‹‹የቅድስት ማርያም ሞት ግን ሁሉን ያስደንቃል›› ቅዱስ ያሬድ
ሊቁ ቅዱስ ያሬድ ‹‹ሞትሰ ለመዋቲ ይደሉ ሞታ ለማርያም የዐጽብ ለኵሉ፤ ሞት ለማናቸውም ሰው ሁሉ የተገባ ነው፤ የቅድስት ማርያም ሞት ግን ሁሉን ያስደንቃል›› በማለት የመሠከረው ስለ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ዕረፍት ነው፡፡ እርሷ በምድር ላይ በአይሁድ ክፋት ብዙ መከራና ኃዘን ካሳለፈች በኋላ በዘመነ ሉቃስ፣ ጥር ሃያ አንድ ቀን፣ በዕለተ እሑድ፣ በስድሳ ዐራት ዓመቷ ወደ ዘለዓለም ደስታ ትገባ ዘንድ ዐርፋለችና፡፡ (ጾመ ድጓ)