mkradio.jpg

የጥምቀት በዓል የሬዲዮ መርሐ ግብር

mkradio.jpg
multimedia.jpg

ማኅበረ ቅዱሳን የህብር ሚዲያ መካነ ድር አገልግሎት ጀመረ

  በተ/ሥላሴ ጸጋ ኪሮስ

ማኅበረ ቅዱሳን ከዚህ በፊት ከነበሩት የአማርኛ(www.eotcmk.org) እና የእንግሊዘኛ (www.eotcmk.org/site-en) መካነ ድሮች በተጨማሪ አዲስ የህብር ሚዲያ መካነ ድር (multimedia website) አገልግሎት ጀምሯል።  

multimedia.jpg

 

 

"multimedia.eotc-mkidusan.org" በሚል አድራሻ የተለቀቀው ይኸው መካነ ድር የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያንን ትምህርተ ሃይማኖት፣ ሥርዓት እምነትና ክርስቲያናዊ ትውፊት የጠበቁ የምስል ወድምጽ ስብከቶችና ተከታታይ ትምህርቶች፣ ዜማዎችና፣ መዝሙራት እንዲሁም የቅዱሳት መጻሕፍትን ትርጓሜና ንባብ ያስተላልፋል። ቅዱሳት ሥዕላትና የቅዱሳት መካናት ፎቶዎችም ከመግለጫ ጋር ይኖሩታል::(http://multimedia.eotc-mkidusan.org/video/?video=2364766985) 

 
በመካነ ድሩ የሚተላለፉ የምስልና የድምጽ ውጤቶች የቤተክርስቲያንን ትምህርትና የስብከተ ወንጌልን  ተደራሽነት እንዲጨምሩና በተለያዩ ቦታዎች ለሚሰጡ ትምህርቶችና ስልጠናዎች እንደ ግብአትነትና ምንጭነት እንዲያገለግሉ ታቅዶ አገልግሎቱ ተጀምሯል። ይህም ኦርቶዶክሳዊ አስተምህሮ  ተጠብቆ ከትውልድ ወደ ትውልድ እንዲተላለፍ ከፍተኛ አስተዋጽኦ ያበረክታል።
 
መካነ ድሩን ለአጠቃቀም ምቹ ለማድረግ የምስል ወድምጽ፣ የድምጽ፣ እና የምስል ዝግጅቶች እያንዳንዳቸው በተለያዩ ክፍሎች (ዐምዶች) ተደራጅተው ቀርበዋል። ተጠቃሚዎች ዝጅቶቹን መካነ ድሩ ላይ በቀጥታ በማጫወት(streaming) ወይም በማውረድ(downloading) መጠቀም የሚችሉበት መንገድም ተመቻችቷል።
 
መካነ ድሩ በአንድ የማኅበሩ ኤሌክትሮኒክስ ሚዲያ ክፍል አገልጋይ የተሠራ ሲሆን በገንዘብ ሲተመን ከ20 እስከ 30 ሺህ ብር ሊያወጣ እንደሚችል ይገመታል፡፡ መካነ ድሩ በሳምንት ከ10 ሰዓታት በላይ የምስል ወድምጽ ዝግጅቶችን ማቅረብ የሚጀምር ሲሆን የኢንተርኔት አገልግሎት በበቂ ሁኔታ ለሌለባቸው አካባቢዎች እነዚህ ዝግጅቶች በሲዲ የሚሰራጩበት መንገድም ከማኅበረ ቅዱሳን የስብከተ ወንጌል ፕሮግራም ጋር በመተባበር እየተመቻቸ ነው ።
 
የህብር ሚዲያ መካነ ድር መሰናዶዎች በተለያዩ ቅርጾች (formats) ማለትም በጽሑፍ፣ በድምጽ እና በተንቀሳቃሽ ምስሎች እና ቋሚ ምስሎች ተዘጋጅተው በመካነ ድር የሚቀርቡበት ሚዲያ ነው፡፡ በአሁኑ ጊዜም በመላው ዓለም በሚገኙ ታላላቅ የሚዲያ ተቋማት ዘንድ ከፍተኛ ተቀባይነት እያገኘ የመጣ እና እጅግ ብዙ የሰው ሀይል፣ ገንዘብ እና ቁሳቁስ የሚያስፈልጋቸውን ዘልማዳዊ (fotress) ሚዲያዎችን እየተካ ያለ አሰራር ነው፡፡
 
ይህንን አገልግሎት ለማሳካትና  የበለጠ ለማሳደግ  በመላው ዓለም ከሚገኙ ምእመናን የጸሎት፣የሐሳብ፣ የሙያ እና የገንዘብ ድጋፍ ይጠበቃል።ለበለጠ መረጃ፣ ለአስተያየቶችና ለድጋፍ የዝግጅት ክፍሉን ወደ mkelectronicsmedia@gmail.com በመጻፍ ማግኘት ይቻላል።

 

hyawEwnet.jpg

“ታሪክ የሚሠራው ከታሪክ ነው።”

  በኪ/ማርያም

በአዲስ አበባ የስብሰባ ማዕከል አዳራሽ ጥር 01 ቀን 2003 ዓ.ም በዓይነቱ የመጀመሪያ የሆነ ‘ሕያው እውነት’ በሚል ርዕስ በኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ/ሰ/ት/ቤቶች ማደራጃና መምሪያ ማኅበረ ቅዱሳን የኦዲዮ ቪዥዋልና ሥነ ጥበባት ሥራዎች ማእከል አማካኝነት የተዘጋጀው መንፈሳዊ ፊልም ብጹአን አበው ሊቃነ ጳጳሳት በተገኙበት ተመረቀ።

በፊልሙ ምርቃት ላይ ብጹእ አቡነ ሚካኤል የወላይታና ዳውሮ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስና የቅዱስ ሲኖዶስ አባል፣ ብጹእ አቡነ ያሬድ የምሥራቅ ሐረርጌ ሊቀጳጳስ የሰበካ ጉባኤ ማደራጃ መምሪያ ሊቀ ጳጳስና የቅዱስ ሲኖዶስ አባል፣ ዶ/ር አባ ኃ/ማርያም መለሠ የስብከተ ወንጌልና ሐዋርያዊ አገልግሎት መምሪያ ሓላፊ፣ መጋቢ ሥርዐት ዳንኤል ወልደ ገሪማ የቁልቢ ገብርኤል ንዋያተ ቅድሳት ማደራጃ መምሪያ ዋና ሥራ አስኪያጅ፣ የቅ/ሥ/መ/ኮሌጅ የሐዲስ ኪዳን ትርጓሜ መምህር ደጉ ዓለም ካሣ፣ አባ ምንይችል ከሠተ፣ ሊቀመዘምራን ኪነጥበብ ወልደ ቂርቆስ፣ ዲ/ን ሙሉጌታ ኃ/ማርያም የማኅበረ ቅዱሳን ዋና ጸሐፊ፣ በፊልሙ የተሳተፉና ተጋባዥ አርቲስቶች እንዲሁም ምዕመናን ተገኝተዋል።

hyawEwnet.jpg

የዚህን የፊልም ምረቃ ከሌሎች በሀገራችን ከተመረቁ ፊልሞች ለየት የሚያደርገው፣ ብዙ ሕዝብ ተገኝቶ የመረቀው ፊልም በመሆኑ ነው። የመርሐ ግብሩ መሪ ዲ/ን አባይነህ ካሴ ከዚህ በፊት በሌሎች የፊልም ምርቃት ላይ መገኘቱን አውስቶ ብዙዎቹ ፊልሞች ሲመረቁ የሚገኘው የሕዝብ /የተመልካች/ ብዛት እምብዛም ነው በማለት በመድረክ ላይ አስታውቋል።

በፊልሙ ምርቃት ላይ ሊቀመዘምራን ኪነ ጥበብ ወልደ ቂርቆስ ዝማሬ አቅርበዋል፣ ዲ/ን ያረጋል አበጋዝ “የተደፈኑትን ጉድጓዶች አስቆፈረ”ዘጸ 26፥18 በሚል ርዕስ ትምህርተ ወንጌል ሠጥተዋል። ሊቀ ትጉሃን ቀሲስ ዶ/ር ሙሉጌታ ሲሳይ የማኅበረ ቅዱሳን ዋና ሰብሳቢ  የማኅበረ ቅዱሳንን መልእክት አስተላልፈዋል።
 
የማኅበሩን አመሠራረት ከመነሻው ጠቅሰው የአገልግሎቱን ዘርፈ ብዙነትም፤ ይህም አገልግሎት ከሀገራችን አልፎ በአውሮፓ፣ በአሜሪካ እንዲሁም በሌሎች የአፍሪካ ሀገራት በልዩ ልዩ የህትመት ውጤቶች፣ በራዲዮ፣ በመካነ ድርና የተለያዩ ዐውደ ርዕዮችን በማዘጋጀት ቤተ ክርስቲያንንና ሀገራችን ኢትዮጵያን በሀገር ውስጥና በውጭ ሀገራት አስተዋውቋል፤ በማስተዋወቅም ላይ ይገኛል። አሁንም አገልግሎቱን በማጠናከር በሀገራችን በዓይነቱ የመጀመሪያ የሆነውን መንፈሳዊ ፊልም አዘጋጅቶ አቅርቦላችኋል በማለት ገልጸዋል።

በመቀጠል የኢ/ኦ/ተ/ቤተ ክርስቲያንም የሥነ ጽሑፍና የሥነ ጥበብ ምንጭ እንደመሆኗ መጠን ያላት ታሪክና የሥነ ጽሑፍ ሀብት ገና በአግባቡ ያልተዳሰሰና ብዙ  የሚያሠራ ነው። በዚህም ምክንያት ማንኛውም የፊልም ጸሐፊ የመረጠውን ጭብጥ የማቅረብ እድሉ እጅግ ሰፊ ነው። በዚህም በኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ/ሰ/ማ/መ/ ማኅበረ ቅዱሳን የኦዲዮ ቪዥዋልና ሥነ ጥበባት ሥራዎች ማእከል ቤተ ክርስቲያን ለሀገራችን ያበረከተችውን አስተዋጽኦ በዋናነት በማንሳትና የሀገራችንን ባህልና ወግ የሚያንፀባርቅና በቤተ ክርስቲያን ላይ የሚሠራውን ደባ መንፈሳዊ ቀናኢነት፣ ሃይማኖትን ሥልጣኔን የአባቶቻችን ጽኑ ሀገራዊ ጀግንነት በጉልህ የሚታይበት መንፈሳዊ ፊልም ሰርቶ እነሆ ዛሬ ለምረቃ አቅርቧል።

ፊልሙም በእውነት ኢትዮጵያዊ በሆነ አቀራረብ የተዘጋጀ ሲሆን በተመስጦ በዘመናት መካከል ወደ ኋላ ወስዶ የቤተ ክርስቲያንን የሥልጣኔ በር ከፋችነት በማስረዳት በቁጭት የሚያነሳሳ፣ የሚያስተምር፣ ማንነትን የሚያሳውቅ፣ አርዓያና ምሳሌ እንዲሁም ማሣያ የሚሆን መንፈሳዊ ፊልም ነው።

ዝግጅቱም በታዋቂ አርቲስቶችና ከተለያዩ የቤተ ክርስቲያኗ አካላት የተውጣጡ ከ400 በላይ በሆኑ የቤተ ክርስቲያኗ ልጆች የተሠራ ነው። ‘ሕያው እውነት’ ፊልም አጠቃላይ ሥራው በአንድ ዓመት ከዘጠኝ ወራት መሥራት የተቻለ ሲሆን የአርቲስቶቹንና የተሳታፊዎችን ነፃ ድጋፍ ሳይጨምር ከ285,000.00 ብር በላይ ወጪ እንደወጣበት ለመረዳት ተችሏል።

ይህ ፊልም ከምረቃ በኋላ ሁሉም ኅብረተሰብ እንዲያየው የማኅበሩ መዋቅር በሚደርስባቸው ቦታዎች ሁሉ ለእይታ ይቀርባል። በመጨረሻም በቪ ሲዲ ና በዲቪዲ ታትሞ ለምዕመናን የሚቀርብ ይሆናል።

በፊልሙ የሚገኘው ገቢ ማኅበሩ በከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ውስጥ የሚማሩ ወጣት ተማሪዎችን ለማስተማርና ስብከተ ወንጌልን ለማስፋፋት ማኅበራዊ ችግሮችን ለመፍታት እንዲሁም የአባላትንና የምዕመናንን ጉልበትና እውቀት አስተባብሮ ገዳማትና አድባራትን በጊዜያዊነት እንዲረዱና በቋሚነት ከችግር እንዲወጡ ለማድረግ የሚውል ይሆናል።

የማኅበሩ ኦ/ቪ/ሥ/ማእከል ይህ ለቤተ ክርስቲያን የመጀመሪያ የሆነውን መንፈሳዊ ፊልም የማዘጋጀት ሂደት ከፍተኛ ልምድ አግኝቶበታል። በቀጣይም ይህን ልምድ በመጠቀም የተሻለ ሥራ ይዞ ለመቅረብ፣ የአፄ ዘርዐ ያዕቆብን ታሪክ ና የቅድስት እናታችን የወለተ ጴጥሮስን ገድል በፊልም መልክ በመሥራት ጽሑፉን የማዋቀር ሥራ ጀምሯል። በአጭር ጊዜም ለማጠናቀቅ ይታሰባል።

በአጠቃላይ በዚህ ደረጃውን ጠብቆ የቤተ ክርስቲያንን ትምህርተ ሃይማኖት፣ ሥርዐትና ትውፊት ሣያፋልስ ቤተ ክርስቲያን ለሀገሪቱ ያበረከተችውን ሥልጣኔ እንዲያሳይ እንዲሁም የሀገራችንን ባህልና ወግ እንዲያንፀባርቅ ተደርጎ በተሠራው መንፈሳዊ ፊልም ላይ ለተሳተፋችሁ የቤተ ክርስቲያን ልጆች፣ አርቲስቶች እንኳን ደስ! አላችሁ እያልኩ በቀጣይም ምክራችሁና የሙያ ድጋፋችሁ እንዳይለየን በእግዚአብሔር ስም እጠይቃለሁ፤ ከፊልሙ ጋር መልካም ቆይታ እንድታደርጉ እጋብዛለሁ። በማለት ንግግራቸውን ጨርሰው የፊልሙን ምርቃት አብስረዋል።

ፊልሙም ታይቶ ሲያበቃ በምረቃው ላይ በተገኙ ብጹአን አባቶች፣ ከቤተ ክርስቲያን ሊቃውንት፣ ከፊልም ባለሞያዎችና አርቲስቶች አንዲሁም ከተሣታፊዎች መካከል አስተያየቶቻቸውን እንዲሰጡ እድሎች ቀርበው ሃሳብ ተሰጥቷል።

ዶ/ር አባ ኃ/ማርያም መለሠ በመጀመሪያም ይህን ፊልም ተዘጋጅቶ እንዲቀርብ ላደረገ ለማኅበረ ቅዱሳን ምስጋናቸውን አቅርበው ከፊልሙም ያገኙትን ጭብጥ “ፊልሙ ሃይማኖታዊና ማኅበራዊ ፋይዳ ያለው ነው በማለት አስረድተዋል። ይህ ደግሞ ለአዲሱ ትውልድ ፈር ቀዳጅና አስተማሪ ነው። ወደ ኋላ ራሱን እንዲያስተውል የሚያደርግና ጽናቱን የሚፈትሽ በመሆኑ ፍጹም አስተማሪ ነው። ታሪክ የሚሠራው ከታሪክ ነው። ታሪክ ሕይወት አለውና በየዘመኑ ከትውልድ ወደ ትውልድ ይተላለፋል። ታሪክ እንደ ሰው አካል ስላለው አካሉ እንደተጠበቀ መቆየት ይኖርበታል። አካሉን ማጉደል ተጠያቂ ያደርጋልና ከዚህ መንፈሳዊ ፊልም የተማርነው መንፈሳዊ የፍትሕ አሰጣጥ፣ ጥንታዊ እይታን ወደ ኋላ እንድናስብ፣ የሽማግሌዎች ሚና እንዲሁም ባህሎቻችን፣ ሥርዐቶቻችን ምን ያህል ጠንካራ እንደነበሩ እንደናስተውልም የሚያስተምር መንፈሳዊ ፊልም ነው። ታሪክ የአንድ ሕዝብ መለኪያ መነሻና መደረሻ እንደመሆኑ መጠን ራሱን ማየት የሚችለው ራሱን ሆኖ በመሆኑ ይህ ፊልም ለኢትዮጵያውያን ራሳችንን በመስታወት እንድናይ ያስቻለ ፊልም ነው። ዘመኑንም ራስን እንዳለ ጠብቆ ነገር ግን ወደኋላ ራሱን እንዲያይ ዘመኑን እንደ መስታወት ተጠቅሞ /ቴክኖሎጂውን/ በእድገት ላይ እድገት ለመጨመር መጀመሪያ ከራስ እድገት መነሣት ስለሚገባ ፍጹም አስተማሪ ነው።” በማለት በዚህ ፊልም መደሰታቸውንና ሌሎች ፊልሞች ተዘጋጅተው አማራጮች ቢኖሩ የቤተ ክርስቲያንንም ሆነ የሀገራችንን ታሪክ እንድናስተውል ያደርጋል ሲሉ ሀሳባቸውን ገልጸዋል።

የቅድስት ሥላሴ መንፈሳዊ ኮሌጅ መምህር የሆኑት መምህር ደጉዓለም ካሣ ይህን ፊልም ያዘጋጁትን አካላት አመስግነው ይህ ፊልም በከተማ ብቻ ተወስኖ እንዳይቀር በተለይም በገጠሪቷ የሀገራችን ክፍል የጥንቷን ቤተ ክርስቲያን ያልተበረዘ እምነት የያዙ ምዕመናንን ቢያዩት ለዚህም የተለየ ቦታ ተፈልጎ ችግሩን የማያውቁት እነርሱ ናቸውና ፊልሙ ቢታይ በጣም ጥሩ ነው ብለዋል። በመጨረሻም በአቡጊዳ ትምህርት፣ በመልእክተ ዮሐንስ፣ በዳዊት፣ በዜማ፣ በቅኔ ብዙ ያልሄዳችሁ በዘመናዊ ትምህርት የበለጸጋችሁ ስትሆኑ የእናንተን አካሄድ በቤተ ክርስቲያን ቀጥ አድርጎ ያቆመ እግዚአብሔር ይክበር ይመስገን በማለት ንግግራቸውን ቋጭተዋል።

ከመንፈሳዊና ከሙያዊ አንጻር የተሰጡ አስተያየቶችን የመድረክ መሪው በይፋ በመቀበል በመጨረሻም ስፖንሰር ላደረጉ ድርጅቶች፣ በፊልሙ ለተሳተፉ አርቲስቶችና የተለያዩ እገዛዎችን ላደረጉ ሰዎች በብጹአን አባቶች የምስክር ወረቀት የተሰጠ ሲሆን በብጹእ አቡነ ሚካኤል ቡራኬ የፊልሙ ምርቃት መርሐ ግብር ፍጻሜ ሆኗል።
                                                         ወስብሐት ለእግዚአብሔር
                                                                             አሜን።
     

stlalibela1.jpg

የገና በዓል አከባበር በቅዱስ ላልይበላ አብያተ ክርስቲያናት

በወ/ኪዳን ጸጋ ኪሮስ
 
በብርሃነ ልደቱ ዋዜማ ከቅዱስ ላልይበላ አብያተ ክርስቲያናት በዓሉን አስመልክቶ የማኅበረ ቅዱሳን የአማርኛ መካነ ድር በስልክ ከደብሩ ዋና አስተዳዳሪ ከሆኑት ቆሞስ አባ ገ/ኢየሱስ መኮንንና ከአገልጋይ ካህናት ጋር ያደረግነውን ቃለ ምልልስ በአጭሩ እንደሚከተለው አቅርበናል መልካም ንባብ።
 
አማርኛ መካነ ድር፦ የበዓል አከባበር ሥርዐቱ ምን ይመስላል?
ቆሞስ አባ ገ/ኢየሱስ መኮንን፦ በዛሬው ዕለት ማለትም ታህሣሥ 29 ቀን የጌታችን የመድኃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ የልደት በዓልና የገናናው ንጉሥ የቅዱስ ላልይበላ የልደት በዓል በአንድነት ይከበራል።
በዓሉ በቦታው አገልጋይ በሆኑ 670 ካህናትና በአካባቢው በሚገኙ አብያተ ክርስቲያናት በሚያገለግሉ ከ500 በላይ በሚሆኑ ካህናት ታጅቦ ማህሌቱ ይካሄዳል፤ በዚህ በዓል መላው ነዋሪ ‘ካህን’ የመስሎ ሚታይበት አከባበር ነው፤ የማህሌት ሥነ ሥርዐቱ 2፡30 (ማታ) ብጹእ አቡነ ቄርሎስ  የሰሜን ወሎ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ መሪነትና ሌሎች ብጹአን አባቶች በሚገኙበት በየዓመቱ ይከበራል።
በዓሉ በእንዲህ ዓይነት ሁኔታ መከበር የጀመረው ከ900 ዓመት በፊት ነው። ከታህሳስ 23(በዓለ ጊዮርጊስ) ጀምሮ እስከ ዛሬ (ታህሳስ 28) ድረስ ሁሌም 2፡00 ሰዓት ሲሆን የሥርዐተ ማህሌት ደወል ይደወልና በአገልግሎት ይታደራል።
ይህ በዋዜማው የሚካሄደው የማህሌት ሥርዐት 1፡30 አካባቢ የሚጀመር ሲሆን ልዩ የሚያደርገው የራሱ ቀለምና ዜማ ያለውና ሙሉ ሌሊቱን በወረብ ዝማሬ እየቀረበ የሚታደር መሆኑ ነው።
የማህሌት ሥነ ሥርዓቱ በብጹዕ አቡነ ቄርሎስ አባታዊ መሪነትና በአስተዳዳሪው አስተባባሪነት እንዲሁም በመሪጌታው በሚመሩ ከ7 ባልበለጡ አስተናጋጆች በሥርዓት ይካሄዳል።የማህሌቱን አካሄድ ስንመለከትም አንድ ጊዜ ከ 12 ያልበለጡ ጥንግ ድርብ የለበሱ’ አንድ ጊዜ ደግሞ ከ 12 ያልበለጡ  ጥቁር ካባ የለበሱ  በድምሩ 24 ሊቃውንተ ቤተክርስቲያን ከቀኝና ከግራ ሆነው በተራ እያሸበሸቡ ያስኬዱታል፡፡
 
stlalibela1.jpg
ማህሌቱም ማዕጠንት በያዙ 4 ካህናትና ከ8 ያላነሱ ዲያቆናት ወርቅ ካባ ለብሰው፣ የወርቅ አክሊል ደፍተው፣ የወርቅ መስቀል ይዘው መለከት እየነፉ ዙሪያውን በመዞር ማህሌቱን ያጅቡታል። የዚህም ምሳሌነቱ ክርስቶስ ዳግም ሲመጣ መላእክት መለከት እንደሚነፉ ለመግለጥ ሲሆን ለማህሌቱ ትልቅ ድባብ ይፈጥራል። የማዕጠንት ሥርዐቱ ካህናቱ በሊቀ ካህናቱ፤ ዲያቆናቱ በሊቀ ዲያቆኑ ይመራሉ። 
  ከሌሊቱ 10 ሰዓት ጀምሮ በአስራ አንዱም ቤተመቅደስ የቅዳሴ ሥርዐት ይፈጸማል። በተለይም ያሉትን ቆራብያን በተቀላጠፈ መልኩ ለማስተናገድ በቤተ ማርያምና በቤተ መድኃኒዓለም በሁለት ልዑክ ቅዳሴው ይከናወናል።
 
ከ12፡00 ሰዓት ጀምሮ ጥንግ ድርብ፣ ካባ እንዲሁም ልብሰ ተክህኖ የለበሱ ካህናት ከአስራ አንዱ ቤተመቅደስ ከእያንዳንዳቸው ከአስራ ሁለት ያላነሱ ካህናት ይህንን ያሬዳዊ ዜማ ለማጀብ ወደ ማሜ ጋራ /ቤዛ ኩሉ ዓለም ሥነ ሥርዓት የሚካሄድበት ቦታ/ ይወጣሉ።
stlalibela.jpg

 
ልክ አንድ ሰዓት ሲሆን ከላይና ከታች የሚሰለፉ ካህናት ቦታቸውን ይይዙና እስከ 4 ሰዓት በሚፈጅ ክንውን እየተቀባበሉ ለሀገር፣ ለወገን፣ ለምድር ሰላም በረከት የሚጸለይበት ‘ቤዛ ኩሉ ዓለም ዮም ተወልደ’  የተባለው የቀለም ክንውን ይካሄዳል። እንግዲህ የበዓሉን አከባበር በቅዱስ ላልይበላ ልዩ የሚያደርገው አንዱ ይህ “ቤዛ ኩሉ ዓለም” የሚባለው የቀለም ዓይነት ነው።
አማርኛ መካነ ድር፡- የቅኔ ሥርዐቱስ ምን ይመስላል?
 
ቆሞስ አባ ገ/ኢየሱስ መኮንን፡-ቅኔ የሚሠጠው የሠዓቱ ሁኔታ ታይቶ ብፁዕ ሊቀ ጳጳሱ ተጠይቀው ሲፈቅዱ ከ3 ያላነሱ የቅኔ ባለሞያዎች (የቅኔ መምህራን) ያራምዱታል (ያስኬዱታል)። በዚህ ክብረ በዓል ላይ የሚቀርቡት ቅኔዎች ጥልቅ ምስጢር ያዘሉ ናቸው፡፡
አማርኛ መካነ ድር፡-አባታችን በመጨረሻ የሚያስተላልፉት መልዕክት ካለ?
 
ቆሞስ አባ ገ/ኢየሱስ መኮንን፡- ይህ በዓል ለመላው የኢትዮጵያ ህዝብ ኩራት በመሆኑ በውጪ ላሉ ሰዎች መተዋወቅ ያለበትና ሁላችንም ለዚህ የበኩላችንን አስተዋፅኦ መወጣት ይገባናል፡፡ ይልቁንም በመንፈሳዊ አገልግሎታችን በቤተክርስቲያናችን ሥርዐት የሚከበረው ይህ በዓል ልዩ ስሜት የሚፈጥር በመሆኑ ለሁሉም መተዋወቅ የሚገባው ነው፡፡
በመጨረሻም በዓሉን ለማክበር ከተለያየ ቦታ ከአውሮፓ፣ ከአሜሪካ፣ ከኤዥያ፣ ከአፍሪካ እንዲሁም ከመላው ኢትዮጵያ የመጡ ምዕምናን በዓሉን በሰላም አክብረው ወደየመጡበት በሰላም እንዲመለሱ የእግዚአብሔር ቸርነት ይሁንልን፡፡ የጻድቁ የቅዱስ ላሊበላ በረከትም ከሁላችን ጋር ይሁን።
 
የጌታችን የመድኃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ የልደት በዓል በመላው  ዓለም የሚከበር ሲሆን  በቅዱስ ላልይበላ በድምቀት የሚከበረው ከቅዱስ ላልይበላ የልደት በዓል ጋር አብሮ በመሆኑ ነው።በዚህ በዓል በርካታ የሀገር ውስጥና የውጭ ሀገር ምዕመናን መንፈሳዊ በዓሉን ለማክበርና በረከት ለመሳተፍ የሚጓዙ ሲሆን ሌሎቹም አብያተ ክርስቲያናቱንና መንፈሳዊ የበዓል ሥርዐቱን ለመጎብኘት ነው። ይህም በዓል ሃይማኖታዊ፣ መንፈሳዊ፣ ትውፊታዊ፣ ባህላዊ፣ ኢኮኖሚያዊና ሀገራዊ ፋይዳ አለው።ይህንንም ለማስረገጥ በየዓመቱ ያለማቋረጥ ምዕመናን ከተለያዩ የዓለማችን ክፍሎች መምጣታቸው ነው።
 
በተጨማሪ ኢአማንያን ይህንን መንፈሳዊ ቦታ ካዩ በኋላ ከሥላሴ ልጅነት አግኝተው ወደተለያዩ ዓለም ተመልሰዋል። ይህም በዓሉ ለአካባቢውና ለሀገራችን ብሎም ለውጭ ሀገር ዜጎች በየዓመቱ እንዲናፈቅ ሆኗል።

 

የጌታችን የመድኃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ ሣህልና ምሕረት
የጻድቁ የቅዱስ ላሊበላ ረድኤትና  በረከትም ከሁላችን ጋር ይሁን። አሜን።

 
hyawEwnet.jpg

ማኅበረ ቅዱሳን የመጀመሪያ ፊልሙን ሊያስመርቅ በዝግጅት ላይ ነው፡፡

በተ/ሥላሴ ጸጋ ኪሮስ

hyawEwnet.jpgበማኅበረ ቅዱሳን ኦዲዮ ቪዥዋልና የሥነ ጥበባት ሥራዎች ማእከል ‹‹ሕያው እውነት›› በሚል ርዕስ የተሠራው ፊልም በአዲስ አበባ የስብሰባ ማእከል ጥር 1 ቀን 2003 ዓ.ም ይመረቃል፡፡

በፋሲል ግርማ የተዘጋጀው ይህ ፊልም የኢትዮጵያ ኦ/ተ/ቤ/ክ ለሀገሪቱ ሥልጣኔ ያበረከተችውን አስተዋጽኦ በዋናነት ያወሣል፡፡ በቤተ ክርስቲያን ላይ የሚሰራው ደባ፣ መንፈሳዊ ቀናዒነት፣ ሃይማኖትና ስልጣኔ የአባቶቻችን ጽኑ ሀገራዊ ጀግንነት ከታሪክ ማኅደር እየተቀዳ በጉልህ የሚታይበት ነው፡፡

ፊልሙ በድርጊት የተሞላና ልብ አንጠልጣይ /suspense/  በሆነ ውብ አቀራረብ የተዘጋጀ ነው፡፡ በተመስጦ በዘመናት መካከል ወደ ኋላ ወስዶ የቤተክርስቲያንን የሥልጣኔ በር ከፋችነት በማስረዳት በሞራልና በቁጭት የሚያነሳሳ፣ የሚያስተምር፣ ማንነትን የሚያሳውቅ አርዓያና ምሳሌ የሚሆን መንፈሳዊ ፊልም ነው በማለት ከማኅበረ ቅዱሳን መካነ ድር ጋር ቆይታ ያደረጉት የኦዲዮ ቪዥዋልና የሥነ ጥበባት ማዕከል ሥራ አስኪያጅ አርቲስት ቶሞስ በየነ ገልጸዋል፡፡ በቤተ ክርስቲያኒቱ ምዕመናን ዘንድ ተወዳጅ እንደሚሆን ይገመታል ያሉት አርቲስት ቶማስ በቤተ ክርስቲያን ታሪክ በዚህ ደረጃ (standard) ፣አቀራረብና ይዘት የመጀመሪያ የሚሆን ፊልም ነው ብለዋል፡፡
በፊልሙ ላይ የአላዳንኩሽም ፊልም መሪ ተዋናይ አርቲስት ዮሐንስ አፈወርቅ እንዲሁም በተለያዩ ፊልሞችና ቲያትሮች የምናውቃቸው አርቲስተ ሳምሶን ግርማ፣ አርቲስት ሞገስ ቸኮል፣ አርቲስት ትዕግሥት ግርማ፣ አርቲስት አብርሃም ቀናው፣ አርቲስት በፍቃደ ከበደ፣ አርቲስት ዘበነ ሞላ እንዲሁም ሌሎችም የሀገራችን ታዋቂ ተዋንያን ተሣትፈውበታል፡፡

ከ400 በላይ ሰዎች የተሳተፉበት ይህ ፊልም ከ250.000 ብር በላይ ወጪ ተደርጎበታል፡፡ ወጪውን የትራንስፖርት፣ የምግብ፣ የቁሳቁስ፣ የአልባሳት፣ ወዘተ ወጪ ብቻ ሲሆን ታዋቂ ተዋንያን በፊልሙ ላይ የተወኑት ያለ ክፍያ ለአገልግሎት እንደሆነ አርቲስት ቶማስ ተናግረዋል፡፡

አያይዘውም የኪነጥበብ ምንጭ ቤተ ክርስቲያን ናት፤ ማንኛውም ክርስቲያን ሙያዊ አስራት ማቅረብ አለባቸው፡፡ የኪነ ጥበብና የሙያ ሰዎችም በሙያቸው ቤተክርስቲያንን ሊያገለግሉ ይችላሉ ብለዋል፡፡

አሁንም ሊሠራ ተጽፎ ኤዲቶሪያል ቦርድ የገባ እንዲሁም ገና እየተዘጋጀ ያለ ፊልም አለን በእነዚህ ፊልሞች የካሜራ ባለሞያዎች፣ ኤዲተሮች፣ ዳይሬክተሮች የራሳቸውን አስተዋጽኦ በማበርከት የልጅነት ድርሻቸውን ቤተ ክርስቲያንን በማገልገል ሊወጡ ይችላሉ ብለዋል፡፡

የፊልሙ ገቢም በዋናነት የማኅበሩን የስብከተ ወንጌል ለመደገፍ እንደሚውል የገለጹት አቶ ቶማስ በተጨማሪም የማኅበሩን ህንጻ ማስፈጸሚያ ገቢ እንደሚስያስገኝ ይታመናል፡፡ ስለሆነም ምዕመናን በፊልሙ እየተማሩ ትሩፋትን እንዲሠሩ ይሆናል ማለት ነው፡፡ በማለት ይጠቀልላሉ፡፡

ፊልሙ በማኅበሩ የሀገር ውስጥ 39 ማእከላትና በውጭም በአሜሪካ፣ በካናዳ፣ በአውሮፓ፣ በኬንያ፣ በደቡብ አፍሪካ፣ በግብጽ፣ በጅቡቲ፣ በኢየሩሳሌም፣ በተባበሩት አረብ ኢምሬትስና በሌሎችም አገሮች ለእይታ ይቀርባል፡፡ በተጨማሪም የተለያዩ ቴአትር ቤቶች በመከራየትና በቤተክርስቲያን ልዩ ልዩ መድረኮች ለዕይታ ይበቃል፤ በመጨረሻም በዲቪዲና ሲዲ ታትሞ ለገበያ ይቀርባል፡፡

ledeteegzie.jpg

የጌታችን የመድኃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ የልደት በዓል

ledeteegzie.jpg

የተከበራችሁ የእግዚአብሔር ቤተሰቦች የጌታችን የመድኃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ የልደት በዓልን አስመልክቶ በመካነ ድር አድራሻችን እንዲሁም በስልክ ተደጋጋሚ ጥያቄ በመጠየቁ ይኽንን አስመልክተን ከማኅበረ ቅዱሳን የሚዲያ ዋና ክፍል ኃላፊ ከሆኑት ከዲያቆን ብርሃኑ አድማስ ጋር ጥቂት ቆይታ አድርገን የሚከተለውን ምላሽ አግኝተናል መልካም ንባብ፡፡

አማርኛ መካነ ድር፡- ብዙ ምዕመናን በስልክና በኢሜል የጌታችን የመድኃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ የልደት በዓል አርብ ነውና የሚውለው፣ ይበላል? ወይስ አይበላም? የሚል ጥያቄ አንስተዋል፤ የቤተ ክርስቲያናችንን ሥርዐት መሠረት አድርገው ምላሽ ቢሠጡን?
 
ዲ/ን ብርሃኑ አድማስ፡- ፆመን በመብልና በደስታ ከምናከብራቸው በዓላት ውስጥ ሦስቱ ልደት፣ ጥምቀትና ትንሣኤ ናቸው፡፡ ‹‹ወእምድኅረዝ ፍትሑ ፆመክሙ እንዘ ትትፈሥሁ ወእምትሐስዩ ሶበ እግዚእነ ኢየሱስ ክርስቶስ ተንስአ እምነ ምውታን….››፣ ‹‹….ከዚህ በኋላ ፈፅሞ ደስ እያላችሁ ፆማችሁን በመብልና በመጠጥ አሰናብቱ…›› እንዲል ፍትሐ ነገሥት ከትንሣኤ ጋር አነካክቶ በሚናገረው አንቀጽ፡፡ ትንሣኤ ሁሌም እሑድ ቀን የሚውል በመሆኑ ቀዳሚት ስኡርን በአክፍሎት ከመፆም በቀር ሌላ ተጨማሪ ትዕዛዝ የሌለበት መሆኑን የቤተ ክርስቲያናችን የሥርዐት መጽሐፍ ያስረዳሉ፡፡ ጥምቀትና ልደት ግን ከአዋድያት በዓላት ውስጥ ስለሆኑ የሚውሉበት (የሚከብሩበት) ዕለት የሚለዋወጥ ነው፡፡ ረቡዕና አርብን ጨምሮ በማንኛውም ዕለት ቢውሉ የሚበላ (የማይፆም) መሆኑን በቤተ ክርስቲያናችን ቀኖና መጽሐፍ ላይ ተጠቅሷል፡፡ ለምሳሌ፡- በቤተ ክርስቲያናችን ቀኖና መሠረት ፆመ ነቢያት 44 ቀን የሚፆም ሲሆን 40 ቀን የሙሴ፣ 3 ቀን የአብርሃም ሶርያዊው አንዷ ቀን ደግሞ ጋድ በመሆን ስለሚፆም በዓሉ ረቡዕም ዋለ አርብ ሁልጊዜ ይበላል እንጂ አይፆምም፡፡
በመሆኑም ይኽ የጌታችን የመድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የልደት በዓል አርብ ዕለት የሚውል ቢሆንም የሚበላ (የማይፆም) መሆኑን የቤተ ክርስቲያናችን የሥርዐት መጽሐፍ ላይ ተጠቅሷል፡፡
አማርኛ መካነ ድር፡- በቤተ ክርስቲያናችን ሥርዐት መሠረት የጌታችን የመድኃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ የልደት በዓልን እንዴት ማክበር አለብን?

ዲ/ን ብርሃኑ አድማስ፡-
ከላይ የጠቅስናቸው ሦስቱም በዓላት በቤተ ክርስቲያናችን ሥርዐት መሠረት ቅዳሴያቸው በመንፈቀ ሌሊት ይከናወናል፡፡ ከቆረብን በኋላም ፆሙን በመበል፣ በመጠጥ፣ በፍፁም መንፈሳዊ ደስታ ማሰናበት እንደሚገባን በመጽሐፍ ላይ ተጠቅሷል፡፡ መንፈሳዊ ደስታ ሲባል ግን ጥቅም (ረብ) የሌለው ነገር በመናገር ማክበር እንደሌለብን (እንደማይገባን) የተረዳ ነው፡፡ አንድ ሰው መብል መጠጥ በማብዛት ሊደሰት አይገባውም፤ በእውነት ሌሎችም በዚህ አልተጠቀሙም፡፡ እህልን ልንሄድበት ልንቆምበት ነው እንጂ ልንሰናከልበት አልተሰጠንምና፡፡
በእነዚህ በዓላት አንድ ሰው ከቤተሰቡ በሞት እንኳ ቢለየው አያልቅስ ምክንያቱም በበዓላቱ የምናገኘው ደስታ ካጣነው ቤተሰብ ጋር የሚነፃፀር ስላልሆነ፤ በዚህ ዓለም በሚሊዮን የሚቆጠር ብር ያገኘ ሰው አንድ ልብስ ጠፋብኝ ብሎ እንደማያዝን፤ በጌታችንም በልደቱ፣ በጥምቀቱና በትንሣኤው ያገኘነው መንፈሳዊ በረከት ከፍተኛ ስለሆነ በእነዚህ እለታት ማዘን ማልቀስ ፈፅሞ የተከለከለ ነው፡፡ በቤተ ክርስቲያናችን የሥርዐት መጽሐፍት ቀኖና ይገባዋል ይላሉ፡፡

አማርኛ መካነ ድር፡-
በመጨረሻም የሚያስተላልፉት መልዕክት ካለ?
 
ዲ/ን ብርሃኑ አድማስ፡- እንግዲህ በመጽሐፍትም እንደተጠቀሰው በዓሉ የሰላም፣ የፍቅር፣ የአንድነት እንዲያደርግልን የእርሱ ፈቃድ እንዲሆን እመኛለሁ፡፡
 
ወስብሐት ለእግዚአብሔር፡፡

qanaze.jpg

ለባለ ትዳሮች የተዘጋጀ መርሐ ግብር

qanaze.jpg
qana.jpg

ቃና ዘገሊላ

qana.jpg

የሃይማኖት አባቶች የቀድሞ የደርግ ባለሥልጣናትን ወክለው ይቅርታ አቀረቡ።

መ/ር መንግስተአብ አበጋዝ

የአራት የሃይማኖት ተቋማት መሪዎች የቀድሞ የደርግ ባለሥልጣናትን የይቅርታ ጥያቄ ለኢትዮጵያ ሕዝብና መንግሥት አቀረቡ።

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን፣ የኢትዮጵያ ካቶሊካዊት ቤተ ክርስቲያን፣ የኢትዮጵያ ወንጌላዊት ቤተ ክርስቲያን መካነ ኢየሱስ እና የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት የሃይማኖት መሪዎች ቅዳሜ ታኅሳስ 9 ቀን 2003 ዓ.ም በኢንተርኮንቲኔንታል ሆቴል ተገኝተው በሰጡት የጋራ መግለጫ ይህን የታሪክ ጠባሳ በአገራዊ ይቅርታና ዕርቅ መጨረስ ከሁሉ በላይ ታላቅ መንፈሳዊ አንድምታ ይኖረዋል ብለዋል።
ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ጳውሎስ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ጉባኤውን ወክለው ባቀረቡት መግለጫ ላለፉት ሁለት ዓመታት ለጉዳዩ ስኬታማነት ሲሠሩ መቆየታቸውን ገልጸዋል። ከኢትዮጵያ ሕዝብና መንግሥት በሚያገኙት ይሁንታ ታኅሣሥ 21 ቀን 2003 ዓ.ም አጠቃላይ ሀገራዊ እርቅ እንደሚካሄድ ተናግረው፥ መላው የኢትዮጵያ ሕዝብ ይህንኑ መንፈሳዊ ጥሪ ተቀብሎ በጎ ምላሽ እንደሚሰጠን በመተማመን ይህን የሰላምና የዕርቅ ሐሳብን ይዘን ቀርበናል በማለት አስረድተዋል።

«ብፁዓን ገባርያነ ሠላም፥ እስመ እሙንቱ ውሉደ እግዚአብሔር ይሰመዩ።
የሚያስታርቁ ብፁዓን ናቸው፥ የእግዚአብሔር ልጆች ይባላሉና»  ማቴ 5፥9