‹‹እግዚአብሔር ልቡናንና ኵላሊትን ይመረምራል›› (መዝ.፯፥፱)
ልበ አምላክ ነቢዩ ዳዊት ‹‹እግዚአብሔር ልቡናንና ኵላሊትን ይመረምራል›› በማለት አስተምሯል፡፡ (መዝ.፯፥፱) ከዚህም ቃል እንደምንረዳው አምላካችን የሚሣነው ነገርም ሆነ ከእርሱ የሚሠወረውም ነገር እንደሌለ ነው፡፡ ሁሉንም ሳንነግረው የሚያውቅ አምላክ እንደሆነ ያሰብነውን ብቻም ሳይሆን ገና ያላሰብነውን እግዚአብሔር ያውቃል፡፡
This author has not written his bio yet.
But we are proud to say that Mahibere Kidusan contributed 976 entries already.
ልበ አምላክ ነቢዩ ዳዊት ‹‹እግዚአብሔር ልቡናንና ኵላሊትን ይመረምራል›› በማለት አስተምሯል፡፡ (መዝ.፯፥፱) ከዚህም ቃል እንደምንረዳው አምላካችን የሚሣነው ነገርም ሆነ ከእርሱ የሚሠወረውም ነገር እንደሌለ ነው፡፡ ሁሉንም ሳንነግረው የሚያውቅ አምላክ እንደሆነ ያሰብነውን ብቻም ሳይሆን ገና ያላሰብነውን እግዚአብሔር ያውቃል፡፡
በግሪክ ቋንቋ ኒቆዲሞስ የሚለው ቃል ትርጓሜ ድል ማድረግን ወይም አሸናፊነትን የሚያመለክት ነው፡፡ በዘመነ ሥጋዌ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ወንጌልን በሚሰብክበት ጊዜ አንድ ፈሪሳዊ ከአይሁድ አለቆችና መምህራን ወገን የሆነ ኒቆዲሞስ የተባለ ሰው እንደነበረና የጌታችንን ቃል በሌሊት ወደ እርሱ በመሄድ እንደተማረ በወንጌለ ዮሐንስ ተጠቅሷል። (ዮሐ.፩፥፪)
በተከበረች መጋቢት ፳፱ ቀን ለእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም የከበረ መልአክ ገብርኤል የምሥራች የነገረበት ድኅነትን የተመላች ታላቅ በዓል ናት፡፡ በዚህም የከበረ ወንጌል ምስክር ሆኗል፡፡
የተወደዳችሁ አንባብያን! እንደምን ሰነበታችሁ? የእግዚአብሔር አምላካችን ስም የተመሰገነ ይሁን! በተከታታይ በሁለት ክፍል የግሥ ዝርዝር ርባታ እንዳቀረብንላችሁ ይታወቃል፤ በዚህ የትምህርት ክፍለ ጊዜያችን ደግሞ የመጨረሻውን ክፍል ይዘንላችሁ ቀርበናል፤ በጥሞና ተከታተሉን!
ለዓለም ሁሉ ድኅነት መድኃኒዓለም ኢየሱስ ክርስቶስ መጋቢት በባተ በ፳፯ኛው ቀን በመስቀል ላይ ተሰቀለ፡፡ በክርስቶስ ክርስቲያን የተባልን ልጆቹም ይህን እናዘክር ዘንድ ዓይን ልቡናችንን ወደ ቀራንዮ እናንሣ!
በጎ አገልጋይ ለጌታው ታምኝ እንደመሆኑ ‹‹ገብር ኄር›› ይባላል፡፡ ይህም ስያሜ ለዐቢይ ጾም ስድስተኛ ሳምንት እንደተሰጠ የቤተ ክርስቲያን አስተምህሮ ይገልጻል፡፡ የስያሜው መነሻ የሚገኘው ደግሞ በዕለቱ ሥርዓተ ቅዳሴ ከሚነበበው በማቴዎስ ወንጌል ክፍል ነው፡፡ (ማቴ.፳፭፥፲፬-፴)
የዓለም መድኃኒት አምላካችን ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ዘንባባና ልብስ ተነጥፎለት በአህያ ውርንጭላዋ ተጭኖ ቤተ መቅደስ የገባበት ዕለት ‹‹ጥንተ ሆሣዕና›› በቅድስት ቤተ ክርስቲያናችን ይዘከራል፡፡ ሆሣዕና ማለት ‹‹አሁን አድን›› ማለት ነው፤ (ማሕቶተ ዘመን ገጽ ፻፷)
ከኢየሩሳሌም በስተምሥራቅ የሚገኝ ቦታ የሚገኘው ተራራ ደብረ ዘይት የጸሎተ ሐሙስ ማታ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የተያዘበት ነው፡፡ ቤተ ፋጌ እና ቢታንያ በኮረብታው ጫፍ እና በምሥራቅ ዳገት ላይ ይገኛሉ። ጌታችን ኢየሱስ ስለ ቤተ መቅደሱ መፍረስ፣ ስለ ዓለም ፍጻሜና ስለ ዳግም ምጽአት በዚህ ተራራ ላይ ተናገሯል።
ውድ አንባብያን! እንደምን ሰነበታችሁ? የእግዚአብሔር አምላካችን ስም የተመሰገነ ይሁን! ባለፈው የትምህርታችን ክፍለ ጊዜ የግሥ ርባታ የመጀመሪያውን ክፍል አቅርበንላችኋል፤ እንደተረዳችሁት ተስፋ እንዳርጋለን፤ ለዛሬ ደግሞ ሁለተኛውን ክፍል እንደሚከተለው አቅርበንላችኋል፤ በጥሞና ተከታተሉን!
ውድ የእግዚአብሔር ልጆች! እንዴት አላችሁ?! የጾምን ወቅት እንዴት እያሳለፋችሁት ነው? አባቶቻችን ሊቃውንት ስለ ጾም እንዲህ ይላሉ፤ ጾም ማለት ከምግብና ከውኃ መከልከል ብቻ ሳይሆን ከክፉ ሥራም መታቀብ (መከልከል) ነው፤ ጾም የጽድቅ በር ናት፤ ጾም ለመልካም ነገር የምታነሣሣን ናት፡፡
ውድ እግዚአብሔር ልጆች! ከጸሎትና ከስግደት ጋር እንዲሁም ትምህርት በማይኖረን በዕረፍት ጊዜያችን ደግሞ ቤተ ክርስቲያን በመሄድ በማስቀደስ፣ ታዛዦች በመሆን የጾሙን ጊዜ ልናሳልፍ ይገባል፡፡ መልካም!
ባለፈው የትምህርት ክፍለ ጊዜ ስለ ዐቢይ ጾምና በጾሙ ወቅት ስላሉት ሳምንታት እስከ እኩለ ጾም ድረስ ተመልክተናል፤ ለዛሬ ደግሞ ቀጥሎ ያለውን እንመለከታለን፤ መልካም ንባብ!!!