‹‹አልጋህን ተሸክመህ ሂድ›› (ዮሐ.፭፥፩-፱)
ለሠላሳ ስምንት ዓመታት በደዌ ዳኛ በአልጋ ቁራኛ ተይዞ የነበረው አንድ በሽተኛ ሰው በጌታችን ቃል ተፈውሶና አልጋውን ተሸክሞ ወደ ቤቱ መሄዱ በቅዱስ መጽሐፍ ተመዝግቧል፡፡
This author has not written his bio yet.
But we are proud to say that Mahibere Kidusan contributed 976 entries already.
ለሠላሳ ስምንት ዓመታት በደዌ ዳኛ በአልጋ ቁራኛ ተይዞ የነበረው አንድ በሽተኛ ሰው በጌታችን ቃል ተፈውሶና አልጋውን ተሸክሞ ወደ ቤቱ መሄዱ በቅዱስ መጽሐፍ ተመዝግቧል፡፡
የክብር ባለቤት ጌታችን አምላካችንና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የተሰቀለበት መስቀል የተገለጠበትና የተገኘበት መጋቢት ፲ ግማደ መስቀሉን የምንዘክርበት ዕለት ነው። የዚህም የከበረ ዕፀ መስቀል መገለጡና መገኘቱ ሁለት ጊዜ ሆኗል። መጀመሪያ የጻድቁ ንጉሥ የቈስጠንጢኖስ እናት በሆነች በንግሥት ዕሌኒ እጅ ነው።
ቤተ መቅደስ ከሁለት ጥምር ቃላት የተገኘ ትርጓሜው ‹የተቀደሰ ቤት› የሚል ሲሆን ይህም የእግዚአብሔር አምላካችን ማደሪያ ወይም ቤት ነው፤ ቤተ መቅደስን የሚወክሉ አካላትም ሦስት ናቸው፡፡
ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ መርቆሬዎስ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ በቀድሞው አጠራር ጎንደር ክፍለ ሀገር በአሁኑ በደቡብ ጎንደር ዞን በአንዳቤት ወረዳ ልዩ ስሙ አረጊት ኪዳነ ምሕረት ገዳም አካባቢ ከአባታቸው ከብላታ ፈንታ ተሰማና ከእናታቸው ከወ/ሮ ለምለም ገሠሠ በ ፲፱፻፴ ዓ.ም ተወለዱ፡፡
ተአምራቱና ትሩፋቱ እንደ ሰማይ ከዋክብት የበዛ የእግዚአብሔር ማደሪያ የሆነው ጻድቅ አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ የዕረፍቱ ቀን መታሰቢያ መጋቢት ፭ ነው፡፡ ይህም ቅዱስ አባት በተወለደበት ቀን ድንቅ የሆነ ሥራን ሠራ፤ ተነሥቶ ከእናቱ እቅፍ ወርዶ “ከጨለማ ወደ ብርሃን ላወጣኸኝ ለአብ ለወልድ ለመንፈስ ቅዱስ ምስጋና ይገባል” በማለት ሰግዷል፡፡
‹‹ከመሥዋዕት ይልቅ ምሕረትን እወዳለሁ፤ የሰንበት ጌታዋ የምሕረት አባቷም እኔ ነኝ፤ የሰው ልጅም የሰንበት ጌታዋ ነው፡፡ ያባቴን ቤት የንግድ ቦታ አታድርጉት››
ውድ አንባብያን! እንደምን ሰነበታችሁ? የእግዚአብሔር አምላካችን ስም የተመሰገነ ይሁን! ባለፈው የትምህርታችን ክፍለ ጊዜ የ ‹‹ሀ፣ አ፣ ወ እና የ›› የሚያመጡት የርባታ ለውጥ በግሥ ርባታ አስተምረናችሁ ነበር፡፡ በዚህ ሳምንት ደግሞ ለሰጠናችሁ መልመጃ ምላሽና ስለ ዝርዝር ርባታ እንመለከታለን፤ በጥሞና ተከታተሉን!
ቅድስት ማለት ‹የተለየች፣ የነጻች፣ የከበረች› ማለት ነው፡፡ ይኸውም ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ጾም የጀመረባት፣ ልዩ፣ የተቀደሰች፣ የከበረች፣ ንጹሕ፣ ክቡር በሚሆን በጌታችን የተጾመች መሆኗን ያመላክታል፡፡ ይህች ጾም በማቴዎስ ወንጌል የተገለጠች ስትሆን፣ አምላካችን በገዳመ ቆሮንቶስ ዐርባ መዓልትና ዐርባ ሌሊት በጾመበት ጊዜያት ሦስቱን አርእስተ ኃጣውእ ድል አድርጓል፡፡ (ማቴ.፬፥፪)
ውድ የእግዚአብሔር ልጆች! ለከበረው ጤንነታችሁ እንዴት አላችሁ? የመንፈቀ ዓመቱ ትምህርት ተጠናቆ ፈተና ተፈትናችሁ ጥሩ ውጤት እንዳመጣችሁ ተስፋችን ነው፤ በርቱ!
ልጆች! ለዛሬ የምንማረው ስለ ዐቢይ ጾም ነው፤ ዐቢይ ማለት ታላቅ ማለት ነው፤ አባቶቻችን በሠሩልን ሥርዓት መሠረት ከሰባት ዓመት በላይ የሆኑ ክርስቲያኖች ሁሉ እንዲጾማቸው የታወጁ ሰባት አጽዋማት አሉ፤ ከእነዚህ መካከል ደግሞ አንዱ ዐቢይ ጾም ነው::
በሰዎች ሕይወት ውስጥ የእግዚአብሔር ክቡር ፍቃድ አለ፤ እነዚህም ሁለት ፍቃዳት ናቸው፡፡ አንደኛው ግልጽ ፈቃድ ሲባል ሁለተኛው ደግሞ ስውር ፈቃድ ይባላል፡፡ ግልጽ ፍቃዳት የሚባሉት በመጽሐፍ ተጽፈው የምናነባቸው ናቸው፤ በሕግ መልክ በብሉይ እና በሐዲስ ኪዳን የተቀመጡልን ትእዛዛቱ እንድንሰማቸው፣ እንድንማራቸው፣ እንድንኖራቸው የተሰጡትን ነው፡፡ መጽናናትን፣መረጋጋትን ገንዘብ የምንዳርባቸው፣ ተግሣጽንና ምክርን የምንሸምትባቸው ገባያችን ናቸው፡፡