Entries by Mahibere Kidusan

‹‹እንግዲህ እግዚአብሔር ያለማወቅን ወራት አሳልፎ አሁን በየቦታቸው ንስሓ ይገቡ ዘንድ ሰውን ሁሉ ያዛል›› (ሐዋ.፲፯፥፴)

ለጊዜው ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ ይህን ስብከት የሰበከው አሕዛብ ለነበሩ የአቴና ሰዎች ቢሆንም፤ ለእኛም ጭምር ትልቅ መልእክትን የያዘ ቃል ነው፡፡ በተለይም ‹‹እንግዲህ እግዚአብሔር ያለማወቅን ወራት አሳልፎ አሁን በየቦታቸው ንስሓ ይገቡ ዘንድ ሰውን ሁሉ ያዛል፤››…..

ቅዱሱን መስቀል ቀብሮ ማስቀረት ቤተ ክርስቲያንንም ማዳከም አይቻልም

ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ ‹‹የመስቀሉ ነገር ለሚጠፉ ሰዎች ዘንድ ስንፍና ነውና፤ ለምንድነው ለእኛ ግን የእግዚአብሔር ኃይል ነው›› በማለት የተናገረው መስቀል እና ቤተ ክርስቲያን ለሚያምኑ ሰዎች ተጋድሎው የክብር መገለጫ ሲሆን ለማያምኑት ግን ሞኝነት መስሎ ስለሚታያቸው ነው።

ያልተጻፈን ከማንበብ፣ የሌለን ታሪክ ከመጥቀስ መቆጠብ ያስፈልጋል

በጥፋት የታወሩ፣ በወንጀል የተጨማለቁ፣ በሐሰት ታሪክ የታጀሉ ወገኖች ቤተ ክርስቲያንን በጥፋተኝነት ሲወቅሷት፣ በቅኝ ገዥነት ሲያሳጧት ይደመጣሉ፡ እነዚህ ወገኖች ከእነሱ የተለየ አመለካከት ያላቸውን አካላት በመተቸት አንድም ተባባሪያቸው ለማድረግ፣ በሌላ በኩል ደግሞ ተሳስታችኋል ብለው እንዳይተቿቸው በር በመዝጋት የሚጠቀሙበት ስልት ነው፡፡