጥረው እግዚአብሔር አምላክ እስትንፋስና ሕይወትን ሰጥቶ ካለመኖር ወደ መኖር ባመጣው ጊዜ የሕይወቱን ዘመናት አሐዱ ብሎ እንደጀመረ መጽሐፈ ኦሪት ያወሳናል፡፡ ወደ አፈር እስኪመለስ ድረስም ሞትን አልቀመሳትም ነበር፡፡ ጊዜው ሆነና ግን ሞተ፤ ተቀበረ፤ አፈርም ሆነ፤ በምድር ላይም ታሪኩ እንጂ ሥጋው አልቀረለትም፤ እናስ መቼ ይሆን የቀደመ ክብሩና ጸጋውን አግኝቶ፣ ሥጋውም ከነፍሱ ጋር ተዋሕዳ በሰማያዊት ቤቱ የሚኖረው?

ከጥምቀት በኋላ ክርስትና

ውድ የእግዚአብሔር ልጆች! እንዴት አላችሁ? የጥምቀት በዓል እንዴት አለፈ? እናንተስ የጥምቀትን በዓል እንዴት አከበራችሁት? ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ለእኛ አብነት ለመሆን እንዲሁም ደግሞ የዕዳ ደብዳቤያችንን ሊደመስስልን መጠመቁን ምክንያት በማድረግ በየዓመቱ በደስታ በምስጋና በዓሉን እናከብራለን፡፡ መቼም ልጆች! ከወላጆች አልያም ከጓደኞቻችን ጋር በመሆን አክብራችኋል፤ መልካም!

ሌላው ደግሞ ወቅቱ ለእናንተ ለተማሪዎች የዓመቱ አጋማሽ የምዘና ፈተና ነበር! ፈተናስ እንዴት ነበር? እንግዲህ የዓመቱ አጋማሽ የትምህርት ወቅት አልቆ ፈተናም ተፈትናችሁ ውጤት የተሰጣችሁ እንዲሁም ውጤት በመጠባበቅ ላይ ያላችሁ ትኖራላች፡፡ ከባለፈው ውጤታችሁ በመነሣት በቀጣዩ የትምህርት ጊዜ በርትታችሁ ለመማር እንደ ምታቅዱ ተስፋችን እሙን ነው፡፡ ደግሞ በዕረፍት ጊዜያችሁ መልካምን ነገር በማድረግ አሳለፉ፡፡ በርቱ! ለዛሬ የምንነግራችሁ ከጥምቀት በኋላ ክርስትና ምን ይመስላል የሚለውን እንመለከታለን፤ መልካም ቆይታ!