Entries by Mahibere Kidusan

ወርኃ ግንቦት

በቀደምት ዘመናት ይኖሩ የነበሩ ኢትዮጵያውያን በተለይም ምእመናን ስለ ወርኃ ግንቦት (የግንቦት ወር) የነበራቸው አመለካከት የተሳሳት እንደነበር ታሪክ ያስረዳል፡፡ በዚያን ጊዜ ወቅቱ የተረገመ እንደሆነ በማሰብም ማንኛውንም ተግባር አይፈጽሙም ነበር። በዚህ ወቅት ነገሮች ሁሉ መጥፎ የመሆን ዕድል እንዳላቸው በማመን ምንም ዓይነት ምግባር አያከናውኑም፡፡ በርካቶችም የሚሠሩት ቤት ወይም የሚያስገነቡት ሕንፃ ፍጻሜው ጥሩ እንደማይሆንላቸው ያስቡ ነበር፡፡ ትዳር በግንቦት ወር የፈጸሙ ምእመናን ካሉ መጨረሻው እንደማያምር ያምኑም ነበር። ለዚህም አስተሳሰባቸው የሚያነሡት ሁለት ምክንያቶች የተሳሳቱ ናቸው፡፡…

ልደታ ለማርያም

በግንቦት አንድ ቀን አምላክን የወለደች እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ተወለደች። እርሷም ለሰው ሁሉ ወገን ድኅነት የሆነባት ናት፡፡ ከወንዶች ወገን የከበረ አባቷም ስሙ ኢያቄም ከሴቶች ወገን የከበረች ሚስቱ ሐና ይባላሉ፡፡ ሁለቱም ልጅ በማጣት ሲያዝኑ ኖሩ። በዚያ ወራት የመካኖች መብዓ ካህናቱ አይቀበሉም ነበርና፡፡ እነርሱም ከሰው የሚደርስባቸውን ሽሙጥና ኅዘናቸውን ያርቅላቸው ዘንድ በቀንና በሌሊት ወደ እግዚአብሔር ፈጽሞ ይማልዱ ነበር፡፡ ሰውን የሚወድ እግዚአብሔርም ከዘራቸው ለዓለሙ ሁሉ መድኃኒት ይሆን ዘንድ መልካም የሆነ ሐሳባቸውን ተመለከተ፡፡ ክቡር ኢያቄምም አርባ ቀን እስኪፈጸም በተራራ ውስጥ ቁሞ ሲጸልይ ከእግዚአብሔር የታዘዘ መልአክ ተገለጸለትና ለዓለሙ ሁሉ ድኅነት የሚደረግባት ዘር እንደሚሰጠው አበሠረው፡፡

ቅዱስ ማርቆስ

ውድ የእግዚአብሔር ልጆች! እንዴት አላችሁ? እንኳን ለዚህ ዕለት አደረሳችሁ! በእግዚአብሔር ምሕረት፣ በትንሣኤው ትንሣኤያችን ተበሥሮልን ከዛሬ ዕለት ደረስን! በቸርነቱ ለዚህ ያደረሰን ፈጣሪ ይመስገን!

ውድ የእግዚአብሔር ልጆች! ለዛሬ ያዘጋጀንላቸሁ የወንጌላዊው ቅዱስ ማርቆስን ታሪክ ነው፡፡

ዘርና ቦዝ አንቀጽ

የተወደዳችሁ አንባብያን! እንደምን ሰነበታችሁ? የእግዚአብሔር አምላካችን ስም የተመሰገነ ይሁን! በዓለ ትንሣኤን በሰላም እንዳሳለፋችሁ ተስፋ እናደርጋለን፤ መልካም!

ታስታውሱ እንደሆነ ባለፈው የትምህርት ክፍለ ጊዜያችን ‹ንዑስ አንቀጽና ቅጽሎች› በሚል ርእስ አስተምረናችኋል። በዚያም መሠረት ትምህርቱን በተረዳችሁበት መጠን እንድትሠሩትም የሰጠናችሁ መልመጃ ነበር። ስለዚህም በዚህ ትምህርት ክፍለ ጊዜ ላቀረብንላችሁ የመልመጃ ጥያቄዎች ምላሻቸውን እንዲሁም ስለ ‹ዘርና ቦዝ አንቀጽ› አቅርበንላችኋል፤ በጥሞና ተከታተሉን!

ምስካዬ ኅዙናን መድኃኒዓለም ገዳም

ምስካዬ ኀዙናን መድኃኒዓለም በታሪካዊ ሂደቱና በአገልግሎቱ የተለያዩ ሥራዎችን በመጀመር ለሌሎች ቤተ ክርስቲያናት አርአያ የሆነ ገዳም ነው፡፡

የቅዱስ ጊዮርጊስ በዓለ ዕረፍት

በሚያዝያ ሃያ ሦስት ቀን ፀሐይና የአጥቢያ ኮከብ የተባለ ታላቅና ክቡር የሆነ የሰማዕቱ የቅዱስ ጊዮርጊስ የምስክርነት ፍጻሜ ሆነ፡፡

‹‹ልቤም በማዳንህ ደስ ይለዋል›› (መዝ.፲፪፥፭)

በሰው ዘንድ የነበረውን መርገም በማጥፋት የሁሉም ፈጣሪ አምላካችን እግዚአብሔር ሞትን ድል አድርጎ ዓለምን አዳነ። ትንሣኤ ሙታን በተባለው የሙታን መነሣትም ነፍስና ሥጋ ተዋሕደው በመነሣት የዘለዓለማዊ ሕይወት መገኛ ጥበብ ወይም የድኅነት መንገድ ሆነልን፡፡

እንኳን ለበዓለ ትንሣኤ አደረሳችሁ!

ውድ የእግዚአብሔር ልጆች እንዴት አላችሁ? እንኳን ለዚህ ዕለት አደረሳችሁ! በእግዚአብሔር ቸርነት የጾሙ ጊዜ ተፈጽሞ፣ በትንሣኤው ትንሣኤያችን ለተበሠረበት ዕለት ደረስን! በቸርነቱ ለዚህ ያደረሰን ፈጣሪ ይመስገን!

ትንሣኤ

ለሰው ልጆች ዘለዓለማዊ ትንሣኤ በኩር የሆነው የክርስቶስ ትንሣኤ ነው፡፡ መድኃኒዓለም ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ለአባታችን ለአዳም በገባው ቃልኪዳን መሠረት በአይሁድ እጅ መከራ መስቀልን ከተቀበለና ነፍሱን በራሱ ሥልጣን አሳልፎ ከሰጠ በኋላ ዐርብ በ፲፩ ሰዓት ዮሴፍና ኒቆዲሞስ መስፍኑ ጲላጦስን አስፈቅደውና ከመስቀል አውርደው ዮሴፍ ራሱ ባሠራው መቃብር በንጹሕ በፍታ ገንዘው ቀበሩት፤ መቃብሩንም ገጥመው ሲሄዱ ጸሐፍት ፈሪሳውያንና መስፍኑ በመቃብሩ ላይ ማኅተማቸውንና ጠባቂዎችን አኖሩ፡፡ በሦስተኛው ቀን እሑድ በእኩለ ሌሊት መግነዝ ፍቱልኝ መቃብር ክፈቱልኝ ሳይል በታላቅ ኃይል ሙስና መቃብርን አጥፍቶ ተነሣ!!!

አንተ ጽኑ አለት ነህ

በጽናትህም ላይ እሠራለሁ መቅደስ

እያለ ሲነግረው ጌታችን  ለጴጥሮስ

በምድርም ያሠርኸው በሰማይ ይታሠር

በሰማይ ይፈታ የፈታኸው በምድር

ብሎ ሾሞት ሳለ በክብር ላይ ክብር

መሳሳት አልቀረም አይ መሆን ፍጡር!